Horn History

Horn History

Share

If you say every thing is possible, it will be possible!

24/01/2026

ከጥንት ጀምሮ እስካዛሬ የቀጠለው የታላቁ ኦሮሞ እና ዎላይታ ህዝብ የወዳጅነት ምስጥር 👇

የታላቁ ኦሮሞ ህዝብ የጀግንነት ተምሳሌት የነበሩ የጅማው ንጉሥ አባጅፋርና የዎላይታው ንጉሥ/ካዎ ጦና እጅግ የጠነከረ መልካም ግንኙነት በመኖራቸው ከጓደኝነትም አልፎ አማቾች ነበሩ። አንዳቸው አንዳቸውን ለማስገበር ብሎ አንድንም ጦርነት አላካሄዱም።

ዛሬ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር የዎላይታ ህዝብ በኦሮሚያ ክልል፣ ኦሮሞውም በዎላይታ ተጋብተውና ተዋልደው እንደ ቤታቸው አድርገው በመቻቻል የሚኖሩበት ምስጥርም ከዚሁ የመሪዎቻቸው ከገነቡት ታሪካዊና ከማይበጠስ ወዳጅነት የመነጨ እንደሆነ ብዙዎች ይመሰክራሉ።

በተጨማሪም ያኔ የተገነባው የዎላይታዎች የአንድነት እና ከየትኛውም ህዝብ ጋር ተስማምተውና አብሮ ሰርተው ጠንክረው የመኖር ስነልቦና የተገነባው በንጉሥ ጦና ጊዜ መሆንንም የታሪክ አዋቂዎች ያስረዳሉ።

ይሄ ስነልቦና ዎላይታዎች ከኢትዮጵያዊያን🇪🇹ወንድሞች ጋር ስቀላቀሉም ሳይቸገሩ እንዲያውም ለሌሎች በአንድነት እና አብረው በመኖር ረገድ ተምሳሌት በመሆን የዘለቁበት ምስጥርም ያኔ በተገነባው ከሌሎች ህዝቦች ጋር አብረው ተስማምተው ለመኖር ያደረጉበት ጠንካራ የካበተ ልምድ መሆኑም ይነገራል።

እንዲያው፦ ንጉሥ ጦና ጋጋ ዎላይታ ሀገር በነበረበት ወቅት ከጅማው ንጉሥ አባ ጅፋር ጋር የነበረው ጠንካራ ዲፕሎማሲ ብቻ ሳይሆን ከአጎራባች ህዝቦች ጋር፣ አልፎም በሀገር እና ሀገርአቀፍ ደረጃ የነበረው አንድነት፣ አብረው መኖር፣ የህዝቦች ወዳጅነትን ለማጠንከር የተወሰዱ ስታራቴጂክ መንገዶች ዛሬ ዘመናዊ አሰራር በሰፈነበት ወቅትም ጠቃሚ መሆናቸው ይነገራል።

ካዎ (ንጉሥ) ጦና ጋጋ እና ንጉስ አባ ጅፋር አማቾች ከመሆናቸው ባሻገር የልብ ወዳጆችና ጓደኛሞች ነበሩ። ከዚህ በተጨማሪ #ዎላይታና #ኦሮሞ የምያመሳስለው ተፈጥሯዊ ጉዳይ፦ ደግነት፣ የዋህነት፣ በጎነት፣ ሰው ወዳድነት እንዲሁም የሰው አክባሪነት በፉጹም ያመሳስላቸዋል ስል የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ።

ከጥንት ጀምሮ እስካዛሬ የቀጠለው የታላቁ ኦሮሞ እና ዎላይታ ህዝብ የወዳጅነት ምስጥርም ከዚሁ የመሪዎቻቸው ከገነቡት ታሪካዊና ከማይበጠስ ወዳጅነት የመነጨ ነው።

21/01/2026

አስገራሚ ዜና፦ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን ዳግም የሚያረጋግጥ ታሪካዊ ግኝት ተመዘገበ!

ኢትዮጵያ በድጋሚ የዓለም የሳይንስ ማህበረሰብ መነጋገሪያ ሆናለች። በአፋር ክልል ሚሌ ሎጊያ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ለ2.6 ሚሊዮን ዓመታት ተቀብሮ የቆየ አዲስ የሰው ልጅ ዝርያ መገኘቱ ተበሰረ።

1. ፓራንትሮፕስ" (Paranthropus) ይባላል።

2. ግኝቱን የመሩት በቺካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑት ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ፕ/ር ዘረሰናይ ዓለምሰገድ ናቸው።

3. ይህ ዝርያ ከዚህ ቀደም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅና አዲስ መሆኑ ተረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኤሊያስ ሽኩር ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ይህ ግኝት ኢትዮጵያ ለሰው ዘር ጥናትና ለአንትሮፖሎጂ ምርምር ያላትን የማይተካ ሚና ይበልጥ እንደሚያጎላው ገልጸዋል።

"ይህ ግኝት ዛሬ በዓለም አቀፉ በታዋቂው ኔቸር (Nature) መጽሔት ላይ ለዓለም ይፋ ይደረጋል።"

አዲሱ ግኝት ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ (Cradle of Mankind) መሆኗን በዓለም መድረክ በድጋሚ ያረጋገጠ ኩራት ነው ተብሏል።

Via FBC

እናንተስ ይህን አዲሱ ግኝት እንዴት አያችሁት?

