Volunteering group

Volunteering group Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Volunteering group, Doha.

15/06/2026
11/05/2026

ትርጉም ወደ አማርኛ
የህወሓት ሳምንታዊ መልዕክት
የህዝባችን መንግስት ለድሉ ይዋጋ!
ወደ 2.8 ሚሊዮን ሕዝብ ተወካይ የሆነውና የትግራይ ሕዝብ ውክልና ያለው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከሚያዚያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይፋዊ ሥራውን ጀምሯል። የምክር ቤቱ የመጀመሪያ ጉባኤ ተካሂዶ ፕሬዝዳንት፣ የምክር ቤት ሰብሳቢ እና ምክትል ሰብሳቢ ተመርጠዋል፤ የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈው ሞሽን ፀድቆ በድል ተጠናቋል። የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከፕሪቶሪያ ስምምነት ተከትሎ ለሰላም ሲል ታግዶ ቆይቷል። የብልጽግና ስርዓት ፕሪቶሪያ ስምምነትን ሙሉ በሙሉ ስለናዳው ታግዶ የቆየው የትግራይ ሕዝብ ምክር ቤት ወደ ሥራው መመለስ ግዴታ ስለሆነ ይፋዊ በሆነ መንገድ ወደ ሥራው ተመልሷል።
የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት እንደ ሌሎቹ የትግራይ ሕዝብ ተቋማት ሁሉ ህልውናው እንዲቋረጥና እንዲፈርስ ከውስጥም ከውጭም በተቀናጀ ሁኔታ ዘመቻ ሲካሄድበት ቆይቷል። አሁን በጠላት ጎራ ተሰልፎ የሚገኘው ሀገራዊ ክህደት የፈፀመው ቡድን ምክር ቤቱን ለማፍረስ ያልቀደደ ድንጋይ የለም። ከዚህ በተጨማሪ የትግራይን አቅም ለበተን የጠላትን ጎን ይዞ የትግራይ ሕዝብ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት፤ "ሉዓላዊነቴ ይመለስ፣ ሞትና ስቃይ ይቁም፣ ወደ መኖሪያዬ ጉዞ ይቻልልኝ፣ የጅምላ ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ይረጋገጥ" ሲል ጦርነት ፈላጊ የሚለውን መሰየሚያ እየለጠፈ ዝምታ እንዲጠብቅ ሲያደርገው ቆይቷል። ይህም ትግራይ ሕዝብን እንደ ሕዝብ ለማጥፋት በዕቅድ እየሰራ ላለው የብልጽግና ስርዓት ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ሲሆን የትግራይ ሕዝብ ሁኔታ ከሕሙም ወደ ሕሙም ወደ ከፋ እያሽቆለቆለ እንዲሄድ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል።
ስድስተኛ ዘመን ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤትን ለማስቆም ያስችሉናል የተባሉ ሁሉም መንገዶች ከውስጥም ከውጭም በተቀናጀ ሁኔታ ተሞክረዋል። ሕዝባችንንና የምክር ቤት አባላትን ለማሸበር ተኩስ ተከፈተ፤ የብልጽግና ስርዓት ድሮኖች በመቀሌ ሰማይ ላይ ሲዞሩ ቆዩ፤ ጉባኤው በሚካሄድበት ሰዓት ደግሞ የጦር አይሮፕላን ልኮ ለማስተጓጎል ሞከረ። ሆኖም ግን የምክር ቤቱ አባላትም ሆኑ አመራሩ መስዋዕትነት ቢጠይቅ እንኳ ለትግራይ ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚከፈል መስዋዕትነት ነው ብለው ሊወስኑ ያቀዷቸውን አጀንዳዎች ተወያይተው ጉባኤያቸውን በድል አጠናቀቁ።
