Al-Ikhlas Academy አል-ኢልኽላስ አካዳሚ مدرسة الإخلاص

  • Home
  • Ethiopia
  • Dire Dawa
  • Al-Ikhlas Academy አል-ኢልኽላስ አካዳሚ مدرسة الإخلاص

Al-Ikhlas Academy አል-ኢልኽላስ አካዳሚ مدرسة الإخلاص Islamic School -
for abetter knowledge

12/09/2022

ለማሳሰብ

አል—ኢኽላስ አካዳሚ የ2015 የትምህርት ዘመን ዛሬ መስከረም 02 ጅማሬ አድርጓል። በዚህ ሳምንት በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ብቻ ትምህርት ይኖረናል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ መደበኛ ትምህርት በጠዋትም በከሰአትም ይጀምራል፣ ይህን በመገንዘብ ወላጆች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ልጆቻችሁን እንድትልኩ እናሳሰወባለን።
ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም!

ምዝገባ ጀምረናል አል-ኢኽላስ አካዳሚ መሰረታዊ የዲን ትምህርቶችን በማከል በአካደሚው ዘርፍ ደግሞ የተሻለ ዕውቀት የሚቀሰምበት ተቋም ነው!!ያሉን ክፍት ቦታዋች ጥቂት ስለሆኑ በጊዜ ልጆን ያስ...
04/08/2022

ምዝገባ ጀምረናል
አል-ኢኽላስ አካዳሚ መሰረታዊ የዲን ትምህርቶችን በማከል በአካደሚው ዘርፍ ደግሞ የተሻለ ዕውቀት የሚቀሰምበት ተቋም ነው!!
ያሉን ክፍት ቦታዋች ጥቂት ስለሆኑ በጊዜ ልጆን ያስመዝግቡ

አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚንፕሮግራሙ ጣፋጭወላጆችን አፍ ሚያስከፍት ሳቢ እና ማራኪ ነበርበጣም ደስ ብሎናል እናመሰግናለን
03/07/2022

አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን

ፕሮግራሙ ጣፋጭ
ወላጆችን አፍ ሚያስከፍት ሳቢ እና ማራኪ
ነበር
በጣም ደስ ብሎናል እናመሰግናለን

congratulationAl-ikhlas academy ለሶስት አመታት በቅድመ መደበኛ ሲያስተምራቸው የቆየውን ተማሪዎች ለማስመረቅ ሽር ጉድ ላይ
03/07/2022

congratulation

Al-ikhlas academy
ለሶስት አመታት በቅድመ መደበኛ ሲያስተምራቸው የቆየውን ተማሪዎች ለማስመረቅ ሽር ጉድ ላይ

ተማሪዎችን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ በየቀኑ እና በተግባር የተደገፈ ካልሆነ ፍሬው እምብዛም አመርቂ አይሆንም።
18/01/2022

ተማሪዎችን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ በየቀኑ እና በተግባር የተደገፈ ካልሆነ ፍሬው እምብዛም አመርቂ አይሆንም።

13/11/2021

በዘንድሮ የትምህርት አመት ከሌሎች አመታት በበለጠ የወላጆች ተሳትፎ ጨምሯል። ጥቂት የማይባሉ ወላጆች አሉ የሚሏቸውን ሀሳቦችና መሻሻል የሚገባቸውን አሰራሮች በግንባር በመቅረብ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ሆኖም መሻሻሎች ይኖሩ እንጂ በሚፈለገው ደረጃ ግን አልደረሰም።

በመሆኑም የተማሪ ወላጆች በተመቻቸው ጊዜና ሁኔታ ወደ ትምህርት ቤታችን ቅጥር ግቢ በአካል በመምጣት፣ ለት/ት ቤቱ አስተዳደር ባሉበት ሆነው በስልክ፣ ወይም ከስራ ሰአት ውጪ ለቦርድ አባላት በአካል ያለቸውን ሀሳብ በማካፈል ላይ መበርታት ይኖርቧቸዋል።