Photos from Horn History's post 13/01/2026

''ይህን ቤት የወላይታ ነገስታት እንደ ማረፊያ ይጠቀሙ ነበር ''

Daanna(‎ዳና) ባልጣ ቴቃ ይባላሉ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋሙራ ቀበሌ ሌሳሳ መንደር ነዋሪ ናቸው። ዛሬ ፈጣሪ ዕድሜ ሰጥቶ 97 አመታቸው ነው፤ የልጅ ልጅ ልጅ አይተዋል፤ ለወግ ማዕረግም አብቅቷል።

በወላይታ ዘፈን፣ በቀረርቶ እና በሌሎች ባህላዊ ክዋኔዎች Allaana daannaa Aadaye Teeqqa Balxxaa ተብሎ ስማቸው ዘወትር ይነሳል፤ ታዲያ እኚህ ቀደምት ጀግና አባትቨ ያሉበት አካባቢ ታሪክ በመጠየቅ ትውልድን ለማነቃቃት አቶ ባልጣ ቴቃ ቤት አቀናን፤ ጠየቀን እንዲህ እያሉ ጀመሩ...እኛ በወላይታ አላና ዳና ሾቦ 7ኛ ልጆች ነን የዳና ሾቦ ልጅ ቀኛዝማች አቤቶ ፣ ቀኛዝማች አቤቶ የወላይታ ጦር መሪ ጋዳዋ አደሎ ወለዱ፤ ጋዳዋ አደሎ ደግሞ ቀኛዝማች አዳዬን ወለዱ፣ ቀኛዝማች አዳዬ አገባዝ ቴቃን ወለዱ፣ አበጋዝ ቴቃ ደግሞ እኔን ዳና ባልጣን ወለዱ ከዚያ በኋላ የወላይታ መንግስት አስተዳደራዊ ሥርዓት መሰረት ስወርድ ሲዋረድ የመጣው ዳኝነት ሥልጣን በኔ አበቃ ይላሉ'

‎''ይህ አሁን እኛ ያለንበት ቦታ ድሮ ትልቅ የወላይታ ባህላዊ ቤት መሹዋ(Sinaa Meeshuwa) ነበር በዚህ የወላይታ ነገስታት በየንግስና ዘመናቸው ሁሉ መጥተው ይውሉም ያድሩም ነበር ፤ እኔ ልጅ እያለሁ ነው የነገስታት ማረፊያ ቤት የፈረሰው''

‎በዚያን ጊዜ አያቶቻችን በየወቅቱ እዚሁ ቤት ድግስ አሰናድተው ነገስታትን ይቀበሉ ነበር ፤ ምክንያቱም ከክንዶ ዎሻቋ፤ ሻትንታሞ መናገሻ ወደ ላሾ ሣና ሣሲያ፤ ዎሺያ፤ ዎይዴ ጋሩዋ እና ዳሞታ ቤተመንግሥት ሲሄዱ በዚህ በኩል ነበር እና ማረፊያ የኛ ቤት ነበር በማለት ገልጸዋል።

‎በወቅቱ ለንጉሡ ይሆናል ተብሎ የተመረጠ kawote booraa,kalaade ussaa የሚሰጠው እዚህ ነበር። የሚገርመው የንጉስ ሣና ልጅ ንጉሥ ኦጋቶ፣ የኦጋቶ ልጅ ንጉሥ አማዶ፣ የንጉሥ አማዶ ልጅ ንጉሥ ዳሞቴ እዚህ ማደሪያ ነበራቸው፤ ንጉሥ ጎቤ ዳልቦ ቤተመንግሥት መኖር ጀምረውም እዚህ ይመጡ ነበር ይህ ታሪክ ያለው ቤት ነው። ይህ ብቻ አይደለም በወላይታ ባህል ''ዎስታቂያ''(Wosttaqiya)ሥርዓት የሚፈጸመው እና የዳና ሥልጣን(Lambbuddaa maataa) የሚሰጠው በዚህ በራፍ በተዘጋጀው ሥፍራ ነበር እንዲሁም በኃይለሥላሴ ዘመነ መንግስት የቀኛዝማችነት፣ ግራአዝማችነትና ደጃዝማችነት ሥልጣን(Qamisiya Mayzzidi maataa) የሚሰጠው እዚሁ ነበር።

