Tibeb Besu College

Tibeb Besu College Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Tibeb Besu College, Educational consultant, Dangila, Dangila.

እንኳን አደረሳችሁ ጥበብ በእሱ ኮሌጅ"ትምህርት የፈጠራ ውጤት ነው!"ለጥበብ በእሱ ኮሌጅ ተማሪዎች፣ ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬት ሌት ተቀን ለምትተጉ የአስተዳደርና የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች፣ ዕ...
10/04/2026

እንኳን አደረሳችሁ ጥበብ በእሱ ኮሌጅ
"ትምህርት የፈጠራ ውጤት ነው!"
ለጥበብ በእሱ ኮሌጅ ተማሪዎች፣ ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬት ሌት ተቀን ለምትተጉ የአስተዳደርና የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች፣ ዕውቀታችሁን ለምታካፍሉ መምህራን እንዲሁም ሁልጊዜም ከጎናችን ለቆማችሁ ደጋፊዎቻችን በሙሉ፤
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!
የትንሳኤው በዓል ለተቋማችን አዲስ ጥንካሬን፣ ለተማሪዎቻችን ብሩህ ተስፋን፣ ለሠራተኞቻችንና ለመምህራኖቻችን ደግሞ የሥራ መነሳሳትን ይዞ እንዲመጣ እንመኛለን። በዓሉ የፍቅር፣ የሰላምና የደስታ ይሁንላችሁ!
• ለተማሪዎቻችን፦ የትንሳኤው ብርሃን ለትምህርታችሁ ስኬትና ለነገው ብሩህ ተስፋችሁ መሠረት ይሁንላችሁ።
• ለአስተዳደርና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች፦ ተቋማችን ውጤታማ እንዲሆን ለምታደርጉት ያልተቆጠበ ጥረት ምስጋናችን የላቀ ነው። እንኳን አደረሳችሁ።
• ለጥበብ በእሱ ኮሌጅ መምህራን፦ በትውልድ ግንባታ ሂደት ላይ ለምታሳዩት ትጋትና ለምታካፍሉት ዕውቀት ትልቅ አክብሮት አለን።
• ለደጋፊዎቻችን፦ በጉዟችን ሁሉ አጋር ለሆናችሁን ሁሉ በዓሉ የበረከት ይሁንላችሁ።
የትንሳኤው ብርሃን ቤታችሁንና ልባችሁን በደስታ ይሙላው!
ጥበብ በእሱ ኮሌጅ - ዳንግላ

እንኳን ለከተራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!! ጥበብ  በእሱ ኮሌጅ
19/01/2026

እንኳን ለከተራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!

ጥበብ በእሱ ኮሌጅ

10/10/2025
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ!መልካም የደመራና የመስቀል በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለንጥብብ በእሱ ኮሌጅዳንግላ ኢትዮጵያ
26/09/2025

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ!

መልካም የደመራና የመስቀል በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን
ጥብብ በእሱ ኮሌጅ
ዳንግላ ኢትዮጵያ

15/09/2025

ከጥበብ በእሱ ኮሌጅ
ምስጋና
ለዶክተር አማረ አቤ እና ለዶክተር ላመስግናው አቤ ኮሌጁ ለተማሪዎች የትምህርት ጥራትና ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ እንዲሁም ለማህበራዊ አገልግሎት ስታደርጉት ለነበረው ጥናታዊ ፁሁፍ ልባዊ ምስጋና እያቀረበ ለቀጠይ ያቀረቡትን የንድፍ ሀሳብ ገምግሞ አፃድቋል።

15/09/2025

በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተከለከሉ እና የእርምት እርምጃ የሚያስከትሉ ተግባራት
-----------------------------------------------------------------
** ከባለሥልጣኑ ፈቃድ ሳያገኝ ሲያስተምር የተገኘ አዲስ ተቋም፤
** ፈቃድ ባልተገኘበት ካምፓስ ወይም ቅርንጫፍ ትምህርት ሲሰጥ የተገኘ ተቋም፤
**ባልተፈቀደ የትምህርት-መስክ እና መረሀ-ግብር ትምህርት እየሰጠ የተገኘ ተቋም፤
** ፍቃድ ሳያድስ ስያስተምር የተገኘ ተቋም፤
** ከባለሥልጣኑ ፈቃድ ሳያገኝ የህንጻ ለውጥ ያደረገ ተቋም፤
** የአጫጭር ስልጠና እና የማማከር አገልግሎት ፈቃድ ሳይሰጣቸው የሚሰሩ ተቋማት ወይም የሙያ ማህበራት፤
** በባለሥልጣኑ ከተሰጠው የደረጃ ስያሜ ውጪ ሌላ የደረጃ ስያሜ ሲጠቀም የተገኘ ተቋም፣
** አሳሳች ማስታወቂያ ያሰራጨ ተቋም፤
** የከፍተኛ ትምህርት የመግቢያ መስፈርት ያላሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የተገኘ ተቋም፤
** በባለሥልጣኑ ተገምግሞ ያገኘውን ስርዓተ ትምህርት ሳይከተል ትምህርት የሰጠ ተቋም፤
** የመምህራንን ቁጥር እና ደረጃ አጓድሎና ቀይሮ የተገኘ ተቋም፤
** በባለስልጣኑ ከተፈቀደው ቁጥር በላይ መዝግቦ ሲያስተምር የተገኘ ተቋም፤
** የተማሪ መረጃ አያያዝ፣ አጠባበቅና አላላክ፤
ባለሥልጣኑ የተሰጠውን የፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት ደብዳቤ በግልጽ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በሚታይ ሁኔታ ያለጠፈ ወይም ያላሳወቀ ተቋም እና
** ግብአቶችን አጓድሎ ወይም ከተቋም ወደ ሌላ ተቋም ወይም ካምፓስ አዛውሮ የተገኘ ተቋም፤ሐሰተኛ ሰነዶች እና ትክክለኛ ያልሆኑ ማስረጃዎች ትክክለኛ አድርጎ ማቅረብ ናቸው፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ

ውድ የጥበብ በእሱ ኮሌጅ መምህራኖች; አስተዳደር ስራተኞች; እስታፍ ሰራተኞች እና ተማሪዎች እንዲሁም ደንበኞቻችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ !አዲሱ ዓመት የሰላም...
10/09/2025

ውድ የጥበብ በእሱ ኮሌጅ መምህራኖች; አስተዳደር ስራተኞች; እስታፍ ሰራተኞች እና ተማሪዎች እንዲሁም ደንበኞቻችን
እንኳን ለ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ !
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና እና የስኬት እንዲሆንልን እንመኛለን።
ጥብብ በእሱ ኮሌጅ
ስለኮሌጃችን መረጃ ለማግኘት ቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/TBEC122119
መማር የፈጠራ ውበጤት ነው!

ጥበብ በእሱ  ኮሌጅ  በተለያዩ የትምህርት  መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። ዳንግላ ከተማ የሚገኘው ጥብብ በእሱ  ኮሌጅ ለመጀመሪያ - ዙር አስመርቋል።የጥበብ በእሱ ኮሌጅ  ዲን እ...
02/09/2025

ጥበብ በእሱ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ዳንግላ ከተማ የሚገኘው ጥብብ በእሱ ኮሌጅ ለመጀመሪያ - ዙር አስመርቋል።
የጥበብ በእሱ ኮሌጅ ዲን እና ባለሀብት ኢንጂነር እሱባለው አቤ በኢፌዲሪ ትምህረት እና ስልጠና ባለስልጣን በዲግሪ ፕሮግራም እውቅና ባገኘባቸው የትምህርት መስኮች ለአራት ተከታተይ አመታት ሲያስተምራቸው የቆየውን ለመጀመሪያ ዙር ተመራቂ ተማሪዎች ማስመረቁ ልዩ ያደረገዋል።

ኢንጂነር እሱባለው አቤ የበጐ አድራጐት ስራዎች በሚመለከት
ከፍሎ ለመማር የአቅም እጥረት ላለባቸው 5 ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ሰጥቶ 2 ተማሪዎች ተመራቂዎች ሲሆኑ 3ቱ ተማሪዎች ደግሞ በመማር ላይ ይገኛሉ፡፡
ኮሌጁ ከሚሰራቸው ስራዎች በኢፊድሪ ትምህረት እና ስልጠና ባለስልጣን እና በክልሉ በስራ እና ክህሎት ቢሮ ከተሠጡት የኮሌጁ ተልኮዎች ውስጥ የስልጠና አገልግሎት፤ችግር ፈች ጥናትና ምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ኮሌጁ ከሚሰጣቸው የአጫጭር ስልጠናዎች 7 ከፍለው ለመማር የአቅም እጥረት ላለባቸው ሰልጣኞችን በነፃ በማሰልጠን የስራ እድል እንዲፈጥሩ አድርጓል፡፡
እንጂነር እሱባለው እንገለፁት ለተማሪዎች በልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ከተለያዩ መንግስታዊ እና ከግሉ አጋር ድርጆቶች ጋር አብሮ በመስራት ለተማሪዎች ትኩረት በመስጥት ከሰራቸው ስራዎች መካከል ከእናት ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሶስት ተማሪዎች የ3 ወር የትምህርት ክፍያ እስፖንሰር እንደሆኑ እና ኮሌጁ ተማሪዎችን ወደተለያዩ ተቋማት ወይም ባንኮች ለልምምድ ሲወጡ በቂ ህሎት የዘው እንዲዎጡ በማድርግ እና መሰል እስፖንሰሮችን በመፈለግ ተማሪዎች ወደ ገበያ እንዲቀላቀሉ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
የከሌጁ ባለሀብት ኢንጂነር እሱባለው አቤ እንገለፁት ከአስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል ጥሩ ውጤት ለስመዘገቡ ከዲፓርትመንት አንድ አንድ በአጠቃለይ 3 ተማሪዎችን ለ2018 በጀት አመት አወዳድሮ ለመቅጠር የኮሌጁ ሴኔት ወስኖ አፅድቆል።
ኢንጂነር እንዳሉት ለተማራቂ ተማሪዎች አሁን የያዛችሁት ዲግሪ የህይወታችሁ ህይወት ጅማሮ እንጂ ፍፃሜ አለመሆኑን አውቃችሁ የዛሬ ምረቃታችሁ ህይወታችሁን የምትቀይሩበት መሠረት የጣላችሁበት ቀን ነው ሚለውን ገልፀው ።
"ትምህርት" ማለት

