Mebre Habesha

Mebre Habesha ውድPlease like, share ancoment on this page

01/10/2020

✟✟✟በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ኣሜን።✟✟✟
ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የድንግል ማርያም የአስራት ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች እንደምን ሰነበታችሁ?ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋራ ዘወትር ፀንቶ ይኑር። እንኳን ለእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግሸን ደብረ ከርቤ ዓመታዊ በዓል በሰላም ኣደረሳችሁ። ስለዛሬው ትምህርት ከፈለጉ በቴሌግራም ቻባላችን t.me/ ወይም Mebre Habesha ብላችሁ በመፈለግ በስፋት መመልከት ትችላላችሁ። መልካም በዓል 👉❤❤❤🇪🇹❤❤❤🙏🙏🙏

እንኳን ኣደረሳችሁ የደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ መስቀል በዓል ኣከባበር ለማየት ማስፈንጠርያውን(ሊንኩን) ይጫኑ።👇👇👇👇👇👇👇👇👇
29/09/2020

እንኳን ኣደረሳችሁ የደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ መስቀል በዓል ኣከባበር ለማየት ማስፈንጠርያውን(ሊንኩን) ይጫኑ።👇👇👇👇👇👇👇👇👇

አንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም ኣደረሳችሁ MEBA HD ምርጫችሁ ይሁን ቴክኖሎጂ ይማሩበታል ቴለግራም ቻናላችን t.me/ ብለው ያገኙናል

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም ኣደረሳችሁ መልካም የመስቀል በኣል።
27/09/2020

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም ኣደረሳችሁ መልካም የመስቀል በኣል።

12/09/2020

ክፍል ስድስት
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
50) ከሦስት ቀንም በኋላ ቅዱሳን አባቶች መነኰሳት አባ እንጦንስ አባ መቃርስ አባ ሲኖዳ አባ ብሶይ አባ ጳኩሚስ ወደርሱ መጥተው እንዲህ አሉት ወንድማችን ውደእኛ ና ከኛ ጋርም ፍጹም ተድላ ደስታ ካለበት በእግዚአብሔር መንግስት ደስ ይበልህ ይህንን ሲሉት ነፍሱ ከስጋው ወጣች። መላእክትም በዓለም ውስጥ በገድል በትሩፋት የደከመ ለዘላለሙ በህይወት ይኖራል እያሉ በክብር በምስጋና ወደ እየሩሳሌም ሰአያዊት አወጡት።
51) ከዚህም በኋላ ጳጳሳት ኤጲስቆጶሳት ሁሉም ካህናት ተሰብስበው ገነዙት በቤተ ክርስትያንም ውስጥ ቀበሩት ከመቃብሩም ቁጥር የሌላቸው ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
ሼር ላይክ በማድረግ ለወገንዎ ያጋሩ።
ይህ በእንደዚህ ሁነታ ማለትም በተቆራረጠ ጽሑፍ የሚቀርብበት ምክንያት ፌስቡክ የፅሑፍ መጠን ስለሚያግድ ነው። ስለዚህ ይህን ችግር ለመፍታት ተብሎ የቴለግራም ቻናል ከፍተናል ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
👉👉👉