‎በጣሊያን ወረራ ጊዜ ከ1928 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት አመታት የነገስታት ልጆች እነ ቀኛዝማች ዋዳ ደሌ፣ ፊትአውራሪ ደስታ ፍሰሐን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ባለቤቶቻቸውንና ልጆቻቸውን እዚህ ቤት ደብቀው እንደነበረ አወጉን

‎በወላይታ ዘመናዊ ትምህርት እንዳሁኑ ባልተስፋፋበት ዘመን ከዚህ ከካዎ ኮይሻ እስከ ወላይታ ሶዶ ኦቶና ድረስ በእግር ተጉዤ ተምሬያለሁ እና በአካባቢው ከሰው ቀድሜ ፊደል በመቁጠር የዕውቀት ችቦ በመለኮስ ብዙዎችን ወደ ትምህርት አለም ጋብዤያለሁ በማለት ያለፈውን ታሪክ በማስታወስ ብዙ ታሪካዊና ትምህርታዊ ነገሮችን አጫውተውናል።

በወላይታ ቴሌቪዥን!

28/12/2025
Photos from Horn History's post 28/12/2025

በወላይታ አከባቢ ብቻ በየአመቱ በታህሳስ ወር የሚጫወት "ገኗ" ባህላዊ ጨዋታ

በወላይታ በፀደይ ወራት እህል ይሰበሰባል፣ እንደዚሁም በአብዛኛው እርሻ በዎላይታ የምታረስበት ወቅት ሲሆን ድካም የሚበዛበት እንደሆነም ይገለፃል።

Gennuwa በተለይ ወጣቶች Baraataa(ባራታ) "ህዳር"መጨረሻ እና "ከታህሳስ" ወይም Duubbala (ዱባላ) ወር መጀመሪያ አከባቢ ጀምሮ እስከ "የካቲት" (Longgiya) ወር አጋማሽ ድረስ ወጣቶች ከየአካባቢው ተሰብስበው የሚጫወቱት ጨዋታ በውስጡ የያዘ ነው (Gennuwa) "ገኗ በዓል"።

"ገኗ"ባህላዊ መንገድን ተከትሎ የሚከናወን ሲሆን ከእየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊትም ስከበር እንደነበረ የታሪክ ድርሳናት ያውሱታል።

"ገና" በዓል ደግሞ በአብዛኛው ሀይማኖታዊ ይዘት ያለው ሆኖ ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ወድህ የተጀመረ ሆኖ ከእየሱስ ክርስቶስ ልደት ጋር ይገነኛል።

"ገኗ"በወላይታ ከብዙ ሺህ ምዕተ-ዓመት ጀምሮ እየተከበረ የመጣ ነው። ነገር ግን በወቅቱ ከነበሩት ከአፀዎች ስርዕት በተደረገ ጫና "ገኗ" በ"ገና በዓል" ውስጥ እንድገባ እንድጨፈለቅ በመደረጉ "ገኗ" ተውጦ እንድቀር ተደርገዋል።

በነገራችን ላይ (Gennuwa) ገኗ ጨዋታ በወላይታ እና ወላይታ አከባቢ ብቻ የሚከናወን ሲሆን ይህም ለሁለት ወራት ወጣቶች በአንድነት እና በአንድ መንፈስ ሆነው መልካም ምኞታቸውን የሚገልፁበት ልዩ ባህል ነው።

በተለይ የመተሳሰብን ፤ አብሮ ተከባብሮና ተፈቃቅሮ የሚኖሩበትን የአባቶች ፈለግ የምከተሉበት፣ወቅቱ በጋ ስለሆኔ በሥራ የደከመውን ሰውነታቸውን በዛ ጨዋታ የምፈታቱበት፣እንዲሁም የወጣቶች እርስበርስ ግንኙነት ስለሚያጠናክር በወላጆች ዘንድ ትልቅ ይሁንታ የሚሰጥ ልዩ ባህል ነዉ (Gennuwa)"ገኗ"።

በGennuwa ገኗ ሥርዓት ወጣቶች በአንድ ላይ ተሰብስበው መዳማ አካባባቢ ወይም ወደ "ጉታራ" ወጥተው ይሁን "ገኑዋ" ያካሂዳሉ።

ወጣቶች ከየቤታቸው ይዞው የመጡትን "ቁዳ"የሚባል የ"ገኗ"መጨዋቻ ቆልማማ እንጨት በጨዋታ ባህል በ"ጵኑዋ" ተብሎ የሚጠራውን ከእንጨት የሚዘጋጀውን ኳስ ይዞ በመገኘት "ገኑዋ"ይጫወታሉ።

