03/02/2020
በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ት/ሥ/ቢሮ የሠልጣኝ፣ አሰልጣኝ፣ አመራር ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሮክቶሬት አዲስ ወደ አመራርነት ለመጡ ዋናና ምክትል ዲኖች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠቱ ተገለፀ፡፡
=================================
በቢሮው የሠልጣኝ፣ አሰልጣኝ፣ አመራር ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሮክቶሬት እንዳስታወቀው አዲስ ወደ አመራርነት ለመጡ ከ70 ለሚበልጡ
የኮሌጅ ዋናና ምክትል ዲኖች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በቡታጅራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጥር ግቢ ለተከታታይ 5 ቀናት መስጠቱ ተገለፀ፡፡ በተያያዘም ሥልጠናው በዋናነት አዲስ ወደ ቴ/ሙያ አመራሪነት የመጡ ዲኖችና ምክትል ዲኖች የቴ/ሙ/ት/ሥ/ ዘርፉን በብቃት፣ በዕውቀት እና በክህሎት እንድመሩ 15 ያህል የሥልጠና ሞጁል ተዘጋጅቶ መሰጠቱ የተገለፀ ስሆን ሁሉም ወደዬ ኮሌጆቻቸው ስመለሱ ለኮሌጁ ማህበረሰብ በማውረድ በስትራቴጅው መሠረት ከመምራትም ባሻገር የሥርዓቱን ዘላቅነት ለማረጋገጥ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባቸዋል ተብሏል፡፡ ቢሮው ያዘጋጀውን ሥልጠና ካሰለጠኑት አሠልጣኞች መካከል አቶ አረጋ ታመነ
ከወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሪጂስትራል አስተባባሪ በበኩላቸው ቢሮው ዋና ዲኖችንና ምክትል ዲኖችን በጋራ ከማሰልጠንም በተጨማሪ ሴት አሠልጣኞችን
ወደ አመራርነት እንድመጡ አድርጎ በርካታ ሴቶች እንድሳተፉ ማድረጉ ሥልጠናውን ለየት እንደሚያደርግ ገልፀው የሥልጠናው ዋና ዓላማም አመራሮች በሰው ሀይል፣ በፋይናንስና ንብረት አስተዳደር፣ በሥርዓተ ትምህርትና ቲቲኤልኤም አዘገጃጀትና አተገባበር፣ በIDP & DAC አዘገጃጀት፣ በካይዘን አተገባበር ወዘተ በአጠቃላይ በቴ/ሙ/ት/ሥ/ስትራቴጂ ላይ የጠራ
አመለካከትና ግንዛቤ በመያዝ ኮሌጆችን በብቃት፣ በዕውቀትና በክህሎት ለመምራት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ከስልጠና ተሳታፊዎች መካከል ወ/ሪት ሰርካለም እሸቱ በሣውላ ፖሊ ቴክኒክ
ኮሌጅ የሠልጣኝ፣ አሰልጣኝ፣ አመራር ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ አስተባባሪ እና ምክትል ዲን የሆኑት በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት አብዛኞቻቸው በሠልጣኝና አሠልጣኝነት በሥርዓቱ ውስጥ አልፈው የመጡ ብሆኑም እንደዚህ ዓይነት ሥልጠና በመሪነት ሚናቸው ላይ ግንዛቤ በመፍጠርና አቅምን በማሳደግ የሚፈጥረው አወንታዊ ተጽዕኖ የጎላ መሆኑን ገልፀው
ለውጤታማነትም የሚችሉትን ሁሉ ለማድረግ መነሳሳታቸውን አስታውቀው ሥልጠናው በስኬት መጠናቀቁን የቢሮው ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮ ዳይሬክቶሬት ዘግቧል፡፡