የትግራይ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ፈፃሚ አካሉን ዘርግቶ እየሰራ እንዲቆይ ምክር ቤቱ በሰጠው ኃላፊነት መሰረትም የካቢኔ የመጀመሪያ ስብሰባ አካሂዶ ይፋዊ ሥራውን ጀምሯል። የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት መመለሱ ለትግራይ ሕዝብ የትግል መድረክ ይሆናል። ትግራይ ስርዓት ያለው ያለምክር ቤት ቁመና ባለው መንግስት እንድትተዳደር፣ ፈፃሚ አካሉ ላይ ቀጣይ ክትትልና ተጠያቂነት እንዲሰፍን የሚያደርግ ነው። ዋናው ደግሞ የትግራይ አቅሞችን በማደራጀት የትግራይ ሕዝብ ሀገራዊ ተቋማት እንደ ሕዝብ ተፈናቅሎ ካለው አደጋ ጋር የሚጣጣም አቋምና አደረጃጀት ፈጥረው እንዲሰሩ የሚያስችል ነው። በአጠቃላይ ደግሞ በተቀናጀ መንገድ ሲበታተን የቆየው የትግራይ አቅምን ለማሰባሰብ፣ ለሚመጡ ፈተናዎች ለመቋቋም የሚያስችል አቅም የሚፈጥር ነው። በዚህም ሉዓላዊ ድንበር ትግራይ እንዲከበር፣ በወራሪዎች ሥር እየተገደሉና እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችን ነፃ እንዲወጡ፣ የተፈናቀሉና የተሰደዱ ወገኖቻችን ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ፣ የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፃሚዎች ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ፣ የትግራይ ዳግም ግንባታና ፈውስ እንዲጀምር፣ በአጠቃላይ ትግራይ ሕዝብ ካንዣበበበት ህልውና አደጋ ወጥቶ ዋስትናው እንዲረጋገጥ የሚያስችል ትግል ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ድርድርና ውይይት ለማካሄድ ሲደረግ ካለው ጥረት አንፃርም ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው።
ሙሉ የትግራይ ሕዝብ ለሰላም ካለህ ፍላጎት ፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲፈፀም በትዕግስት ስትጠይቅ ቆይተሃል። ሆኖም ግን የብልጽግና ስርዓት ስምምነቱን ሌላ ዓይነት ጅምላ ጭፍጨፋ እያደረጉ ሲጠቀሙበት ቆይቶ አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ አናዷቷል። አሁንም ቀደም ሲል እንደምታደርገው ያንዣበበህን ህልውና አደጋ ለመቋቋም ከመንግስትህና ከመሪ ፓርቲህ ህወሓት ጎን ተሰልፈህ ወሳኝ ሚናህን እንደምትወጣ አይጠራጠርም። ለሚፈጠርልህ አቅም ከዚህ አደጋ ወጥተህ ባትወጣ ብለው ቀጣይ ባለ ሁኔታ ላይ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚደረጉ ዘመቻዎችን ከምንም ጊዜ በላይ ከሀይ ብለህ ለማስቆም ወደ አንድነትህና ድርጅቶቸህ ትኩረት ሰጥተህ ማይቀረውን ድልህን የሚያፋጥን ትግል ማካሄድ ያስፈልጋል።
ታግዶ የቆየው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት መመለሱ ከጦርነትና ከጦርነት ወሬ ጋር ፈፅሞ ያስተሳስረዋል ብለን አናምንም። የትግራይ ሕዝብና አመራሩ ህወሓት አሁንም ቢሆን ሁሉም አለመግባባቶች በድርድርና በውይይት መፈታት አለባቸው የሚለው አቋማቸው ነው። ከዚህ በተጨማሪ በሕዝብ የተመረጠ መንግስት ወደ ሥራው መመለሱ በምንም ዓይነት መልኩ የጦርነት ምክንያት ነው ብለን እንደማናምን በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እንፈልጋለን።
የህዝባችን መንግስት ለድሉ ይዋጋ!
ለሰማዕታቶቻችን ዘለዓለማዊ ዝክርና ምስጋና!
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ!
ሚያዚያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