በተባበረና በተናበበ መልኩ ከወላጆች ጋር የሚኖረን የሀሳብ ልውውጥ ለትምህርት ቤታችን እድገት ትልቁን ሚና ይጫወታል።

24/10/2021

መልካም ትውልድ ለመቅረፅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ትምህርት ቤታችን ተሳታፊ በመሆኑ እጅጉኑ ደስታ ይሰማናል።
መልካም ትውልድ ለመቅረፅ የመንግስት፣ የትምህርት ቤት አስተዳደር፣ የመምህራንና የወላጆች የጋራ ጥረት ይጠይቃል።

በድሬዳዋ ገቢዎች ባለስልጣን የጤና ቡድን አስተባባሪነት በተዘጋጀው አንድእሽግ ለአንድ ልጅ/one pack for one child/ በሚለው ንቅናቄ ላይትምህርት ቤታችን/አል-ኢኽላስ አካዳሚ/ የበ...
26/09/2021

በድሬዳዋ ገቢዎች ባለስልጣን የጤና ቡድን አስተባባሪነት በተዘጋጀው አንድ
እሽግ ለአንድ ልጅ/one pack for one child/ በሚለው ንቅናቄ ላይ
ትምህርት ቤታችን/አል-ኢኽላስ አካዳሚ/ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከቱ ከድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አብድሰላም ሙሀመድ የተፈረመ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶናል።
በጥቅሉ 12 ቦርሳ፣ 12 ደርዘን እስክሪፕቶ፣ 24 ደርዘን እርሳስ፣ ሁለት ፓኬት ላፒስ፣ አንድ ፓኬት መቅረጫ ግምቱ 10 ሺ ብር የሚሆን ድጋፍ አድርገናል።
ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም‼

19/09/2021

በመልካሙ ተጠናቋል‼
ዛሬ እሁድ መስከረም 9/2014 ከተማሪ ወላጆች ጋር የነበረን ስብሰባ በመልካሙ ተጠናቋል። በዚህ ስብሰባ በዋነኝነት ለ2014 የትምህርት ዘመን የተደረጉ ቁሳዊና የሰው ዝግጅቶች ለወላጆች ሪፓርት ቀርቧል። የ2014 የትምህርት አጀማመርን በተመለከተ ገለፃ ተደርጓል። በዋነኝነት የዩኒፎርም አለባበበስ፣ የመግቢያና መውጫ ሰአትና የአመጋገብ ሁኔታ በዝርዝር ተቀምጧል።
በተጨማሪም የወላጆች ሚና ምን መምሰል እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጧል።
በመጨረሻም የወላጆች ሀሳብ ተቀብለን ማብራሪያ በመስጠትና ገንቢ ሀሳቦችን በመክተብ የወላጅ ኮሚቴ በመምረጥ ስብሰባው ተጠናቋል።
ከ1—4 ኛ ክፍል ላሉ ልጆች ትምህርት ነገ ሰኞ 10/2014 ይጀምራል።
ጥራት ያለው ትመወህርት ለሁሉም‼

19/09/2021

ለውድ ወላጆች‼
የ2014 የትምህርት አጀማመር በተመለከተ ዛሬ እሁድ ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ነምበርዋን በሚገኘው አዲሱ ቅርንጫፍ ስብሰባ እንዳለን ይታወቃል።
ስለሆነም የተማሪ ወላጆች በዚህ ወሳኝና የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት በምንይዝበት ስብሰባ በተባለው ሰአት እንዲገኙ ለማሳሰብ እንወዳለን።
ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም‼

14/09/2021

ለ2014 የትምህርት ዘመን ለመዋለ ህፃናት ትላንት ሰኞ መስከረም ሶስት ትምህርት ጀምረናል።
ይህ ሳምንት ማለትም ከሰኞ መስከረም 03 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ መስከረም 08 ድረስ በጠዋቱ ክፈለ ጊዜ ብቻ ትምህርት ይኖራል።
መስከረም 10 መደበኛ ትምህርት በሙሉ ቀን ፕሮግራም ይሰጣል።
ስለመረጡን እናመሰግናለን‼
ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም‼

Address

Behind Ashewa Bilal Mesjid
Dire Dawa

Telephone

+251910701250

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al-Ikhlas Academy አል-ኢልኽላስ አካዳሚ مدرسة الإخلاص posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Al-Ikhlas Academy አል-ኢልኽላስ አካዳሚ مدرسة الإخلاص:

Shortcuts

Share

Category