12/09/2020

ክፍል አምስት
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
ይህ ካልሆነ ግን ራሳችሁን በሰይፍ ልቆርጥ ምያለሁ።
40) የተላኩ ወታደሮችም ፈልገው በጭንቅ አገኙትና ለብጹእ አባ ሚልኪ የንጉሱን መልእክት ልጁን ጋኔን እንደ አደረባት የምትናገረውንም ነገር ነገሩት። እርሱም እኔ ሽማግሌ ሰው ነኝ ወደ ሮም አገር ለመሔድ አልችልም አላቸው። እነርሱም አባታችን ሆይ አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድክ ንጉስ በሰይፍ ቆርጦ እንደሚገድለን ነግሮናል አሉት ሰምቶም እጅግ አዘነ እንዲህም አላቸው ልጆቼ ሂዱ እኛ እርስበርሳችን በሮም ከተማ መግብያ እንገናኛለን።
41) ቃሉንም ሰምተው ሔዱ በዓመቱም ፍጻሜ ከሮሜ ከተማ መግብያ መድረሳቸውን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ያን ጊዜም ደመና ተሸክማ ከሮሜ ከተማ መግብያ አደረሰችው። የንጉስ መልእክተኞችም በአዩት ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው። ለንጉሡም የከበረ አባ ሚልኪ መምጣቱን ነገሩት። እርሱም ወጥቶ በክብር ተቀብሎ ወደ እልፍኙ አስገባው ስለልጁ ስለደዌዋ ነገረው ቅዱስ አባ ሚልኪም አምጧት ብሎ አዘዘ። በአመጧትም ጊዜ ጋኔኑ ጥሎ አረፋ አስደፈቃት ሞተች ብለው እስከሚጠራጠሩ። ያን ጊዜም አባ ሚልኪ ተነስቶ ጸለየ በቅፊቱዳ ላይም ውኃን ረጨ ዘይትንም ቀባት ሰይጣንንም ከርሷ ይወጣ ዘንድ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዘዘው። ያን ጊዜም በጥቁር ባርያ አምሳል ከእርሷ ወጣ።
42) ቅዱስ አባ ሚልኪን ሰይጣንን በስውር ይዞ በቤት ውስጥ ዘጋበት በዚያም አሠረው።
43) ንጉሱም ይህን ድንቅ ስራ አይቶ ከእግሩ በታች ሰገደ እገዳሙ ለሚያስፈልገው ነገር እንዲሆነው ብሎ ብዙ ወቅና ብርን አመጣለት እርሱም መቀበልን እምቢ አለ። ንጉሡም አባቴ ሆይ ከዚህ ተቀመጥ እኔም ገዳም እሠራልሃለሁ አለው። አባ ሚልኪም ልጆቸን መተው አይሆንልኝም አለው ግን በሽተኞችን እየፈወሰ በሮሜ ከተማ ጥቂት ቀኖች ተቀመጠ።
44) ወደ አገሩ ይመለስ ዘንድ ተነስቶ በወጣ ጊዜ ንጉሡም ከመኳንንቱ ጋራ ሊሸኘው ተነሳ። ከንጉሥ ግቢ በስተውጭ የንጉስ ፈረሶች የሚጠጡበት ታላቅ የደንጊያ ገንዳ የተበሳ ታላቅ የሆነ ደንግያን አባ ሚልኪ አይቶ ንጉሡን ይህን ገንዳ ይህንንም የተበሳ ታላቅ ደንግያ ለገዳም አገልግሎት እሻዋለሁና ስጠኝ አለው። ንጉሱን አስራ አራት ሰዎች ከፍ ለማድረግ የማይቻላቸው ወደ ገዳምህ እንዴት ይደርሳልተሸክሞ ወደፈለከው ቢታ የሚያደርስ ሃይል ካለህ እኔ ሰጠሁህ አለው።
45) ያን ጊዜም ቅዱስ አባ ሚልኪ ሰይጣንን ከአሰረበት ቦታ አምጥቶ ያንን የተበሳ ደንግያ በአንገቱ ውስጥ አንጠለጠለ ገንዳውንም ተሸክሞ ከፊት ከፊቱ ተገልጦ እንዲጓዝ አዘዘው።ሰይጣንም እነዝያን ገንዳዎች የተበሳውንም ደንግያ ተሸክሞ በፊት በፊቱ ይጓዝ ጀመረ። ንጉሱና የተሰበሰቡት ህዝብ አይተው እጅግ አደነቁ ለሚፈሩት ለሚያመልኩት ይህን ጸጋ የሚሰጥ ምስጉን እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
46) የከበረ አባ ሚልኪም እነዝያን ደንግያዎች ሰይጣንን አሸክሞ ወደ ገዳሙ አደረሰው በገዳሙም ደጃፍ አጠገብ እንዲአስቀምጣቸው አዘዘው እስከዛረም በዚያ ይኖራሉ።
47) ሰይጣንንም ዳግመኛ መጥቶ እንዳይፈትነው በዓለት ዋሻ ውስጥ ዘግቶ በመስቀል ምልክት ለዘላለሙ አሸገው
48) አባ ሚልኪም ከመነኰሰ አርባ አምስት ዓመታት ሲሆነው እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ ወደርሱ መጣ እነሆ የምታርፍብትን ቀን ቀቧል ከሦስት ቀን በቀር አልቀረህም ወደ ዘላለምም ተድላ ደስታ ትሔዳለህ።
49) ያን ጊዜም ልጆቹን ሁሉ ጠርቶ ሰይጣን ከሚያመጣው ስሕተት እንዲርቁና እንዲጠበቁ በፍርሃትም ሁነው እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ አዘዛቸው።
50) ከሦስት ቀንም በኋላ ቅዱሳን አባቶች መነኰሳት አባ እንጦንስ አባ መቃርስ አባ ሲኖዳ