በቀላል መልክ የመማር እና እውቀት የማግኘት ሂደት ነው። በዙሪያችን ስላለው አለም መረጃን፣ ክህሎቶችን፣ እሴቶችን እና ግንዛቤን እንዴት እንደምናገኝ ይረዳናል ። ትምህርት ትምህርት ቤቶች እና ክፍሎች ብቻ አይደለም; በሕይወታችን ውስጥ ይከሰታል፣ በምንመራምርበት፣ በጠየቅን ቁጥር፣ መጽሐፍ ባነበብን፣ ወይም ከልምዶቻችን በተማርን ቁጥር ትምህርትን እንቀስማለን።
የትምህርት አስፈላጊነት
ትምህርት በህይወታችን እና በዙሪያችን ባለው አለም ላይ ትልቅ ተጽእኖ አለው። ትምህርት ፈጠራን እና ፈጠራን ያቀጣጥላል, ማህበረሰቡን ወደፊት ይገፋል። በመጨረሻም ኢንጂነር እሱባለው
በትምህርት አለም ትቀየራለች በመማሬ አለምን አየኋት"እንዳሉት ሁሉ እናንተም ነገ አለምን ለማየት መማር ከወዲሁ ይጠበቅባችኋል ።
የኮሌጁ ዲን እና ባለሀብት የሆኑት እሱባለው አቤ እንደገለፁት ኮሌጁ እውቅና ካገኘ ጀምሮ በጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት የተሰማራ መሆኑን ገልጿል።
ኮሌጁም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ተማሪዎች የወርቅ ዋንጫ እና ሜዳሊያ እንዲሁም የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል : ለ3 ተመራማሪዎች የስራ እድልም ተፈጥሮላቸዋል ።

የጥበብ በእሱ ኮሌጅ ቦርድ ስብሳቢ እና የዳንግላ መጀመሪያ  ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል  ዳይሬክተር እንዲሁም የዶ/ር አማረ  መካከለኛ  ክሊኒክ ባለቤት ዶ/ር አማረ አቤ በ2017 ዓ.ም ከአስመረ...
01/09/2025

የጥበብ በእሱ ኮሌጅ ቦርድ ስብሳቢ እና የዳንግላ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር እንዲሁም የዶ/ር አማረ መካከለኛ ክሊኒክ ባለቤት ዶ/ር አማረ አቤ
በ2017 ዓ.ም ከአስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት ለአስመዘገቡ ከዲፓርትመንት አንድ አንድ በአጠቃላይ 3 ሠልጣኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የጥበብ በእሱ ኮሌጅ ሴኔት ማፅደቁን አድንቆ።
እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል::

ለዛሬዋ ቀን ላደረሰን በመጀመሪያ ፈጣሪን እያመሠገንሁ።
ውድ ተመራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሠቦች በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ ብለው ።
ይህን ሁሉ ፈተና እና ውጣ ውርድ አልፍችሁ የመጀመሪያ ዙር ተማሪዎች እና ተመራቂዎች መሆናችሁ ኮሌጁ ልዩ መዝገብ ሰንዶ ለታሪክ ያስቀምጠዋል።
አክለውም ዶክተር አማረ አቤ
ለዚህ ሁሉ ውጤት መሳካት ጠንካራ አስተዳደር ስራተኞች እና መምህራን እንዲሁም ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች የእናንተ ድምር ውጤት ነው እና በኮሌጁ እና በኔ ስም ልባዊ ምስጋና ላቀርብላችሁ እወዳለሁ።

👉      ባሉበትጉዳዩ፡- የዳግም ምዝገባ አፈጻጸምን ስለማሳወቅ፤የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የዳግም ምዝገባ አፈጻጸምን በተመለከተ ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀ...
21/08/2025

👉
ባሉበት

ጉዳዩ፡- የዳግም ምዝገባ አፈጻጸምን ስለማሳወቅ፤

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የዳግም ምዝገባ አፈጻጸምን በተመለከተ ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ለግማሽ ቀን የሚቆይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡

በመሆኑም በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የሚሳተፍ የተቋሙ ባለቤት ወይም ተወካይ የሆነ አንድ ተሳታፊ ከላይ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት በትምህርት ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት እንዲሳተፍ እያሳሰበብን የተሳታፊው ሙሉ ወጪ ተሳታፊውን በሚልከው ተቋም የሚሸፈን መሆኑን እንገለጽን የተሳታፊዎችን ዝርዝር የሚገልጽ ሁለት ገጽ አባሪ ከዚህ ደብዳቤ ጋር አያይዘን ልከናል፡፡

Address

Dangila
Dangila

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tibeb Besu College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Tibeb Besu College:

Shortcuts

Share