በዚህ ጨዋታ ብዙ ጎል ያስቆጠረ ቡድን በወላይታ "ዋሌስ"(walees)ይባላል።

በጨዋታ ወቅት የእንጨት ኳሷ በድንገት ጉዳት ካደረሰች እንደ ባህሉ አገላለጽ "phinnoy xammiis" ይባላል።

ደግሞ በ"ገኗ" ጨዋታ የራሱ የሆነ ግጥም እና ዜማ ያለውና ከጥንት አባቶች ጋር ተያይዞ የመጣ የ"ገኗ"ዘፈን ይህንን ልዩ ባህልን አጉልቶ የሚያሳይ ነው።

የ"ገኗ"ዘፈን ግጥም እና ዜማ ከጥንት ተያይዞ የመጣና ከሀይማኖታዊ በዓል ጋር ምንም የሚያገናኝ ነገር እንደለለ የሚያረጋግጥ ነው።

በጣም ቅኔ የተሞላበት የዎላይታ ህዝብ ባህላዊ የአዘፋፈን ስልቱ እና ቃላት አጠቃቀሙ ከምያውቁት ከባህሉ ባለበቶች ውጪ ማንም እንዳሻው በዋዛ መተረጎም አይችለም። ለምሳሌ ፦
Genno genno hoy
ገኖ ገኖ ሆይ
Genni gershsho hoy
ገን ገርሾ ሆይ
Ani arshsho hoy
አን አርሾ ሆይ
Achchaa kiiraara hoy
አቻ ክራራ ሆይ
Maahiya makkala hoy
ማህያ ማካላ ሆይ/የነብር ተንኮል
Machchiya gacino hoy
ማችያ ጋጭኖ ሆይ/ምስቱ ወልዳለች
Azinay udulee hoy
አዝናይ ኡዱለ ሆይ/ባሏ መወቀጫ
Uttanay oydee hoy
ኡታናይ ኦይዴ ሆይ
Uyanay gosee hoy
ኡያናይ ጎሴ ሆይ/የምንጠጣው በቅል
Gosiyaa gooro hoy
ጎስይል ጎሮ ሆይ/ቅሉ በራቁት
Waayu halchchaye hoy
ዋዩ ሐልቻዬ ሆይ
Odoruwa balla hoy
ኦዶሯ ባላ ሆይ
Olomuwa tuusaa hoy
ኦሎሟ ቱሳ ሆይ
Maanay malddo hoy
ማናይ ማልዶ ሆይ
Baanay kinddo hoy
ባናይ ክንዶ ሆይ
Sukkul"uwa quunaa hoy
ሱኩልኡ ቁና ሆይ
Eceriya ziitaa hoy
ኤጨርያ ዝታ ሆይ
Haraphphiya yaa"aa hoy
ሃራጵያ ያአ ሆይ/የእርግብ ጉባኤ

Elii elelo elelo ኤል ኤሌሎ
Barandossee barandosee toskka!2x
ባራንዶሴ ባራንዶሴ ቶስካ (2×)
Doyo dooyawu dooyo
ዶዮ ዶያው ዶዮ/ይከፈት ለከፈተው
Aquwa dooyo dooyawu
አቋዋ ዶዮ ዶያው/የሀብት በር
Peeshsha dooyo dooyawu
ፌሻ ዶዮ ዶያው/የውሎ በር
Yeluwa dooyo dooyawu
ዬሏ ዶዮ ዶያው
Haaruwa dooyo dooyawu
ሀሯ ዶዮ ዶያው
Gimaa dooyo dooyawu
ግሟ ዶዮ ዶያው
Keedaa dooyo dooyawu
ኬዳ ዶዮ ዶያው
GiraacaTanattenne Intte Eriyoogaግራጫ ጋንግያ ዶዮ
🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪🇩🇪

18/12/2025

በይርጋለም የሚኖሩ የወላይታ ሴት 1947 ዓም / A Wolayta woman in Yirgalem 1954
#ታሪካችን

18/12/2025

የህንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ማን ናቸው?

#ምልሰት

የህንድ ማህበረሰብ ላለፉት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በሃይማኖታዊ እና በማህበራዊ መዋቅር ላይ የተመሰረተ "የካስት ሥርዓት" (Caste System) በመደብ ተከፋፍሎ የኖረ ነው። እያንዳንዱ ህንዳዊ በተወለደበት ቤተሰብ የሥራ ድርሻ እና በማህበራዊ ደረጃው አራት ዋና ዋና መደቦች ይመደባል።

ብራህሚኖች (Brahmins) የበላይ መደብ በመባል የሚታወቅ ማህበረሰብ ነው። ተግባራቸው ካህናት፣ መምህራን እና ምሁራን ሲሆኑ በሁሉም የህንድ ማህበረሰብ ከፍተኛው ቦታና ደረጃ ይሰጣቸዋል። ኃላፊነታቸውም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን መፈጸም እና እውቀትን ማስተላለፍ ነው።

