14/04/2024
የንባብ ባህልን ለማጎልበት በትናንትናው ዕለት የተከፈተው የመፅሐፍት አውደ ርዕይ በኦፔኖ ህፃናት አካዳሚ በተለያዩ መርሃግብሮች እንደቀጠለ ነው።
በዛሬው ዕለትም የተማሪዎች የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል።
ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ሚያዝያ 06/2016 ዓ.ም)
በኦፔኖ ህፃናት አካዳሚ አዘጋጅነት "ፍኖተ ንባብ" በሚል መሪ ቃል በትናንትናው ዕለት የተከፈተውን የመፅሐፍት አውደ ርዕይ ምክንያት በማድረግ የተማሪዎች የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል። '
በውድድሩ ላይ የኦፔኖ ህፃናት አካዳሚ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ውድድሩ መነሻውን መቱ ማዞሪያ አድርጎ በኦፔኖ ህፃናት አካዳሚ ውስጥ ተጠናቋል።
የሩጫ ውድድሩ ተማሪዎች በስፖርት ጤናቸውን እንዲጠብቁና በአካልና በአዕምሮ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያስተምር እንደሆነ ተገልጿል።
ከዚህ ባሻገር በተማሪዎች መካከል ያለውን መቀራረብና የእርስ በእርስ ግንኙነት እንዲዳብርም ውድድሩ የራሱን አስተዋጽዖ ያበረክታል ተብሏል።
በወንዶች ውድድር ሙይ ኡባንግ፣ ቸደጆክ አቺዲና ናትናኤል ተፈራ እንዲሁም በሴቶች መስታወት አሸናፊ፣ መሰረት መልካሙና ፀደይ ገላይ ከአንድ እስከ ሶስት በመውጣት ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
በኬጂ ተማሪዎች ውድድር ፋሩቅ ሲሳይ፣ ናታን ተስፋዬና ምትኩ ዮናስ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
በዚህ ውድድር ከአንድ እስከ አምስት ለወጡ ተማሪዎች የመፅሐፍ ሽልማት ተበርክቷል።