08/08/2026
።
==============================
ነሀሴ 02/2018 (ወልቂጤ)፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት፣ በጉራጌ ዞን የሚገኙ የወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች በ2018 ዓ.ም. በዲግሪ እና ከደረጃ 1 እስከ 5 ባሉ የሥልጠና መርሃ-ግብሮች ሥልጠናቸውን ያጠናቀቁ በአጠቃላይ 1,041 ሰልጣኞችን በጋራ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመረቁ።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ በወልቂጤ ክላስተር ሥር በሚገኙ ሰባት ኮሌጆች በተለያዩ የሥልጠና መስኮችና ደረጃዎች በመማር ሥልጠናቸውን በብቃት ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን በአንድ የጋራ መድረክ ለማስመረቅ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የኢንዱስትሪ ተወካዮችና ባለቤቶች፣ የኮሌጆች አመራሮችና መምህራን፣ የተመራቂዎች ቤተሰቦች እንዲሁም የተጋበዙ እንግዶች በብዛት ተገኝተው ታድመዋል።
በተለይም የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ በዲግሪ እና ከደረጃ 1 እስከ 5 ባሉ የሥልጠና መርሃ-ግብሮች ሥልጠናቸውን በብቃት ያጠናቀቁ 402 ሰልጣኞችን ማስመረቅ ችሏል። ይህም ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ ብቁ፣ ተግባራዊ እውቀትና ክህሎት የተላበሱ የሰው ኃይል ለማፍራት እያከናወነ ያለውን ሚና የሚያሳይ ነው።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልልና የጉራጌ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኞች፣ ለኮሌጆች አመራሮችና ለመላው የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ቤተሰብ የማበረታቻ መልዕክትና የሥራ አቅጣጫ ሰጥተዋል። አመራሮቹ ተመራቂዎች በሥልጠና ወቅት ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በተግባር በመተርጎም ለራሳቸው፣ ለቤተሰባቸውና ለሀገራቸው የሚጠቅም የሥራ እንቅስቃሴ እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።
በተጨማሪም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የሀገርን የሰው ኃይል አቅም በማጎልበት፣ የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ምርታማነትን በማሳደግና የኢንዱስትሪውን የብቃት ፍላጎት በማሟላት የሚኖረውን ወሳኝ ሚና በማጉላት የሥልጠና ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች በቅንጅት እንዲሠሩ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
የወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች በተለያዩ የሥልጠና ደረጃዎች ያስመረቋቸው ሰልጣኞች የሰለጠኑትን የንድፈ ሀሳብ ከተግባራዊ ሥልጠና ጋር በማጣመር የሥራ ዓለምን ለመቀላቀልና የራሳቸውን የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችል እውቀትና ክህሎት አግኝተዋል።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ በከፍተኛ የደስታና የኩራት ስሜት የታጀበ ሲሆን፣ የክልልና የዞን አመራሮች፣ የተለያዩ ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች አመራሮች፣ የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ተወካዮች፣ የትምህርትና የሥልጠና ተቋማት አመራሮች፣ የተጋበዙ እንግዶች እና በርካታ የተመራቂ ሰልጣኞች ቤተሰቦች በመገኘት ለተመራቂዎቹ ደስታቸውን አጋርተዋል።
የወቂጤ ክላስተር ኮሌጆች በ2018 ዓ.ም. 1,041 ሰልጣኞችን በተለያዩ የሥልጠና ደረጃዎች ማስመረቃቸው በጉራጌ ዞንና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብቁ የሰው ኃይል ልማትን ለማጠናከር የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ የሚያሳይ ነው። በቀጣይም ኮሌጆቹ ከኢንዱስትሪውና ከሌሎች የሥራ ዕድል ፈጣሪ ተቋማት ጋር ያላቸውን ትስስር በማጠናከር፣ የሥልጠና ጥራትን በማሻሻልና በገበያው ፍላጎት መሠረት የተዘጋጀ ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት ለክልሉና ለሀገር ልማት ያላቸውን አስተዋፅኦ ማሳደግ ይጠበቅባቸዋል።
---------------------------
!
!
-----------------------------
Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!