05/04/2026

እንኳን ለመድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ ዝክር መድዓኒአለም በዓል አደረሰን!

11/09/2025

እንቁ ለእኛ ምናችን ትሆን?"
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

“ክረምት አልፎ በጋ መስከረም ሲጠባ፣
አሮጌ ዓመት ሄዶ አዲሱ ሲገባ፣
አደይ ተከናንባ እንቁጣጣሽ ስትደምቅ፣
ምድር በልምላሜ በፀሐይ ሳቅ ስትሞቅ፣
አዲስ ዓመት ሁሌም አዲስ ይታሰባል፣
ምኞት ይታቀዳል ተስፋ ይታለማል፣
ሁሉም በየቤቱ እንደ አዲስ ይነቃል፣
ሁሉም በየሙያው በአጭር ይታጠቃል፡፡”

#እንቁጣጣሽ( ) ?
የኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያው ወር መስከረም ነው፡፡ ታዲያ እሱ አንድ ብሎ የሚጀምርበት ቀን ዘመን መለወጫ፣ እንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡

ብርሃን፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት የዓመት ኡደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ የመስከረም ወር የመጀመርያ ወይም የዘመን መለወጫ አልያም አዲስ ዓመት እንደተባለ የሀይማኖት መፅሀፍት ይገልጣሉ።

እንቁጣጣሽ እንኳን ደህና መጣሽ እንላለን።
አዲስ ዓመት ሲቃረብ እንቁጣጣሽ ግን ከየት መጣች?

የሀይማኖት መዛግብት “ዕንቁ – ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባውን መፈንዳት ያመለክታል ይሉታል አንዱን ፍች።

ሁለተኛው ደግሞ “ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በእጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኀ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ ይህቺን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል” ይላሉ።

ሌላኛውና የመጨረሻው “ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሣባ የንጉሥ ሰሎሞንን ጥበብ ለማየት ከብዙ ሠራዊቶቿ ጋር የእጅ መንሻ በመያዝ ወደ ንጉሡ ሀገር ሄደች፡፡ ንጉሡም ኢትዮጵያዊቷን ንግስት በደስታ ተቀበላት። በመምጣቷ በመደሰቱም “እንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንሽ” በማለት አራት አይነት ቀለም የሚታይበት በቀንና በሌሊት የሚያበራ ቀለበት ሰጣት። የሰጠበት ወርም ወርኀ መስከረም ነበር፡፡”

ከዚህ በመነሣት እንቁ ለጣትሽ ተሰጠሽ በማለት ለመስከረምና ለአዲሱ ዓመት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ ወጥቷል፡፡

?
ብዙዎቻችን ስኬታችንን፣ ድክመታችንን፣ መሻገራችንን፣ የምንለካው በአዲስ ዓመት ዑደት ነው። እንቁጣጣሽ ስትመጣ ለአዲስ ሰውነት፣ ለመልካም ሥራ፣ ለስኬት፣ ለአብሮነት እናቅዳለን።

እንደሀገር ከተቸገርንባቸው ጉዳዮች ለመሻገር መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

እንቁ ለውበት እንደሆነ ሁሉ ዛሬ ላይ እንቁ ለእኛ ተስፋ፣ እንቁ ለእኛ አብሮነት፣ እንቁ ለእኛ አንድነትና ብልፅግና የሚያስፈልግበት ጊዜና የዘመን መሸጋገርያ ላይ ነን።

አዲስ ዕድል፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ምኞትና አዲስ ስኬት፣ በአዲሱ ዓመት ስንፈልግ እንደ እንቁጣጣሽ ውድ የሆነውን ሰላማችንን በመጠበቅ፣ እንደእንቁ የከበረ ስምና ታሪክ ያላትን ሀገራችንን በአንድነትና በፍቅር በመተጋገዝ ለእድገቷ በመትጋት፣ ካለፈ የታሪክ ቁርሾ ወጥተን በይቅርታና በምክክር ችግራችንን ፈተን በመሻገር፣ ትክክለኛውን እንቁ እንድንገልጥ ያስፈልጋል።

!
🍀🍀🍀🍀🌼🌼🌼🌼🌺🌺🌺

እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን!
ዘመኑ የሠላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የስኬት ይሁንልን!!

Address

Doha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Volunteering group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Featured

  • Koala Nursery

    Koala Nursery

    West Bay –Dafna-district, United Nation Street, opposite to the Lebanese School

Share