25/11/2025
መንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 ስር የተዘረዘሩ የሚያስቀጡ ስህተቶች እነ የቅጣት ደረጃዎች ከስር ተቀምጧል።
የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ በአሽከርካሪዎች የሚፈጸሙ ጥፋቶችን በመዘርዘር ያስቀመጠ ሲሆን ለጥፋቶቹም ደረጃዎችን አስቀምጧል፡፡
ቀላል የሆኑ ጥፋቶች ማለትም እንደ ተሽከርካሪን ያለአግባብ መጎተት፣ ሄልሜት ሳያደርጉ ብስክሌት መንዳት፣ የተሟላ የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ ኪትና የእሳት ማጥፊያ ሳይኖር የንግድ ተሽከርካሪ ማሽከርከር፣ የሚበኑ ወይም የሚበተኑ ነገሮችን ጭኖ ያለአግባብ ማሽከርከር፣ በትራፊክ መብራ ወይም መስቀለኛ መንገድ ላይ በልመና ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ መስጠት፣ ከ13 አመት በታች የሆነን ህፃን ከአሽከርካሪው ጎን በሚገኘው አስቀምጦ ማሽከርከር የመሳሰሉ ጥፋቶች ሲሆኑ ለዚህም ጥፋት ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ለጥፋቱ1 ነጥብ ተመዝግቦበት እስከ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት ተደንግጓል፡፡
በደረጃ ሁለት ላይ ተቀመጡ ጥፋቶች በመካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ጥፋቶች ሲሆኑ እነሱም የተሟላ የጭነት ማቀፊያ /እስፖንድ/ ሳይኖር ጭነት ጭኖ ማሽከርከር፣ ጥሩንባ ያለአግባብ መጠቀም፣ በመንገድ ላይ ተሽከርካሪ ማጠብና ማሳጠብ፣ በተከለከለ ስፍራና ሁኔታ ተሽከርካሪን ማቆም፣ ከመጠን በላይ የሆነ ድምጽ እያሰሙ ወይም በጆሮ ማዳመጫ እያዳመጡ ማሽከርከር፣ በእግረኛ ላይ ውሃ መርጨት፤ ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል የመሳሰሉ ጥፋቶች ሲሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ለጥፋቱ 2 ነጥብ ተመዝግቦበት እስከ 1,000 ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል፡፡
ሌላው በሶስተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ጥፋቶች ከባድ ጥፋቶች ሲሆኑ ይህም የጉዞ ረድፍን ወይም መስመርን ሳይጠብቁ ማሽከርከር፤ ከተሽከርካሪው የመጫን አቅም በላይ ትርፍ ሰው መጫን፣ ተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገሩ ወይም መልእክት እየተጻጻፉ ወይም እያነበቡ ማሽከርከር፣ በጭነት ተሽከርካሪ በህግ ከተፈቀደው ውጪ ሰውን መጫን፣ የደህንት ቀበቶ ሳያስሩ ወይም ተሳፋሪዎች ማሰራቸውን ሳያረጋጋግጡ ማሽከርከር፣ ቀይ የትራፊክ መብራት መጣስ፣ በተከለከለ መንገድ ወይ አቅጣጫ ማሽከርከር፣ ጫት እየቃሙ ወይም አደንዛጅ እጽ ወስዶ ማሽከርከር የመሳሰሉ ጥፋቶች ሲሆኑ ለዚህም ጥፋት ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ለጥፋቱ 3 ነጥብ ተመዝግቦበት እስከ 1,500 ብር የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት በደንቡ ላይ ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን አሽከርካሪው ለሁለተኛ ጊዜ እና ከዛ በላይ ያጠፋ እንደሆነ የቅጣት ነጥቦቹ እየተደመሩ የሚጣለውም ቅጣት ከፍ እያለ የሚሄድ ይሆናል፡፡
