11/12/2025
በዲላ ከተማ ት/ት መመሪያ በዳዊት ክላስተር ስር የሚገኙ ፋሬስ: ትንሳኤና ቅ/ሚካኤል አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች በጋራ በመሆን ለመምህራኖቻቸው በአዲሱ ስረዓተ ትምህርት አተገባበር፡ ፈተና ዝግጅትና በዕለታዊ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ለሁለት ቀን የሚቆይ ስልጠና ዛሬ በቀን 02/04/2018 ዓ.ም ጀምረዋል፡፡ ስልጠናው በዞን ባለሙያ እተሰጠ ያለ ሲሆን በመክፈቻ መረሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የዲላ ከተማ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ የተከበሩ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፋ ሲሆኑ በንግግራቸው መንግስት በአሁኑ ሰዓት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ሁሉን አቀፍ ርብርብ እያደረገ ያለ መሆኑን ገልፀው የዲላ ከተማም በተለይ ባለፉት ሁለትና ሶስት ዓመታት በክልላዊና በሀገራዊ ፈተናዎች የ6ኛ የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤት በየዓመቱ አንፃራዊ ለውጥ እያሳየ በመሆኑ ለውጡን ለማስቀጠል ለመምህራን የሚሰጡ ስልጠናዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸው መ/ራንም ሙያቸውን በማክበር ህዝብና ሀገሪቷ የሰጠቻቸውን ትውልድ የማነፅ ተልዕኮ በሀላፊነት እንዲወጡ ጥሪያቸውን አሰተላልፈዋል፡፡
28/11/2025
28/11/2025