የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት

የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት

Share

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሃገረ-ስብከት በደሴ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት የደሴ መዝገበ-ምሕረት ሰ/ት/ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ነው

10/03/2026



የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በርዕሰ አድባራት ታዕካ ነገሥት አትሮንሰ ማርያም ቤተክርስቲያን በደረሰ አደጋ 4 አገልጋይ ካህናትና 1 አገልጋይ መነኩሴ እናት መገደላቸውንና በ26 ምእመናን ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

በአገልጋዮች ላይ በደረሰው ጉዳትም የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል።

ለዓለም ሰላም ለምእመናን ደህንነት ዘወትር መሥዋተ እግዚአብሔርን በሚያቀርቡና በሚጸልዩ ካህናት፣ አምልኮተ እግዚአብሔርን በሚፈጽሙ መነኮሳትና ምእመናን ላይ እንዲህ ዓይነት አደጋ መከሰቱ እጅግ በጣም አሳዛኝ ድርጊት ነው ብሏል።

መነኮሳቱ፣ ካህናቱና ምእመናኑ እየተራቡና እየተጠሙ ታሪክና ቅርስን ጠብቀው ለትውልድ ያሻገሩ የአባቶቻቸውን አደራ የተወጡ መሆናቸውን ሀገረ ስብከቱ በመግለጫው ጠቅሷል።

እንዲህ ዓይነት አደጋ የሚያደርሱ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

Photos from የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት's post 08/03/2026

"ተንሥዕ ንሣዕ ዓራተከ ወሑር፤ ተነስተህ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ"《ዮሐ.5፡8》

የዐቢይ ፆም አራተኛው ሳምንት መጻጉዕ ይባላል፡፡በዚህ ዕለትም የደሴ መዝገበ ምሕረት ሰ/ት/ቤት በየዓመቱ የተለመደውን ተግባሩን በደሴ ሪፈራል ሆስፒታል በመገኘት ህሙማንን ጠይቋል የደሴ መዝገበ ምሕረት ቅ/ድ/ማርያም እና ቅ/ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን መዝገበ ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት በየአመቱ ካህናትን ፣ የአብነት ተማሪዎችን ፣ መቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ፣ የህግ ታራሚዎችን፣አቅመ ደካሞችን እንደተለመደው ዘንድሮም ስለሚያስፈስክ የተለመደ መንፈሳዊ ተግባርዎን እንዲያደርጉልን ስንል በእመቤታችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በአካል መደገፍ ላልቻላችሁ 1000362595642 የደሴ መዝገበ ምሕረት ሰ/ት/ቤት ድጋፍዎን ማድረግ ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ 0930320328 / 0925019942 ይደውሉ

04/03/2026

"ከመዝኑ መሪር እንከ ውእቱ ሞት"
በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?1ኛ ሳሙ115÷32
😥😥😥😥😥😥😥😥😥😥😥😥
የደሴ መንበረ ጸሀይ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አባል እና የደብሩ ዋና ፀኃፊ በነበሩት ቀሲስ ኃይሉ ጌታሁን ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለመላው የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አባላት እና ቤተሰቦች እግዚአብሔር አምላካችን መጽናናት ይሰጥልን ዘንድ እንመኛለን🙏

የደሴ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ ምሕረት ሰ/ት/ቤት
የካቲት 25/06/2018ዓ.ም

27/02/2026

አንዱ ወደ አንድ አባት ቀረብ ብሎ "ድንግል ማርያም እኮ እንደ እኛ ሰው ናት" አላቸው። እርሳቸውም "ልክ ነህ እርስዋ በተፈጥሮዋ ሰው ናት ፣ አንተ ግን ሰው ነህ?" አሉት።

ነገሩ ስድብ ይመስላል ፣ አስተውሎ ላየው ግን ሰው ነኝ ለማለትም መሥፈርት እንዳለው ያስታውሳል። "ኤልያስ እንደ እኛ ሰው ነበረ" ነገር ግን ዝናምን በጸሎቱ ያቆመ መሆኑን ስንሰማ ሰው ነን ለማለት እንፈራለን። ንጉሥ ዳዊት ለልጁ ሰሎሞን "ሰው ሁን" ያለው ሰው መሆን ማለት እንደ ሰው ክብርን አውቆ መኖር ስለሆነ ነው። ክቡር ሆኖ ሳለ ካላወቀና በኃጢአቱ ከጸና እንደሚጠፉ እንስሳት ይመስላል።

ሰው ለመሆን ብዙ መሥፈርቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ተቀምጠዋል ፣ የድንግል ማርያምን እናትነት መቀበልም ሰው የመሆን ምልክት ነው።
"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል" ተብሎ እንደተጻፈ "ጽዮን እናታችን" ማለት ያልቻለ ምኑ ሰው ይባላል?

