Halas Technology and Business College

Halas Technology and Business College Degree program and Short term trainings

******ምዝገባ ላይ ነነ*******ሀላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ አሁንም ምዝገባ ጀመረ። አሁኑኑ ይምጡ ለእርሶና ለልጆቾ በቋንቋ ትምርቶች፣ በቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሶፍት ዌር ...
29/10/2024

******ምዝገባ ላይ ነነ*******

ሀላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ አሁንም ምዝገባ ጀመረ። አሁኑኑ ይምጡ ለእርሶና ለልጆቾ በቋንቋ ትምርቶች፣ በቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሶፍት ዌር ስልጠናዎች በከፍተኛ ጥናትና ምርምር አሰራርና አፃፃፍ፣ በፒች ትሪ ሶፍትዌር እና ሌሎችም ይማሩ ።

ኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ

27/10/2024
ኃላስ የቴክኖሎጂና ቢዝነስ  ኮሌጅ በቴክኒክ እና ሙያና በአጫጭር ስልጠና ዘርፎች ለመጀመሪያ ዙር  ያሰለጠናቸውን 150 ተማሪዎች አስመረቀ።በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው...
27/10/2024

ኃላስ የቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ በቴክኒክ እና ሙያና በአጫጭር ስልጠና ዘርፎች ለመጀመሪያ ዙር ያሰለጠናቸውን 150 ተማሪዎች አስመረቀ።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዮ ሳፒ እንደተናገሩት ዛሬ ላይ አደጉ የሚባሉ ሀገራት መሰረታቸው በትምህርትና በምርምር ስራዎች ነው ብለዋል።

ብቃት ያለው ፣ ተወዳዳሪ ፣ ፈጣሪና አካባቢን የሚለውጥ ሀይል ለማፍራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት ሚና የግላ ነው ብለዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ የተለያዩ የትምህርት ፖሊሲዎችን ነድፋ ስትተገብር ቆይታለች ብለዋል። ከቅርብ አመታት ወዲህ ከመንግስት የትምህርት ተቋማት ባሻገር የግሉ ዘርፍ አድማሳቸውን በማስፋት የተማረ ዜጋን በማፍራት ረገድ የድርሻቸውን እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል።

ባደጉ ሀገራት የሀገራቸውን ችግር የፈቱት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት መሆኑን ገልጸው ለዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠትና መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋችሁ ፣ በጥረትና በትጋት ዛሬ ለምረቃ የበቃችሁ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። የተማረ የሰው በማፍራት ረገድ ትልቁን ኃላፊነት ለወሰደው የኃላስ ኮሌጅ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።

የኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጨነቁ ኮንታር በመድረኩ እንደተናገሩት ኮላጁ በ2013 ዓመተ ምህረት ከተለያየ ሙያ በተውጣጡ 50 ግለሰቦችና በ2 ሚሊየን ብር ካፒታል የተመሰረተ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በአካባቢ ቋንቋዎችን ጨምሮ በአጫጭር ስልጠናዎች 3 ዙር ማስመረቁን ገለጸው ዛሬ 150 ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ እያስመረቀ ይገኛል ብለዋል።

በቀጣይም የትምህርት አድማሱን በማስፋት ለመስራት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የገለፁት አቶ ጨነቁ ከዞኑና ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ለኮሌጁ ህንጻ ግንባታ 1ሺ 700 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ማግኘቱን ገልጸዋል።

የኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ዲን አቶ ወንድሙ አለማየሁ በበኩላቸው የኮሌጁን ያለፉት አራት አመታት የስራ እንቅስቃሴ ሪፖርት ለታዳሚው አቅርበዋል።

የዕለቱ በትምህርታቸው የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎችም ከዕለቱ የክብር እንግዶች እጅ የምስክር ወረቀትና ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።

በመድረኩ የክልል ፣ የዞንና የሚዛን አማን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ማጠቃለያም በጋራ ብሔራዊ መዝሙር መዘመርና በጋራ ፎቶ በመነሳት ተጠናቋል።

***********እንኳን ደስ አላችሁ ************ኃላስ ኮሌጅ በመማር ማስተማር ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እየተመራ  ሙሉ ዕውቅና ባገኘንባቸው በቢዝነስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች...
26/10/2024

***********እንኳን ደስ አላችሁ ************
ኃላስ ኮሌጅ በመማር ማስተማር ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እየተመራ ሙሉ ዕውቅና ባገኘንባቸው በቢዝነስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች በቴክኒክና ሙያ እና በአጫጭር ስልጣና በቤንች ኖን እና በሸኮ ኖጉ ያስተማራቸውን ተማሪዎችን በደማቅ ሁኔታ በቀን 17/02/2017 ያስመርቃል ።

በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ።
ኃላስ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ

******በምዝገባ ላይ ነን!!
16/10/2024

******በምዝገባ ላይ ነን!!

09/10/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Tsalafo Chaka Chame, Olani Sutuma, Tesfaye Kebede, Tariku Tamirat, Daniel Markos, Tamerat Alemayehu Adello Kocha, Tekle Gizaw, Mohamed Amin, Solomon M Goberasha, Buzabe Demelash Baynki

የኃላስ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ  ኮሌጅ  ለሴት ተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል  ሰጠ።ኃላስ ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የሴቶች የሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሁሉም የባለድርሻ...
03/10/2024

