Logical Educational service PLC

Logical Educational service PLC this is official page of logical business and technology college

ሎጂካል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 210 ተማሪዎች እሁድ ያስመርቃል።ሎጂካል ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 210 ተማሪዎች መጪው እሁድ ሚያዚያ 25 ቀን 20...
01/05/2026

ሎጂካል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 210 ተማሪዎች እሁድ ያስመርቃል።

ሎጂካል ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 210 ተማሪዎች መጪው እሁድ ሚያዚያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሚዛን አማን ከተማ እንደሚያስመርቅ አስታውቋል።

ኮሌጁ በዚህ የምረቃ መርሃ ግብር በአካውንቲንግ፣ በማናጅመንት፣ በአግሪካልቸራል ኢኮኖሚክስ እና በማርኬቲንግ ማናጅመንት የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች የሚያስመርቅ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል 5ቱ ተማሪዎች በኢኮኖሚ አቅም ማነስ ምክንያት ትምህርታቸውን መከታተል ያልቻሉና በኮሌጁ ሙሉ የነፃ ትምህርት ዕድል ተጠቃሚ የነበሩ ናቸው።

የኮሌጁ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መሰረት አስፋው እንደገለፁት፤ ኮሌጁ ትውልድን በዕውቀት የማነፅ ስራውን ከማህበራዊ ኃላፊነት ጋር በማጣመር ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በተለይም አቅም ደካሞችንና የኢኮኖሚ ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት በማምጣት የነገ ብሩህ ተስፋቸውን እንዲያሳኩ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተሰራበት መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው አብራርተዋል።

አቶ መሰረት አክለውም እንደገለፁት፤ ሎጂካል ኮሌጅ ከኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን እውቅና ባገኘባቸው በ5 የዲግሪ እና በ2 የዲፕሎማ የትምህርት ዘርፎች ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ስልጠና እየሰጠ የሚገኝ ተቋም መሆኑንም አብራርተዋል።

ኮሌጁ በትምህርት ስራ ላይ ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከ2,000 በላይ ብቁና በዕውቀት የሰለጠኑ ተማሪዎችን አስመርቆ ለሀገርና ለክልሉ ብሎም ለአከባቢው ልማት ማበርከት እየቻለ መሆኑንም አመላክተዋል።

ኮሌጁ እስካሁን ባደረገው የማህበረሰብ ተጠቃሚነት እንቅስቃሴ 37 ተማሪዎች በኮሌጁ ሙሉ የነፃ የትምህርት ዕድል አግኝተው ትምህርታቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

ተቋሙ እነዚህን ተማሪዎች በነፃ አስተምሮ ከማስመረቅ ባለፈ ህይወታቸውን እንዲመሩና ራሳቸውን እንዲችሉ የስራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው በማድረግ ረገድ የበኩሉን ከፍተኛ ድርሻ ተወጥቷል።

Logical college moving forward
23/03/2025

Logical college moving forward

Logical college moving forward
07/03/2025

Logical college moving forward

ኮሌጃችን አካል ጉዳተኛ ለሆኑት እና በተለያዩ ትምህርት ቤቶች እገዛ ተምረዉ ትምህርታቸዉን ላጠናቀቁ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት እድል በመስጠት ማህበራዊ ሀላፊነቱን እስካሁን ካደረገዉ በላይ አሁንም አካል ጉዳተኛ ለሆኑ ተማሪዎች የትምህርት እድል በመስጠት እገዛ ያደረጋል
የኮሌጃችን ዋና ስራ አስፈፃሚ እና መስራች
አቶ መሠረት አስፋዉ

11/12/2024

ሁሌ ምዝገባ አለ ሁሌ ትምህርት አለ !
ሎጂካል ኮሌጅ ይለያል !

20/11/2024
31/03/2021

የኮቪድ-19 ቫይረስ ስርጭት አሳሳቢ በሆነ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ሕብረተሰቡ፡-
⨳የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ
⨳ ሰዎች በሚበዙበት፣
⨳በቂ አየር ዝውውር በሌለበት፣
⨳ርቀትዎን መጠበቅ በማይችሉበት ቦታ አስገዳጅ ካልሆነ በቀር እንዳይገኙ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጥሪውን ያቀርባል፡፡

25/03/2021

Address

Merkb Building
Mizan Teferi

Telephone

+251936521342

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Logical Educational service PLC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Logical Educational service PLC:

Shortcuts

Share

Category