"የእግዚአብሔር ከተማ ጽዮን ሆይ ይሉሻል የናቁሽ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ" ተብሎ ለዳዊት ከተማ ተነግሮላት ነበር። ስንት ኃጢአተኛ ሲራኮትባት ለሚውልባት ለዳዊት ከተማ የሚሰገድ ከሆነ ለንጽሕቲቱ ከተማው ለድንግል ማርያም አይሰገድም እንዴት ይባላል? ነቢዩ ከጽዮን ጫማ በታች ይሰግዳሉ ብሎ ለዳዊት ከተማ ከተናገረ ከድንግሊቱ ጫማ በታች እንዴት ይሰገድ ይሆን?

በእርግጥ የናቅዋት ሁሉ ወደ ጫማዋ ሊሰግዱ ይሆን? በፍጹም አይሆንም! የድንግልን ጫማዋንማ ለእኛ ለምናከብራትም ማን ባደለን? እኛ አክሱም ጽዮን ቁስቋም ግሸን በረከቷን ሽተን እየተጓዝን የናቋት እንዴት ጫማዋን ያገኛሉ?

አባ ጊዮርጊስ "ገሊላዊትዋ ድንግል ጫማን እሸከም ዘንድ ፣ ጥላዋ ያረፈበትን እስም ዘንድ ማን ባደለኝ?" ይል የለምን? ከእግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ ማለት ይዋረዳሉ ነው እንጂ ይህ ክብር ለናቋት የሚገባ አይደለም።

"ጽዮንን ክበቧት በዙሪያዋም ተመላለሱ" (መዝ 48:12)

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ❤️

30/01/2026

እናመሠግናለን

28/01/2026

ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ”
"ሞት ለማንኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡"
ቅዱስ ያሬድ
++++++++++++++++++++++++++++++++

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ እረፍት አደረሳችሁ። የእናታችን፣ የእመቤታችን፣ የአዛኝቷ የአማላጅቷ ረድኤትና በረከት አይለየን።

ምልጃዋን አምነን ለምንማጸናት፣ የምሕረት ዐይኗን አታዙርብን። ሀገራችን ሰላም ሆና በመከራ ያሉ ወገኖቻችን ሐሴት ያደርጉ ዘንድ ቅድስናዋ ይርዳን።🙏

26/01/2026

ሼር🙏🙏🙏

በዓለ አስተርዮን በደሴ መዝገበ ምሕረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን አይቀርም🙏

Photos from የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት's post 20/01/2026

በዓለ ጥምቀትን እንዲህ ባመረ መልኩ አከበርን እግዚአብሔር ይመስገን🙏

Photos from የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት's post 18/01/2026

ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባህሩ እየተንቀሳቀሱ ይገኛል

መልካም በዓል🙏

Photos from የደሴ መዝገበ-ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መዝገበ—ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት's post 17/01/2026

እንኳን አደረሳችሁ

ጥምቀትን ከደሴ መዝገበ-ምሕረት ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በጋራ እናክብር🙏🙏

22/12/2025

✍️​ሩፋኤል✍️
​ስሙ 'እግዚአብሔር ይፈውሳል' ማለት ነው
​የቅዱስ ሩፋኤል ስም ከሁለት የዕብራይስጥ ቃላት የተዋቀረ ነው። (ሩፋ)ማለት 'ፈውስ' ሲሆን 'ኤል' ማለት ደግሞ 'እግዚአብሔር' ማለት ነው።
ስለዚህም 'እግዚአብሔር ይፈውሳል' ማለት ነው። ይህ ስሙ ታሪኩን በሙሉ ከጦቢት መጽሐፍ ጋር አገናኝቶት እና ለመጀመሪያ ጊዜ ለጦቢያ ይፋ ሲያደርግለት እንዲህ ብሏል:
​“እኔም ስሜ ሩፋኤል ነው፤ ከሰባቱ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነኝ፤ እግዚአብሔር የላከኝ እኔ ነኝ።” (ጦቢት 12÷15)

