Jawi Wereda Teachers' Association Page-Fendika

Jawi Wereda Teachers' Association Page-Fendika Education is a key to solve our problems❗️

07/08/2026


🙏❤
በ2018/19 ዓ.ም ከትምህርት ቤት ወደ ትምህርት ቤት የዝውውር ግብረ-መልስ ያልወጣላችሁን ጨምሮ የመጨረሻው ግብረ-መልስ በቴሌግራም ገጻችን ላይ ስለተለቀቀ ከታች ባለው ሊንክ ተመልከቱ።

ከዚሁ ጎን ለጎን ​በአሁኑ ወቅት የዝውውሩን ሥራ እየሰራን ስለሆነ፣ በቅርብ ቀን አጠናቀን እስክናሳውቃችሁ ድረስ በትዕግሥት እንድትጠብቁን እናሳስባለን።

https://t.me/+3LLEMLj5tn00YWE0

የጃዊ ወረዳ መምህራን ማህበር ጽህፈት ቤት
ነሐሴ፤ 01/2018 ዓ.ም
ፈንድቃ

 !~~~~~~~~~~~~~~~~~በምዕራብ ጎጃም ዞን በመምህርነት እና በትምህርት ቤት አመራርነት እየሰራችሁ ላላችሁና መስፍርቱን ለምታሟሉ ሁሉ የወጣ የርዕሰ-መምህርነት የደረጃ ዕድገት ቅጥር ማ...
06/08/2026

!
~~~~~~~~~~~~~~~~~
በምዕራብ ጎጃም ዞን በመምህርነት እና በትምህርት ቤት አመራርነት እየሰራችሁ ላላችሁና መስፍርቱን ለምታሟሉ ሁሉ የወጣ የርዕሰ-መምህርነት የደረጃ ዕድገት ቅጥር ማስታወቂያ!

05/08/2026
04/08/2026


***************
የዳንግላ ዙሪያ ወረዳ የ2018/19 ዓ.ም መርሱ ከትምህርት ቤት ትምህርት ዝውውር ከዚህ በታች ባለው የቴሌግራም ቻናላችን ተለቋል ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ።

የጃዊ ወረዳ መርሱ ከትምህርት ቤት ትምህርት ቤት ዝውውር ተሰርቶ ሲጠናቀቅ የምናሳውቅ ይሆናል።

 !🌟®®®®®®®®®​በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ በጃዊ ወረዳ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል የወርቅ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተ...
04/08/2026

!🌟
®®®®®®®®®
​በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ በጃዊ ወረዳ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል የወርቅ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የአንደኝነትን ደረጃ ተቆናጠዋል!

​🏆 የከፍተኛ ውጤት አሸናፊዎች፦

​🥇 1ኛ፦

​🏫 ከወርቅ ሜዳ ትምህርት ቤት |
📊 አማካይ ውጤት፦ 90.28%

​?? 2ኛ፦

​🏫 ከወርቅ ሜዳ ትምህርት ቤት |
📊 አማካይ ውጤት፦ 89.03%

​🥉 3ኛ፦

​🏫 ከወርቅ ሜዳ ትምህርት ቤት |
📊 አማካይ ውጤት፦ 88.06%

​👏 ውድ ተማሪዎቻችን፣ ለዚሁ አስደናቂ ውጤት አብቅቷችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ!

​💡 የነገ የተሻለ እና ብሩህ ተስፋ የሚገነባው በዛሬው ጠንካራ ትጋትና ጥረት ነው፤ በመሆኑም ወደፊትም ለበለጠ ውጤት በትምህርታችሁ በርቱ፣ ጠንክሩ እንላለን!

 ‼️®®®®®®®®®በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፤ ጃዊ ወረዳ በ2018 ዓ/ም ከተፈተኑ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያመጡ!!1ኛ➞   ከአልኩራንድ ትምህርት ቤት አማካይ=93....
03/08/2026

‼️
®®®®®®®®®
በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፤ ጃዊ ወረዳ በ2018 ዓ/ም ከተፈተኑ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያመጡ!!
1ኛ➞
ከአልኩራንድ ትምህርት ቤት አማካይ=93.22
2ኛ➞
ከጃዊ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት አማካይ=90.59
3ኛ➞
ከጃዊ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት አማካይ=89.64

ውድ ተማሪዎቻችን ለዛሬው ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ!!!

ለነገው የተሻለ ውጤት ደግሞ ዛሬ ላይ ጠንክሮ መማርን ይጠይቃልና በርትታችሁ እንድትማሩ እንላለን።

03/08/2026

!!!
®~~~~~~~~~~~~~~~~~®
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት በቴክኖሎጅ ታርሞ ይፋ የተደረገ ሲሆን በክልሉ 194374 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸው ይታወቃል። ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 165342(85.06%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ይህም ከባለፈው አመት ተመሳሳይ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ3% ብልጫ አሳይቷል።

ተማሪዎች በሁለት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ ሲሆን :-
➊ በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) ለ6ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara6.ministry.et/ #/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2) በሚመጣው ቅጽ (form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት
3) ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡
❷ በተጨማሪም በሚለው የቴሌግራም ቦት ላይ በመግባት ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ ሲሆን ለመጀመሪያ
1) start የሚለውን ይጫኑ!
2) በመቀጠልም ክፍልዎን ይምረጡ
3) ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ
4) በመቀጠል የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው ማቅረብ ይችላሉ። ቅሬታቸውንም ለማቅረብ

➌ በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ላይ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application )
1) ለ6ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara6.ministry.et/ #/complaint የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2) በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የተማሪውን የመጀመሪያ ስም (First Name)በማስገባት
3) የትምህርት ዓይነት አሳይ(Fetch course) የሚለውን ቁልፍ በመጫን
4) ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ
5) በመጨረሻም ሪፖርት (Add Complaint) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ።

ማስታወሻ ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡

 ‼️  🙏
03/08/2026

‼️

🙏

02/08/2026

!!!
®~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~®
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ይፋ ሆኗል።

የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት በቴክኖሎጅ ታርሞ ይፋ የተደረገ ሲሆን በክልሉ 173699 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸው ይታወቃል።
➤ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135003(77.72%)ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ይህ ውጤት ከ2017ዓ.ም ከተመዘገበው ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ20% ጭማሪ(እድገት) ተመዝግቧል።

ተማሪዎችም ውጤታቸውን በሁለት አማራጮች ማየት የሚችሉ ሲሆን:-
➊ በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara.ministry.et/ #/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2) በሚመጣው ቅጽ (form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት
3) ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡

❷ በተጨማሪም በሚለው የቴሌግራም ቦት ላይ በመግባት ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ ሲሆን መጀመሪያ
1) start የሚለውን ይጫኑ!
2) በመቀጠልም ክፍልዎን ይምረጡ
3) ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ
4) በመቀጠል የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው ቅሬታ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን ይችላሉ። ቅሬታቸውንም ለማቅረብ
➌ በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ላይ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara.ministry.et/ #/complaint የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2) በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የተማሪውን የመጀመሪያ ስም (First Name)በማስገባት
3) የትምህርት ዓይነት አሳይ(Fetch course) የሚለውን ቁልፍ በመጫን
4) ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ
5) በመጨረሻም ሪፖርት (Add Complaint) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ።

#ማሳሰቢያ፦ውጤት ለማየት በቅድሚያ VPN ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።

👉 2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል።

ምንጭ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

Address

Dangila

Telephone

+251918131117

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jawi Wereda Teachers' Association Page-Fendika posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share