የኃላስ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ ለሴት ተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል ሰጠ።

ኃላስ ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የሴቶች የሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሁሉም የባለድርሻ አካላት ኃላፊነት መሆኑን በማመን ለቤንች ሸኮ ዞን ሴት ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም ነጻ የትምህርትና እድል መሰጠቱን አሰታወቀ ።በቀጣይ ጥቅት ቀናት የመጀመሪያ ዙር ተማሪዎችን ለማስመረቅ ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን እየገለጽን በቀጣይ ጥቂት ቀናት ለአዲስ ተማሪዎች ትምህርት እንደሚጀመር አሰታወቀ ።

*********ኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በምዝገባ ላይ ይገኛል *******ኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ በቋንቋ ዘርፍ በእ...
02/10/2024

*********ኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በምዝገባ ላይ ይገኛል *******

ኃላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ በቋንቋ ዘርፍ በእንግሊዝኛ ከ5ኛ - 12ኛ ክፍል እንዲሁም በስራ ላይ ላሉ እንደየደረጃቸው ለየብቻ ለማሰልጠን ምዝገባ ላይ ይገኛል። በቤንችኛና በሸኮኛ ትምህርት ላጠናቀቁ በስራ ላይ ላሉና ለመማር ፍላጎቱ ላላቸው አስተምሮ ሰርተፍኬት ይሰጣል። አሁኑኑ ይመዝገቡ ልጆቾን የቋንቋ ባለቤት ያድርጉ።ኃላስ በቴክኒክና ሙያ በተለያዩ የትምህርት አይነቶችም ምርጥ በሆኑ ዩኒቨርስቲ መምህራኖች የእውቀት ባለቤት ያደርጎታል።

እንግሊዝኛ ላይ እንዴት ኖት? ቤንችኛና ሸኮኛስ መናገር ብቻ ወይስ መንበብና መፃፍ ይችላሉ እንግዲያውስ ወደ ሀላስ ይምጡ ጥቂት ጊዜ ሰጥተው በርካታ እውቀት ይሸምቱ።
05/08/2021

እንግሊዝኛ ላይ እንዴት ኖት? ቤንችኛና ሸኮኛስ መናገር ብቻ ወይስ መንበብና መፃፍ ይችላሉ እንግዲያውስ ወደ ሀላስ ይምጡ ጥቂት ጊዜ ሰጥተው በርካታ እውቀት ይሸምቱ።

ለመማር ለመወቅና ለመስራት ለምትፈልጉ ሁሉ ወደ ኃላስ ኮሌጅ ይምጡ በአጭር ጊዜ ምርጥ የእንግሊዘኛ ተናጋሪና የአካባቢ ቋንቋ ጸሀፊ ይሆናሉ። እርሶም ልጆቾም ይመዝገቡ!
30/07/2021

ለመማር ለመወቅና ለመስራት ለምትፈልጉ ሁሉ ወደ ኃላስ ኮሌጅ ይምጡ በአጭር ጊዜ ምርጥ የእንግሊዘኛ ተናጋሪና የአካባቢ ቋንቋ ጸሀፊ ይሆናሉ። እርሶም ልጆቾም ይመዝገቡ!

15/05/2021

ከ5ኛ _ 12ኛ ላሉ ተማሪዎች እንዲሁም በስራ ላይ ላሉ አካላት በሙሉ በምርጥ እና ልምድ ባላቸው መምህራኖቻችን(በላንጉጅ ስኩል) የእንግሊዘኛ፣ ቤንቸኛ፣ ሸኮኛ፣ ግእዝ እና ሌሎች የውጪ ቋንቋዎች ለማስተማር በምዝገባ ላይ ነን እርሶም ይምጡ ልጆቾንም ይላኩ ሀላስ ኮሌጅ ሚዛን ጀሚቲ ህንፃ

ሀላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ በቋንቋ ዘርፍ በእንግሊዝኛ ከ5ኛ - 12ኛ ክፍል እንዲሁም በስራ ላይ ላሉ እንደየደረጃቸው ለየብቻ ለማሰልጠን ምዝገባ ላይ ይገኛል። በቤንችኛና በሸኮኛ ትምህርት...
05/05/2021

ሀላስ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ በቋንቋ ዘርፍ በእንግሊዝኛ ከ5ኛ - 12ኛ ክፍል እንዲሁም በስራ ላይ ላሉ እንደየደረጃቸው ለየብቻ ለማሰልጠን ምዝገባ ላይ ይገኛል። በቤንችኛና በሸኮኛ ትምህርት ላጠናቀቁ በስራ ላይ ላሉና ለመማር ፍላጎቱ ላላቸው አስተምሮ ሰርተፍኬት ይሰጣል። አሁኑኑ ይመዝገቡ ልጆቾን የቋንቋ ባለቤት ያድርጉ
ሀላስ በቴክኒክና ሙያ በተለያዩ የትምህርት አይነቶችም ምርጥ በሆኑ ዩኒቨርስቲ መምህራኖች የእውቀት ባለቤት ያደርጎታል። ሀላስ የደቡብ ምእራብ ኮከብ

Address

Jemiti Building 4th Floor
Mizan Teferi

Telephone

+251917150809

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halas Technology and Business College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category