ሌላው በዚህ ደንብ ላይ ልዩ ደረጃ ያላቸው ጥፋቶችን የተቀመጡ ሲሆኑ እነዚህም ጥፋቶች ተሽከርካሪ በማሽከርከር በሰው ሕይወት፣ አካል እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ፣ የአልኮል መጠጥ ጠጥቶ ማሽከርከር፣ በህግ ከተፈቀደው የፍጥነት መጠን በላይ በፍጥነት ማሽከርከር፣ አፈር፣ አሸዋ ድንጋይና ተመሳሳይ ነገሮችን የሚመለከተው አካል ሳይፈቅድ በተሽከርካሪ ወይም በእግረኛ መንገድ ላይ ማራገፍ፣ ጉዳት አድርሶ በቦታው ያለመቆም ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ሕክምና በመውሰድ እንዲታከም አለማድረግ የመሳሰሉ ጥፋቶችን እንደየ ጥፈቱ ቅለት እና ክብደት መጠን እንዲሁም የጥፋቱ ነጥብ ከ8 እስከ 21 ነጥብ በሚሆንበት ጊዜ ከብር 1,500 አስከ 10,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲሁም ከ6 ወር እስከ 1 አመት ከ6 ወር የሚደረስ እግደን ያካተተ ቅጣትን አካቷል፡፡
ደንቡ ሌሎች የደንብ መተላለፍ ጥፋቶችን አብዛኛውን ግዜ አሽከርካሪ ባልሆኑ ሰዎች የሚፈጸሙ ጥፋቶችን ያካተተ ሲሆን ይህም ከሚመለከተው አካል ፍቃድ ሳያገኙ በእጅ የሚገፋ ጋሪ በመንገድ ላይ መንዳት፣ በመንገድ ላይ እንስሳትን መንዳት፣ በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል መጨመር ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጪ መቀመጫ መጨመር፣ ከሚመለከተው አካል ፍቃድ ሳያገኝ ተሽከርካሪዎችን ወይም እግረኞችን የሚያውክ ቁሳቁስ ወይም ሸቀጥ በእግርኛ ወይም በተሽከርካሪ መንገድ ላይ ማስቀመጥ፣ የንግድ ሥራ መስራት፣ ያለፍቃድ የእግረኛ ወይም የተሽከርካሪ መንግድ መቆፈር፣ የአሽከርካር ብቃት ማረጋገጫ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ማሽከርከር፣ ከፖሊስ በተሽከርካሪው ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የጽሑፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና ማከናወን የመሳሰሉ ጥፋቶችን የሚያካትት ሲሆን እንደየ ጥፋቱ ቅለት እና ክብደት ከብር 100 እስከ ብር 20,000 በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስከጣ ተደንግጓል፡፡
ደንቡ በእግረኞች የሚፈጸሙ ጥፋቶችንም ያካተተ ሲሆን ተገቢ ጥንቃቄ ሳያደርጉ መንገድ ማቆረጥ፣ ለተሽከርከሪ የተፈቀደ መንገድ ላይ ያለበቂ ምክንያት መቆም ወይም መጓዝ፣ እግረኛ መንገድ በሌለበት መንገድ ቀኝ ጠርዝ ይዞ መጓዝ፣ ለእግረኛ መንግድ ተብሎ ከተከለለ መንግድ ውጪ መጓዝ፣ በብረትም ሆነ በግንብ ተለይተው የታጠሩ መንገዶች ዘሎ መንገድ ማቋረጥ፣ በጆሮ ማዳመጫ የተለያዩ ድምጾችን እያዳመጡ ማንገድ ማቋረጥ፣ ለእግረኛ ክልከል ነው የሚል ምልክት ባለበት መንገድ ወይም እግረኛ እንዳያቋርጥ በተከለከለበት የማሳለጫ ወይም የቀለበት መንገድ ማቋረጥ ከብር 100 እስከ በር 150 የሚያስቀጣ ነው፡፡
Via👉ፍትሕ ሚኒስቴር