12/09/2020

ክፍል አራት
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም

ይህም አባ አውጊን ብዙ ትሩፋትን የሚሰራ ጻድቅ ሰው ነው በእርሱም ሥር የተመረጡ ሰባ ሁለት መነኰሳት ነዋሪዎች አሉ። አባ ሚልኪም ከእግሩ በታች ሰግዶ አባቴ ሆይ በጥላህ ሥር እንድሆን የምንኲስናንም ልብስ ታለብሰኝ ዘንድ እሻለሁ አለው። አባ አውጊንም ከወዴት ወገን ነህ ብሎ ጠየቀው እርሱ አባ ሚልኪም
አገሩ ቊልዝም ለአባ አውጊንም የእህቱ ልጅ ምእሆኑ ነገረው ሰምቶም ፈጽሞ ደስ አለው።
29) ሦስት አመትም በአመክሮ አቆየው ከዚህም በኋላ የምንኲስናን ልብስ አለበሰው ዜናው በፋርስ አገር እስቲሰማ ትጋትንና ተጋድሎን አበዛ።
30) እግዚአብሔርም የመፈወስን ሀብት ስጥቶት አጋንንትን ከሰዎች ላይ አስወጥቶ ይሰዳቸዋል።
31) ከዕለታትም በአንዲቱ ዕለት የዳዊትን መዝሙር እያነበበ ብቻውን ሲጓዝ ታላቅ ጒድጓድ ወዳለበት ደረሰ በአጠገቡም የበለስ ዛፍ አለ ብዙ እረኞችም በዚያ ያለቅሱ ነበር። አባ ሚልኪም ምን ያስለቅሳችኋል አላቸው። እረኞችም እንዲህ ብለው መለሱለት የአገረ ገዢው ልግ ከእኛ ጋራ ከበለስ ፍሬ ሲበላ ታላቅ ዘንዶ ወጥቶ ልጁን ውጦ ወደ ጒድጓድ ተመለሰ አሉት። እረኞችም እየነገሩት ሳለ የህጻኑ አባት ልብሱን በመቅደድ ፊቱን
በመጽፋት ከብዙ ሰዎች ጋር መጣ ቅዱስ ሚልኪንም ስለ ልጁ ማለደው። አባ ሚልኪም ልጄ ሆይ በእግዚአብሔር ታመን እንጂ አትፍራ የጌትነቱንም ድንቅ ስራ ታያለህ አለው።
32) ያን ጊዜም ፊቱን ወደ ምስራቅ መልሶ ረጅም ጸሎትን ጸለየ ጸሎቱንም በጨረሰ ጊዜ ዘንዶውን ጠርቶ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሕጻኑን ይተፋው ዘንድ አዘዘው ምንም ሕማም ሳይነካው ጉዳትም ከቶ ሳያገኘው ወድያውኑ ተፋው በከይሲውም አድሮ ያለ ሰይጣን እንዲህ ብሎ ጮኸ የቊልዝም ሰው ሚልኪ ከአንተ የተነሳ ወዴት ልሒድ ይህንን ብሎ እንደ ጢስ ተበተነ።
33) የህጻኑም አባት ይህንን ድንቅ ስራ ልጁም እንደ ዳነ በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለው። ለቅዱስ አባ ሚልኪም ብዙ ወርቅና ብር አመጣ አባ ሚልኪም መቀበልን አይሆንም አለ ግን በጽድቅ ስራ አንድ እንድንሆን ገዳምን ስራ አለው። አገረ ገዢው የሕጻኑ አባትም ደስ አለው ሦስት መቶ የመነኰሳት ቤቶችን ሠራ ዙርያዉንም በግንብ አጠረ መዝግያዎችንም ከብረት ሰራ።
34) ቤተ ክርስትያንም ሲሰሩ ሦስት መቶ ሰዎች ሊአንቀሳቅሷት የማይችሉ ለማእዘን የምትሆን ደንግያን አገኙ በጻድቁ በአባ ሚልኪ ጸሎትም ራስዋ ተነስታ እንደሚፈልጉዋት ሁና ተሰራች።
35) ከዚህም በኋላ በዚያ ገዳም ሦስት መቶ ሰዎች ተሰብስበው የተመረጡ መነኰሳትን ሆኑ። የቅዱስ አባ ሚልኪም ዜና በሃገሩ ሁሉ ተሰምቶ በየዓይነቱ ደዌ ያለባቸውን በክፉዎች አጋንንትም የተያዙትን ወደርሱ የሚያመጧቸው ሆኑ ሁሉም በጸሎቱ ይፈወሱ ነበር።
36) በዚህ ጻድቅ ጸሎትና ምልጃ የፋርስ ሰዎች ተጠብቀው የሚኖሩ ሆኑ።
37) ከዚህ በኋላ አባ ሚልኪ ከዋሻ ውስጥ ገብቶ የዋሻውን በር ዘጋ በልቡም እስከ ዕድሜዬ ፍጻሜ ከዚህ ዋሻ አልወጣም ብሎ ቃል ገባ።
38) የበጎ ስራ ጠላት ሰይጣንም እንዲህ ብሎ ዛተበት ጠብቀኝ እኔ ከዚህ ከበዓትህ አስወጥቸ የተሳልከውን ቃል አፈርሳለሁ ይህንንም ብሎ ሒዶ በሮም ንጉሥ ላይ አድሮ አሳበዳት እርሷም እየጮኸች እንዲህ አለች ከቊልዝማዊው ሚልኪ በቀር የሚያድንኝ የለም።
39) ንጉሥ አባቷም ሰምቶ ከወታደሮቹ ውስጥ አራት መቶ ሰዎችን ላከ እንዲህም ብሎ አዘዛቸው በኍ ቦታ ተገኝታችሁ አባ ሚልኪን ፈልጋችሁ ወደ እኔ አምጡት እኔም በጎ የሆነ ዋጋችሁን እከፍላችኋለሁ።