ክሻትሪያዎች (Kshatriyas) በመባል የሚታወቁት ከብራህሚን ቀጥሎ ያለውን ደረጃ ይይዛሉ። ነገሥታት፣ መሪነት፣ የጦር ሰራዊት አዛዥነት እና የአስተዳደር ኃላፊነት የሚሰጣቸው ናቸው። በአጠቃላይ ማህበረሰቡን መጠበቅ እና ሀገር ማስተዳደር ለዚህ መደብ የተሰጠ ነው።

ነጋዴዎች፣ ገበሬዎች እና የእጅ ጥበብ ባለሙያዎች ደግሞ ቫይሺያዎች (Vaishyas) በመባል የሚታወቀው ሦስተኛ መደብ ማህበረሰብ አባላት ናቸው። መካከለኛውን የማህበረሰብ ክፍል ይወክላሉ።

ጉልበት የሚጠይቁ ስራዎችን የሚሰሩ እና ከላይ ያሉትን ሶስት መደቦች የሚያገለግሉት ደግሞ ሹድራዎች (Shudras) ወይም የአገልጋይ መደብ በመባል ይታወቃሉ።

በህንድ "ዳልቶች" (Dalits) በመባል የሚታወቅ እና ለማህበረሰባዊ ምደባ የማይበቃ ህዝብም አለ። ከላይ ከተጠቀሱት አራት "የማይነኩ" (Untouchables) ተብለው የሚጠሩ የህብረተሰብ ክፍል መደቦች ውጭ ናቸው። እነዚህ በታሪክ እጅግ ዝቅተኛ ተብለው የሚታሰቡ ህዝቦች ቆሻሻ ከማጽዳት ያለፈ ስራና ቦታ አይሰጣቸውም። ለዘመናት ተበድለው ፍትህ መጠየቅ የማይችሉ፣ ተናግረው መታመን ቀርቶ የማይደመጡ ሆነው ኖረዋል።

ይህ ክፍፍል በአገሪቱ የገጠር አካባቢዎች እና በጋብቻ አሁንም ድረስ በስፋት የሚስተዋል ቢሆንም ህንድ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነፃነቷን ካገኘችበት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 15 ቀን 1947 በኋላ በወጣው ህገ መንግስት በመደብ ላይ የተመሰረተ መድልዎ ታግዷል። በዚህም ከመደብ ውጭ ተደርገው የነበረት "ዳልቶች" በትምህርት እና በስራ የኮታ እድል (Reservation System) ተመቻችቶላቸዋል።

#ትውልድ
ናሬንድራ ሞዲ በህንድ ነጻነት ማግስት እ.ኤ.አ. መስከረም 17 ቀን 1950 በጉጃራት ግዛት "ቫድናጋር" በተባለች ትንሽ ከተማ ተወለዱ:: የተወለዱትም ከመደብ ስርዓት ውጭ ከነበረው የ"ዳልት" ማህበረሰብ/ቤተሰብ ነበር:: አባታቸው ዳሞዳርዳስ ሞዲ ሲባሉ እናታቸው ደግሞ ሂራቤን ሞዲ ይባላሉ።

አባታቸው በባቡር ጣቢያ ውስጥ ትንሽ የሻይ መሸጫ ነበራቸው። ሞዲ በልጅነታቸው ሻይ እያፈሉና እያስተናገዱም አባታቸውን ያግዙ ነበር።

#ትዳር
ናሬንድራ ሞዲ 50 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ የትዳር ህይወታቸው ለህንዳውያውን እንቆቅልሽ ነበር:: ጋዜጠኞች የህይወት ታሪካቸው ይጻፍባቸዋል የተባሉ ቅጾችና መ/ቤቶችን ቢያስሱም ቅንያት ማስረጃ ማግኘት አልቻሉም ነበር:: ምክንያቱ ደግሞ ሞዲ "የትዳር ሁኔታ" የሚሉ ቅጾችን ምንም አይጽፉባቸውም ነበር:: ባለትዳር ወይም ያላገባ ብለው ጽፈው አያውቁም::

እውነተኛ የትዳር ህይወታቸው ይፋ የወጣው እኤአ በ2014 ለጠቅላይ ሚንስትርነት በእጩነት ሲቀርቡ ነው:: የህንድ ህግ እጩ ጠቅላይ የትዳር ሁኔታን እንዲገልጽ ያስገድዳል::

በዚህም መሰረት በትዳር ሰነዳቸው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ "ያገባ" ብለው የሚስታቸውን ስም "ጃሾዳቤን" ሲሉ ጠቅሰዋል::

