07/04/2020
ማስታወቂያ
በደቡብ ክልል ለሚትገኙና ከ7-12 ክፍል ለሚትማሩ ተማሪዎች፣ ለሚታስተምሩ መምህራንና ለተማሪ ወላጆች በሙሉ
ጉዳዩ፡- ከየትምህርት በሬዲዮ ስርጭትን ይመለከታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ዓለምን እያስጨነቀ ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ከመጋቢት 7/2012 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ መደረጋቸው ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ተማሪዎች በቤታቸው በሚያደርጉት ቆይታ ከትምህርት ውጪ መሆን ስለሌለባቸው በራሳቸው የጥናት ፕሮግራም በማውጣት ማንበብ ማጥናትና የተለያዩ መልመጃዎች እየሰሩ እንዲቆዩና ወላጆችም ትምህርት ቤቶች የተዘጉት የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት መሆኑን ተረድተው ልጆቻቸው ከቤት እንዳይወጡ በማድረግ በሽታውን ከመከላከል ጎን ለጎን ትምህርታቸው ላይ ትኩረት አድርገው ፕሮግራም አውጥቶ እንዲያጠኑ በመከታተል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ምክሮችና መልዕክቶች በመገናኛ ብዙኃን ሲተላለፍ ቆይቷል፡፡
አሁንም ቫይረሱ በቁጥጥር ሥር ውሎ ተማሪዎች ወደ መደበኛ ትምህርት እስክ መለሱ ድረስ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር ከ7-12 ክፍል ላሉ ተማሪዎች በክልሉ በሚገኙ በ9 ኤፍ ኤም ቅርንጫፍ ሬዲዮ ጣቢያዎች ሰባት ትምህርት ዓይነቶችን በተመረጡ መምህራን የትምህርት በሬዲዮ ቀረፃውን አጠናቆ ተማሪዎች በቤታቸው ሆነው እንዲከታተሉ የተመቻቸ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
ስለሆነም ከመጋቢት 28/2012 ዓ.ም ጀምሮ
1/ በአርባምንጭ ቅ/ሬዲዮ ጣቢያ ማክሰኞ፣ ሀሙስና እሁድ ከቀኑ 7፡00 እስከ 11፡00 ሠዓት እንዲሁም
ሰኞ፣ ረቡዕ እና ዓርብ ከቀኑ 7፡00 እስከ 12፡00 ሰዓት
2/ ሆሳዕና ቅ/ጣቢያ ማክሰኞ፣ ሀሙስና እሁድ ከቀኑ 7፡00 እስከ 11፡00 ሠዓት እንዲሁም ሰኞ፣ ረቡዕና
ዓርብ ከቀኑ 7፡00 እስከ 12 ሰዓት
3/ በሚዛን ቅ/ጣቢያ ማክሰኞ፣ ሀሙስና እሁድ ከቀኑ 7፡00 እስከ 11፡00 ሠዓት እንዲሁም ሰኞ፣ ረቡዕና
ዓርብ ከቀኑ 7፡00 እስከ 12 ሰዓት
4/ ፍስሀ ገነት ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 7፡00 እስከ 12፡00 ሠዓት
5/ በንሳ ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 7፡00 እስከ 12፡00 ሠዓት
6/ ወልቂጠ ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 6፡00 እስከ 11፡00 ሠዓት
7/ ቦንጋ ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 6፡00 እስከ 12፡00 ሠዓት
8/ በጂንካ ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 9፡00 እስከ 12፡00 ሠዓት
9/ ሳውላ ቅ/ጣቢያ ከሰኞ እስከ ዓርብ ከቀኑ 6፡00 እስከ 12፡00 ሠዓት በተጨማርም በወላይታ፣ በሚዛንና በይርጋለም በሚገኙ ትምህርት በሬዲዮ ማሰራጫ ጣቢያዎቻችን ዘውትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከማለዳው 2፡00 እስከ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ጣቢዎቹ ትምህርቱን ማሰራጨት የሚጀምር መሆኑን እየገለጽን ትምህርቱ የሚተላለፍበት ጊዜ ሰሌዳ ተከታትለን የሚናሳውቅ ሲሆን ተማሪዎች ትምህርቱን እንዲትከታተሉ እያስገነዘብን የተማሪ ወላጆችም ልጆቻቸው ጊዜያቸውን በተገቢው ተጠቅመው መከታተል አለመከታተላቸውን ክትትል እንዲታደርጉ ቢሮ አጥብቆ ያሳስባል፡፡