12/09/2020

ክፍለ ሦሥት
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም

14) በዚችም ቀን ዳግመኛ የታላቂቱ አገር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ አባ ሚልዮስ አረፈ እርሱም ለአባታችን ሐዋርይዳንዳ ወቅንጌላዊ ለሆነ ማርቆስ ሦስተኛ ነው።
15) ይህም አባት የሮሜ ንጉሥ አስባስያኖስ በነገሠ በዐስራ አምስት ዓመት ተሾመ ይኸውም የክብር ባለቤት ጌታችን በዓረገ በአርባ ዓመት ነው ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው በሹመቱም ዐስራ ሁለት ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም በፍቅር አንድነት አረፈ።
16) ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

17) በዚችም ቀን ዳግመኛየቊልዝም ሰው የሆነ ፍጹም ጻድቅ አባ ሚልኪ አረፈ።
18) የዚህም ጻድቅ ወላጆች ከቊልዝም አገር ከታላላቆች ወገን ናቸው።እርሷም ከላይኛው ግብጽ አውራጃ ውጽጥ ናት እነርሱም በብርና በወርቅ የበለጸጉ ናቸው። ለድሆችና ለችግረኞች ምጽዋትን የሚሰጡ እግዚአብሔርንም እጅግ የሚወዱ ናቸው።
19) ነገር ግን ልጅ አልነበራቸውም ከዕለታት ባንዲቱ ከምምህር ዘንድ የሚማሩ ልጆችን አዩ በእጃቸውም ሰሌዳዎችን ይዘዋል። በሰሌዳዎቹም ውስጥ እንዲህ የሚል ጽሑፍ አለ፡ እኛ የሕያው እግዚአብሔር ልጆችእንድንሆን በሕይወታቸው ሳሉ ያስተማሩን አባቶቻችንን አስባቸው አቤቱ ነሶቻቸውንም ከተመረጡቅዷን ጻድቃንና ሰማእት ጋር አሳርፍ።
20) የአባ ሚልኪ አባትም ከልጆች አንደበት ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ከዚህ አለም ከሔድኩ በኋላ ልጅ የሌለኝ እኔን ማን ያስበኛል ወዮልኝን እያለ እጅግ በማዘን ተከዘ።
21) ከዚህም በኋላ በጾም በጸሎት ምጽዋትንም በመስጠት ከሚስቱ ጋር ምህላ ያዘ። የክብር ባለቤት እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ ወንድና ሴት ሁለት ልጆችን በአንዲት ጊዜ ሰጣቸው በእነርሱም ፈጽሞ ደስ አላቸው።
22) ወደ ክርስትናም በአስገቧቸው ጊዜ ወንዱን ልጅ ሚልኪ አሉት እህቱን ስፍና አሏት ትርጓሜአ ርግብ ማለት ነው በመልካም አስተዳደግ አሳደጓቸው።
23) ለሚልኪ ሰባት ዓመት ሲሆነው አባቱ ወስዶ ለመምህር ሰጠው የብሉያትና የሐዲሳት መጻሕፍትን ሁሉ ተማረ መንፈስ ቅዱስም አደረበት። ከህጻናቱም ጋር አይጫወትም አይስቅም በቀንም በሌሊትም አዘውትሮ መጻሕፍትን ያነባል እንጂ።
24) ዕድሜውም አስራ ዘጠኝ ዓመት በሆነው ጊዜ ወላጆቹ ጠርተው ስለጋብቻ ሚስት አግብቶ መታሰብያቸው ይሆን ዘንድ ተናገሩት። እርሱም ይህን አክወደደም ነገር ግን በተንኮል እሺ ቃላችሁን ተቀብዬ ያዘዛችሁኝ ሁሉ ደርጋለሁ አላቸው እርሱ ግን ከዓለም ሸሽቶ ያመልጥ ዘንድ ያስባል።
25) ከዚህም በኋላ አባቱን እንዲህ አለው አባቴ ሆይ ከእኔ ጋራ ለተማሩ ልጆች ለባልንጀሮቸም ምሳ ላደርግላቸው እሻለሁ ምሳንም ለባልንጀሮቹ ያዘጋጅላቸው ዘንድ አባቱ አንድ ሺህ የወርቅ ዲናር ሰጠው። ዳግመኛም የሚያስፈልገው ስራ እንዲያገለግሉ ወንዶችና ሴቶች አገልጋዮችን አዘዘለት።
26) ክዚህም በኋላ በፈረስ ተቀምጦ ከአባቱ ፊት ወጣ ሎሌዎቹንም እንዲህ አላቸው መቶ የወርቅ ዲናር ወስዳችሁ በፍጥነት ምሳ አዘጋጁልኝ ልጆች ባልንጀሮቼን እኔ ብቻዬ ሒጄ እጠራቸዋለሁ። ዘመዶቹም ሰምተው ተመለሱ እርሱም ብቻውን ሒዶ ያንን ወርቅ ለድሆችና ለሚስኪኖች በተነ ፈረሱንም ለአንድ ድኃ ሰጠ በላዩ ካለ ልብስ በቀር ምንም ምን አላስቀረም።
27) መምጣቱም በዘገየ ጊዜ ፈለጉ ግን አላገኙትም። እያለቀሱም ተመልሰው ለአባቱና ለእናቱ ነገሯቸው። እነርሱም የመረረ ልቅሶን አለቀሱ ከልቅሶ ብዛትም የተናሳ የእናቱ ዐይኖቿ ታወሩ ለሞትም አደረሳት።
28) ይህ አባ ሚልኪ ግን ጡር ወድ ምትባል ገዳም ሔደ ይቺም አባ አውጊን ለሚባል ለእናቱ ገዳሙ ናት።