በኋላ እንደተረጋገጠው ሞዲ በ18 ዓመታቸው በቤተሰብ መራጭነት ባህላዊ የጋብቻ ስርዓት ፈጽመዋል:: ይሁን እንጂ ሞዲ ጊዜያቸውም ልባቸውም ከሚስታቸው ጋር አልነበረም:: ሁለነገራቸውን ለፖለቲካው ሰጥተው ለሚስታቸው ' #ባል' መሆን አልቻሉም:: በዚህ ምክንያት ሚስታቸው ጃሾዳቤን ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ በመምህርነት ተቀጥረው ህይወታቸውን በብቸኝነት መርተዋል:: ሁለቱም የጋብቻ ውላቸውን በህግ ሳይቀዱ፣ እንደ ባልና ሚስትም በአንድ ቤት ሳይኖሩና ሳይወልዱ ዛሬም ድረስ ለየብቻ ዘልቀዋል። በአሁኑ ወቅትም መምህርቷ #ጃሾዳቤን ጡረታ ወጥተው ለብቻቸው እንደሚኖሩ ታውቋል።

ጡረተኛዋ ባለቤታቸው ጃሾዳቤን አሁንም ድረስ ለሞዲ ከፍተኛ አክብሮትና ድጋፍ እንዳላቸው የሚዲያ ዘገባዎች ይጠቁማል።

#ትምህርት
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የትምህርት ታሪክ ልክ እንደትዳራቸው አወዛጋቢ ነው። ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸው ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ድረስ የሚገኙ የትምህርት ማስረጃዎቸው ሁልጊዜ የተቃዋሚዎቻቸው አጀንዳዎች ናቸው::

ይሁንና የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተወለዱባት ቫድናጋር ከተማ ውስጥ እንደተማሩ ይነገራል:: እ.ኤ.አ. በ1967 (በ17 ዓመታቸው) የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቅቀዋል። የትምህርት አቀባበላቸው መካከለኛ ተማሪ የነበሩ ቢሆኑም በክርክር ችሎታቸው እና በቲያትር ክህሎታቸው ግን ከፍተኛ ብቃት እንደነበራቸው ይነገራል።

ናሬንድራ ሞዲ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲወዳደሩ ባቀረቡት መረጃ መሰረት ዴሊሂ ዩኒቨርሲቲ (University of Delhi) - የርቀት ትምህርት ክፍል በፖለቲካል ሳይንስ (ዲግሪ) ተመርቀዋል:: የተመረቁትም ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ከጨረሱ ከ11 ዓመታት በኋላ (እ.ኤ.አ በ1978) ነው:: በመቀጠል በተመሳሳይ የትምህርት መስክ እ.ኤ.አ በ1983 ሁለተኛ ዲግሪያቸውን (ማስተርስ) በጉጃራት ዩኒቨርሲቲ እንደተማሩ ማስረጃዎቻቸው ያመላክታሉ:: ሁለትኛ ዲግሪያቸው የተማሩትም በርቀት ሲሆን ከዲግሪ እስከ ማስተርስ "አብረን ተምረናል" የሚሉ እማኞች አለመኖራቸው ተቃዋሚዎቻቸው የመማራቸው ነገር አጠራጣሪ ያደርጉታል::

በተለይም "አም አድሚ ፓርቲ" - AAP እና አንዳንድ የመብት ተከራካሪዎች የዲግሪ ማስረጃዎቻቸው "ፎርጅድ" ወይም ሀሰተኛ ናቸው በሚል በፍርድ ቤት ክስ እስከማቅረብ ደርሰው እንደነበር ይነገራል:: ለምሳሌ፣ በዲግሪው ላይ ያለው የፊደል አጻጻፍ እና የቀኖች አለመጣጣም እንደ ማስረጃ ይጠቀሳሉ። ዋና መከራከሪያቸው የነበረውም በማስተርስ ትምህርት ማስረጃቸው ላይ የተጻፈው " በወቅቱ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ማስተማር አልተጀመረም ነበር' የሚል ነው:: ይሁን እንጂ የዴሊሂ እና የጉጃራት ዩኒቨርሲቲዎች ዲግሪዎቹ ትክክለኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤት በደብዳቤ አረጋግጠዋል:: ይሁንና ዩንቨርስቲዎቹ የተማሪዎች ዝርዝር እንዲያቀርቡ ተጠይቀው የግላዊነት መብትን በመጥቀስ ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ጉዳዩ እስከ ህንድ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች አከራክሮ የዩንቨርስቲዎቹ ምክንያት ተቀባይነት በማግኘቱ ክሱ ውድቅ ተደርጓል:: ተቃዋሚዎች ግን የሞዲ ትምህርት ማስረጃ ጉዳይ ዛሬም ድረስ 'አልተዋጠላቸውም'::



