17/08/2026
የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአረጋዊያንና አቅመ ደካሞች የምገባ ፕሮግራም አካሄደ፣
🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬🧬
(ነሀሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም)
የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 በጀት አመት የክረምት እቅዶች ውስጥ አንዱ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ መሳተፍ ነው።
ለዚህም በአጣዬ ከተማ አልማ አካባቢ ለሚገኙ ከ53 በላይ ለሚሆኑ አረጋዊያን የኮሌጁ ዲን አቶ እንድሪስ ሰይድ እና ም/ዲኖች አቶ አረጋኸኝ ጌታቸው፣ ወ/ሮ ባንችአምላክ አዳነ እና ባለሙያዎች በቦታው በመገኘት #የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አድርጓል።
ከማዕድ ማጋራቱ በተጨማሪ #በኮሌጁ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር እሸቱ አባተ አሰልጣኝነት የተመረተ 26 ሊትር ፈሳሽ ሳሙና ድጋፍ አድርጓል። እንደ አቶ እንድሪስ ሰይድ ገለፃ አረጋዊያንን መደገፍ በጎ ተግባር በመሆኑ ግለሰብ እንዲሁም ተቋም ተጠናክሮ መያዝ ያለበት ተግባር መሆኑን ገልፀዋል።
መረጃው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ነው