12/09/2020

ስንክሳር ዘወርሃ መስከረም
ክፍል ሁለት
የአገረ ገዥውም ልጅ በሞተ ጊዜ ከሞት አስነሳው የሀገር ሰዎችም ሁሉ አመኑ እግዚአብሔርንም ወደ ማወቅ ተመለሱ።
7) ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በርበር ወደሚባል አገር ሂዶ ያስተምር ዘንድ ሐዋርያ በርተሎሜዎስን ኣዘዘው እንዲረዳውም ሐዋርያ እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ ጋር ላከለት። የዚያች አገር ሰዎች ግን እጅግ የከፉ ስለሆኑ በፊታቸው ድንቆች ተአምራቶችን እያደረጉላቸው ሐዋርያትን አልተቀበሏቸውም።
8) ጌታችንም ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ በሚያዙት ሁሉ ተዛዛቸውን እንደይተላለፍ አዘዘው።ሐዋርያትም ወደዚአች አገር ሁለተኛ ይዘውት ይዘውት ገቡ የሓገር ሰዎችም ሓዋርያትን ይበሏቸው ዘንድ ነጣቂዎች የሆኑ አራዊትን አወጡ። ያን ጊዜም ያ ገጸ ከልብ በአራዊቱ ላይ ተነስቶ እየነጠቀ በላቸው ይህንንም ገጸ ከልብ ከመፍራት የተነሳ ሰዎች በድንጋጤ የሞቱ ብዙዎች ናቸው።
9) የሀገር ሰዎችም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ከሐዋርያትም እግር በታች ሰገዱየሚሏቸውን የሚያደርጉ ታዛዦች ሆኑ። ሐዋርያትም ቤተክርስትያን ሰርተውላቸው ካህናትንም ሹመውላቸው ከእነርሱ ዘንድ ወጥተወግዚአብሔርን እያመእገኑ ሔዱ።
10) ሐዋርያ በርተሎሜዎስም እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎች ወደሚኖሩት በባሕር ዳርቻ ወዳሉ አገሮች ሕኤዶ የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከላቸው በፊታቸውም ተአምራትን አደረገ ሁሉም የጌታችን በሆነች በቀናች ሃይማኖት አመኑ።
11) ሐዋርያ በርተሎሜዎስም ከዝሙት ርቀው ንጹሐን እንዲሆኑ ሰዎችን የሚያዝዝ ሆነ።
12) ንጉስ አግሪጳም ስለርሱ በሰማ ጊዜ በከበረ ሐዋርያ በርተሎሜዎስ ላይ እጅግ ተቆጣ። በማቅ ከረጢት ውስጥ እንዲአደርጉትና አሸዋ ሞልተው ከባሕር እንዲጥሉት አዘዘ። እንዲሁም ይህን አደረጉበት ምስክርነቱንና ተጋድሎውንም በዚች ዕለት ፈጸመ።
13) ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን በሐዋርያ በርተሎሜዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
👉👉 ሼር 👍ላይክ እያደረጋችሁ ኣስተያየታችሁን ኮሜንት ላይ ኣስቀምጡ።

12/09/2020

እንኳን ከ ዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም ኣሸጋገረን። መልካም ኣዲስ ዓመት🌻🌻🌻2013🌻🌻🌻

ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
ክፍል 1(አንድ)
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የእግዚአብሔርን ረድኤት አጋዥ በማድረግ በበጎ ስጦታውም ትርጓሜው የተሰበሰበ ማለት ነው፡፡ ይህንኑ የስንክሳር መጽሐፍን ለመጻፍ እንጀምራለን፡፡ የኸውም የከበሩ አባቶቻችን የቤተ ክርስትያን መምህራን የአትሪብና የመሊግ ኤጵስቆጶስ ክቡር አባት አባ ሚካኤልና የሃገረ ቡርልስ የከበረ አባት አባ ዮሃንስ
እንዲሁም ሃይማኖታቸው የቀና ሌሎች አባቶች ከቅዱሳን ሰማእታት ከጻድቃን ከነብያት ከሐዋርያት ከሊቃነ ጳጳሳት ከኤጲስቆጶሳት ከመነኮሳትም ሁሉ ከገዳማውያን ከገድሎቻቸው ከመላእክት አለቆችም ከድርሳናቸው የሰበሰቡትና ያቀነባበሩት አምላክን የወለደች እመቤታችን የከበረች ድንግል ማርያም ከአደረገቻቸው ድንቆች ተአምራቶችም የክብር ባለቤት የሆነ የመድሃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የበዓላቶቹን መታሰብያ በዘመናት ሁሉ ከመስከረም መባቻ እስከ አመቱ ፍጻሜ ሁልጊዜ መመናን እንዲያነቡት እንዲሰሙትም:: ይህንን መጽሐፍ ያቀነባበሩት በሽህ ሦስት መቶ ንጹሐን በሆኑ ሰማእታት ዘመን ነው:: የእሊህ የተባረኩ አባቶቻችን ጸሎታቸውና በረከታቸው ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን::
የተባረከ የመስከረም ወር የግብጽና የ ኢዮጵያ ዓመታት ወሮች ርእስ ነው። የቀኑ ሰዓትም የተስተካከለ ዓእስራ ሁለት ሰዓት ነው። ከዚህ በኋላ ያነሰ ይሄዳል።አሁንም በፍጹም ንጽህና ታላቅ በዓልን አድርገን ልናከብር ይገባናል። ይህች ዕለት ከሌሎች ዕለታት ተለይታ የተባረከች ናትና ከክፉ ሥራዎችም ሁሉ ተለይተን እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝባቸውን አዳዲስ የሆኑ
በጎ ስራዎችን እንስራ። ሐዋርያ ጳውሎስ እነሆ የቀደሙት ሥራዎች አልፈው ሁሉ በክርስቶስ ሐዲስ ሆነ እንዳለ። ይህም ከእግዚአብሔር ዘንድ እንዲሁ የጎላየ ተረዳ ሆነ እርሱም በክርስቶስ ልጅነትን በመስተት ይቅርታውንና ቸርነቱን አደለን። ኢሳይያስም እንዲህ አለ። በኔ ህልውና ያለ ያዋሐደኝ ህይወቴ መንፈስ ቅዱስ ስለርሱ ድኆችን በልብ ያዘኑ ሰዎችን ደስ አሰኛቸው