በህንድ RSS እና BJP "እናት እና ልጅ" ወይም "አካል እና መንፈስ" በመባል ይታወቃሉ:: ይኸውም RSS - Rashtriya Swayamsevak Sangh የቀኝ ዘመም የሂንዱ ብሄርተኛ፣ ግብረ-ሰናይ (Volunteer) ድርጅት ነው:: ዓላማውም የህንድን ባህል መጠበቅ እና በሂንዱ እሴቶች ላይ የተመሰረተ ማህበረሰብ መገንባት ነው። ርዕዮተ ዓለሙ "ሂንዱትቫ" (Hindutva) ይባላል። በቀጥታ በምርጫ አይወዳደርም:: ፓርላማ አይገባም፣ ወይም መንግስት አያቋቁምም። ስራው ማህበረሰቡን መቅረጽ እና ካድሬዎችን ማሰልጠን ነው።

BJP (Bharatiya Janata Party) ደግሞ የRSS "የፖለቲካ ክንፍ" ነው። በህንድ ምርጫ ቦርድ የተመዘገበ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ነው። ዓላማው በምርጫ በመወዳደር ስልጣን መያዝ እና ሀገር ማስተዳደር ነው። ለዚህም RSS ህጻናትን ታዳጊዎችን እየመለመለ፣ እየሞረደና በርዕዮተ ዓለሙ እየቀረጸ አሳድጎ ብቁ ፖለቲከኞች ሲሆኑ ለBJP ያስተላልፋል። በአጠቃላይ BJP የRSSን ርዕዮተ-ዓለም ወደ መንግስት ፖሊሲነት የሚቀይር የፖለቲካ ፓርቲ ነው። በምርጫ ወቅት የRSS በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አባላትም ለBJP ቅስቀሳ ያደርጋሉ፤ ድምጽ ይሰጣሉ።

RSS በመንግስት ስራ ውስጥ በቀጥታ ጣልቃ አይገባም። ነገር ግን BJP ከሂንዱትቫ መስመር እንዳይወጣ የሞራል እና የርዕዮተ-ዓለም መመሪያ ይሰጣል።

ሞዲ ገና በ8 ዓመታቸው የተመለመሉትና የተቀረፁት በዚህ RSS በተሰኘ ድርጅት ነው:: በድርጅቱ ርዕዮተ ዓለም እየታነፁ አድገው የወጣቶች አደረጃጀት ውስጥ ሲገቡም ሙሉ ጊዜያቸውን የሚሰጡ "ፕራቻራክ" (አደራጅ) ሆኑ። ይህም የፖለቲካ ዲስፕሊን፣ የማደራጀትና የፖለቲካ ብቃታቸውን አሳድጎታል።

ሞዲ መደበኛ ጋዜጠኛ ባይሆኑም በነበራቸው ከፍተኛ የመጻፍ ችሎታ በጉጃራቲ እና በሂንዲ ቋንቋዎች የተለያዩ መጽሐፍት እና ግጥሞችን ጽፈዋል። በRSS ልሳናት ወይም በRSS የሚደገፍ ህትመቶችም በርካታ ጽሁፎችን አጋርተዋል:: በራሪ ወረቀቶችን ያዘጋጁ እና ያሰራጩ እንደነበርም ይነገራል:: በዚህም "ድብቁ ጋዜጠኛ" እስከመባል ደርሰው ነበር::

RSS እኤአ በ1987 ሞዲን ከፍተኛ የፖለቲካ መዋቅር ወደሆነው BJP ላካቸው። በፓርቲው ውስጥ በነበራቸው የማደራጀት ብቃት ከፍተኛ ተቀባይነት ቢያገኙም የመጡበት ማህበረሰብ የፈጠረባቸው ፖለቲካዊ ጫና ለትልቅ ኃላፊነት ለመታጨት እድሜያቸው 50 ዓመት እስኪሞላ ጠብቀዋል። አያሌ ውስብስብ መሰናክሎችን በብልህነትና በትዕግስት ማለፍ ግድ ብሏቸዋል።

የሞዲ የመጀመሪያው ከፍተኛ ስልጣን እ.ኤ.አ. በ2001 የተሾሙበት የጉጃራት ግዛት ሚንስትርነት ነው። በወቅቱ በአካባቢው የተከሰተውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የነበረው አስተዳደር ተገቢ መከላከል ባለማድረግና ምላሽ ባለመስጠት ተባረረ። ፓርቲው ሞዲን የግዛቱ ዋና ሚኒስትር አድርጎ ሾማቸው። በህንድ የግዛት ሚንስትር ማለት በኢትዮጵያ የክልል ፕሬዝዳንት እንደማለት ነው። በዚህ ኃላፊነት ለ13 ዓመታት (2001-2014) ግዛቱን ሲያስተዳድሩ በኢኮኖሚ ዕድገትና በኢንዱስትሪ ግንባታ የላቀ ለውጥ አስመዝግበዋል። በመልካም አስተደርም ግዛቱን ግንባር ቀደም ምሳሌ አድርገውታል። ይህ ታላቅ ስኬት ፖርቲያቸው BJP ለአገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትርነት በእጩነት ለማቅረብ አስወሰነው።



