13/09/2019
- Ethiopia
የ2012 የዩኒቨርስቲ የመግቢያ ነጥብ ውሳኔ መግለጫ
በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመደበኛና በግላቸው ተምረው ለዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና 322,717 ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን 319,264 (ወንድ 180,825; ሴት 138,439) ለፈተና ተቀምጠዋል፡፡ ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ 43.36 በመቶ ሴቶች ነበሩ፡፡
ከውጤት መጋሸብ ችግር ጋር በተያያዘ በ2012 የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት በ4 የትምህርት አይነቶች ማለትም፤
ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በእንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ ቴስት እና ፊዚክስ
ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በእንግሊዘኛ፣ በሒሳብ እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ ቴስት እና ጂኦግራፊ
በአራት የትምህርት አይነቶች ከ400 እንዲያዝ ተወስኗል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ 1152/2011 አንቀፅ 40(3) በተደነገገው መሰረት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የቅበላ መስፈርትን ይወስናል፡፡
በዚሁ መሰረት የተመዘገበውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት እና በግልና በመንግስት, ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያለውን የቅበላ አቅም መነሻ በማድረግ ወደ ዩኒቨርስቲ ገብተው መማር የሚችሉት በ4ቱ ትምህርት አይነቶች ከአራት መቶ 140 እና ከዚያ በላይ ያመጡት ብቻ ይሆናሉ፡፡ በዚህ አነስተኛው የመግቢያ ነጥብ ከጠቅላላ ተፈታኞች 233,102 (73.07 በመቶ) ያህሉ በከፍተኛ ትምህርት መማር የሚችሉ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከነኚህም ውስጥ 142,821 ተማሪዎች በመንግስት ተቋማት መደበኛ ፕሮግራም ቅበላ ያገኛሉ፡፡ የተቀሩት 90,281 በግላቸው በመንግስትና በግል ተቋማት ገብተው መማር ይችላሉ፡፡
በመንግስት ተቋማት ቅበላ ከሚያገኙት 142,821 ውስጥ 61,567 (43.1 በመቶ) ሴቶች ያሆናሉ፡፡ ዝርዝር የመግቢያ መስፈርትና የመቁረጫ ነጥብ በምስሉ እንደሚታየው ተጠቃልሎ ቀርቧል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
ጳጉሜ 06/2011
አዲስ አበባ