ዘንድ ለተማረኩም ሰዎች ነጻ መውጣትን አስተምራቸው ዘንድ እውሮችም ያዩ ዘንድ እግዚአብሔር የወሰነውን ዘመን የተመረጠ እለው ዘንድ ፍዳ የሚደረግባትንም ቀን ደግ እላት ዘንድ ያዘኑትንም ሰዎች ደስ አሰኛቸው ዘንድ ላከኝ። ነቢይ ዳዊትም ዳግመኛ እንዲህ አለ። የምህረትህንም ዓመት እህል ትትባርካለህ። ምድረ በዳዎችም ከበረከትህ ጠሎችን ይጠግባሉ ልምላሜዎችን ያገኛሉ።

1) በዚችም ዕለት እዮብ በፈሳሽ ውሃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ተፈወሰ።
2) ይህም ለሰዎች ልማዳቸው ሁኖ ዓመቱ ዙሮ ሲመጣ ፈሳሹ ውኃም በመላ ጊዜ በአዲስ ውሃ ይጠመቃሉ በእርሱም ይባረካሉ።
3) የጻድቁ እዮብ በረከትም ከኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

4) ዳግመኛም በዚች እን ከዓእስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሐዋርያ በርተሎሜዎስ ምስክር ሁኖ አረፈ።
5) ለዚህም ሐዋርያ ሒዶ ያስተምር ዘንድ እልዋህ በሚባል አገር ዕጣው ወጣ። እርሱም ከጰጥሮስ ጋር በአንድነት ሄደ የክብር ባለቤት በሆነ ገታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተማሩ ልባቸውንም የሚያስደነግጥ ድንቆች ተአምራትን በፊታቸው ከአደረጉ በኋላ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ መለሳቸው።
6) ከዚህም በኋላ ወደ ከተማው ውስጥ ገብቶ ያተምር ዘንድ ምክንያት አደረገ ቅዱስ ጴጥሮስም እንደ ባርያ ሸጠው። ባለ ጽጋ ለሆነ መኰንንም በወይን አትክልት ውስጥ የሚያገለግል ሆነ ድንቅ ታምርን በማድረግ የተቆረጡ የወይን ቅርንጫፎች በሰራተኞች እጅ ላይ ሳሉ አፈሩ።

ውድ የመብሬ ሐበሻ ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሳኤ በሰላም ኣደረሳችሁ!!!
22/08/2020

ውድ የመብሬ ሐበሻ ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሳኤ በሰላም ኣደረሳችሁ!!!

የላሊበላ የፀሐይ ግርዶሽ 14/10/2012 ዓ.ም
21/06/2020

የላሊበላ የፀሐይ ግርዶሽ 14/10/2012 ዓ.ም

በኣላማጣ የፀሐይ ግርዶሽ ሰኔ 14/10/2012 ዓ.ም
21/06/2020

በኣላማጣ የፀሐይ ግርዶሽ ሰኔ 14/10/2012 ዓ.ም

Address

Maych'ew

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mebre Habesha posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Mebre Habesha:

Shortcuts

Share