ህንድ ፖርላማንታዊ ሥርዓት የምትከተል ታላቅ አገር ናት። ጠቅላይ ሚንስትር የሚመረጠው በምክር ቤት አባላት አብላጫ ድምጽ ሲሆን የአንድ ጊዜ የሥልጣን ዘመን ገደቡ አምስት አመታትን የሚዘልቀው የፓርላማ ስራ ዘመን ነው። ይሁንና አንድ ሰው የፓርላማ አባል እስከሆነ ድረስ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ለመወዳደር ወይም በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚችልበት የጊዜ ገደብ የለም።

ናሬንድራ ሞዲ የፓርላማ ምርጫ ቅስቀሳ መርህ 'Acche Din Aane Wale Hain' የሚል ነበር። "ጥሩ ቀናት ይመጣሉ!" እንደማለት ነው።

ተቃዋሚዎች የግል ታሪካቸውን ፈልፍለው በአደባባይ ሞዲ "ሻይ ሲቀዳ የነበረ የደሃ ልጅ ነው" ሲሏቸው በራስ መተማመን ቀና ብለው "እኔ ከናንተ ከድሆቹ መካከል የወጣሁ ነኝ" በማለት ወደ ትልቅ የፖለቲካ ካፒታልነት ቀይረውታል።

"የሚታወቅ ትዳር እና ልጆች የሌሉት፣ ቤተሰብ መርቶና አስተዳድሮ የማያውቅ ሰው" እያሉ ሲዘምቱባቸውም
አንደበተ ርቱዑ ሞዲ "ሕይወቴን የምሰጠው ለሀገሬ ነው፣ ቤተሰብና ልጆች የሉኝም፣ ስለዚህ የምሰርቀውም ለራሴ የማከማቸው ሀብት ሊኖር አይችልም" እያሉ የህዝቡን ጆሮ፣ አይንና ልብ ለመሳብ ቻሉ። በሙስና የተጨማለቀውን የቀድሞ መንግሥት በመተቸትም አዲስ የለውጥ ንቅናቄ ፈጠሩ። በከፍተኛ ድምፅም የፓርላማ አባል ለመሆን ቻሉ። በመጨረሻም ፓርቲያቸውን በመወከል ለጠቅላይ ሚንስትርነት ተጠቁመው በድምጽ ብልጫ አሸንፈው ታላቅ አገር የመምራት ታላቅ የታሪክ ኃላፊነት ተረከቡ።

በመቀጠልም ለሁለተኛ ጊዜ (እ.ኤ.አ. 2019 ) ተመርጠው የጠቅላይ ሚንስትርነት ስልጣናቸውን ለማስቀጠል በቅተዋል:: በቅርቡ (እ.ኤ.አ. 2024) በተካሄደው 18ኛው አጠቃላይ ምርጫ ፓርቲያቸው BJP በብቸኝነት የነበረው መቀመጫ ቢቀንስም ሞዲ ለፓርላማ አባልነት የሚያበቃ ድምጽ አግኝተዋል:: በዚህም ከሌሎች አጋር ፓርቲዎች ጋር በመሆን (National Democratic Alliance - NDA) አብላጫውን ድምጽ በማግኘቱ ለሦስተኛ ጊዜ በጠቅላይ ሚንስትፍነት ተመርጠው ታላቋ ህንድን ይበልጥ ታላቅ እያደረጓት ይገኛሉ::

ይህም ናሬንድራ ሞዲ ከህንድ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ከጃዋሃርላል ኔህሩ ቀጥሎ ለሦስት ተከታታይ ዘመናት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን የተመረጡ ሁለተኛው መሪ አድርጓቸዋል።

Tesfaye Y.Hailu

Photos from Hailemariam & Roman Foundation's post 11/12/2025
10/12/2025

Ethiopia has five UNESCO-inscribed intangible cultural heritages: the Gada System, Meskel (Finding of the True Cross), Fichee-Chambalaalla (New Year for Sidama people), and Timkat (Ethiopian Epiphany),
Wolayta Gifata(New year for Wolayta people)

Photos from Horn History's post 10/12/2025

የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት በመመዝገቡ እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ!

ሕዳር 01፣ 2018ዓ.ም አዲስ አበባ

"ጊፋታ" በሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት መመዝገቡ በዓሉ ባህላዊ ዕሴቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ እና የሀገራችን የቱሪስት ፍሰት እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

"ጊፋታ" በወላይታ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታላቅ በዓል ሲሆን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የሕዝቡ የማንነት መገለጫ የሆነ የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የአዲስ ዓመት መጀመሪያ የመሸጋገሪያ በዓል ነው፡፡

እንኳን ደስ አላችሁ!

Want your school to be the top-listed School/college in Sodo?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Sodo