✍️ የፈውስ መልአክ ነው
​ቅዱስ ሩፋኤል የፈውስ መልአክ በመባል ይታወቃል። በጦቢት መጽሐፍ ውስጥ፣ ዓይነ ስውር የነበረውን አዛውንት ጦቢትን ዓይኑን በዓሣ ሐሞት ፈውሶታል። ይህም የፈውስ ተልዕኮው ዋና አካል መሆኑን ያሳያል።
​“ዓይኑንም በመክፈት፣ ጦቢት በዓይኑ እንዲመለከት አደረገው።” (ጦቢት 11÷13)

​✍️የመንገድ መሪና ተጓዦችን ጠባቂ ነው
​ጦቢያን ከእጁ በጉዞው ከደጀን እስከ ሜዶናውያን አገር ድረስ በጥሩ ሁኔታ እና በሰላም ይመራዋል። ይህ ጉዞ ጦቢያ እና በዚያ ቦታ የነበረችው የሣራ ልጅን እንዲያገባ አድርጎታል። ሩፋኤል የጦቢያ መሪ ብቻ ሳይሆን ጠባቂም ነበር።

​“ጉዞውም በመጀመር፣ የጦቢያ ወላጆቹንና እኔን ከእርሱ ጋር፣ ወደ ሜዶናውያን አገር ሄድን።” (ጦቢት 5÷12)

✍️ከትዳር በፊት ስለሚመጣ ችግር መከላከል የሚችል መልአክ ነው
​ቅዱስ ሩፋኤል ሰባት ባሎቿን የገደለው ጋኔን አስወግዶ የሣራን መከራ አቃልሎላት ነበር። ጋብቻዋ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም ረድቷል፣ ይህ ደግሞ በራሷ ፈቃደኝነት እና በክብረ በዓል ላይ የተመሠረተ ነበር።
​“ወደ ውኃው ገብቶ ጋኔኑንም አስወግዶ ከሰውየው አወጣው።” (ጦቢት 8÷3)

​✍️ ሚስጥር የሚጠብቅ መልአክ ነው
​ቅዱስ ሩፋኤል ታሪኩን እና ማንነቱን ለጦቢያ እና ለጦቢት ከመግለጹ በፊት፣ ሙሉ በሙሉ ሚስጥር ጠባቂ ነበር።
​“ሩፋኤልም በምላሹ፣ ‘አስደናቂ እና ሚስጥር ያለው ነገር ነው፤ አንተና ቤተሰብህ ማንም ሌላ ሰው እንዳያውቀው ለእናንተ የተፈጠረ ነው።’” (ጦቢት 12÷11)

✍️የጸሎት መልስና የጾም ምላሽ መልአክ ነው
​የጦቢት እና የሣራ ጸሎት መልስ ሆኖ ሩፋኤል ወደ ምድር ተልኳል። ይህ የሚያሳየው እግዚአብሔር ለልጆቹ ጸሎት ምላሽ ለመስጠት ቅዱሳን መላእክትን እንደሚልክ ነው።
​“አንተም ወደ ቤተ መቅደስ እንድትሄድ፣ የጸሎትህን ምላሽ በሩፋኤል በኩል ትቀበላለህ።” (ጦቢት 3÷25)

✍️ደስታን የሚመልስ መልአክ ነው
​ሩፋኤል የጦቢት ዓይነ ስውርነትን በመፈወስ እና ለጦቢያ የሚስት ፍለጋ በማገዝ ለቤተሰቡ ደስታን አምጥቷል።
​“በዚያን ቀን፣ የደስታ ቀን ነበር።” (ጦቢት 11÷15)

✍️የንጽሕናን መልአክ ነው
​ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢትን እና ሣራ ከጋብቻ በፊት በንጽሕና እንዲኖሩ አሳስቧል። ይህ የጋብቻ ትርጉምን እና የእግዚአብሔርን ስጦታ መሆኑን ያጎላል።
​“በእነዚያ ቀናት፣ ጦቢያና ሣራ በንጽሕና ከእግዚአብሔር ጋር እንዲኖሩና እንዲኖሩባቸው ነበር።” (ጦቢት 6÷18)

​✍️እግዚአብሔርን የሚያመሰግን መልአክ ነው
​በጦቢት መጽሐፍ መጨረሻ ላይ፣ ሩፋኤል የሰው ልጆች እግዚአብሔርን እንዲያመሰግኑ አሳስቧል። ይህ የጸሎት እና የምስጋና አስፈላጊነትን ያጎላል።
​“እግዚአብሔርንም አመስግኑ፤ በጎ ነገርንም አድርጉ፤ የእግዚአብሔርን መልካምነትና ምሕረትን አትዘንጉ።” (ጦቢት 12÷6)

መልካም በዓል🙏🙏

Want your school to be the top-listed School/college in Dessie?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Dessie