08/06/2026
በሀላባ ዞን በዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት 8.6 ኪ.ሜ መንገድ ግንባታ ሥራ ሕብረተሰቡን በማስተባበር ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው
=====
ሰኔ 01/2018 በዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ህብረተሰቡን በማስተባበ አርሾ አቦክቾ-አርቶ-ምዕራብ ጎርጣንቾ ቀበሌ 8.6 ኪ.ሜ 100% መንገድ ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ የቀጠለ ስሆን የመንገድ ያለበት ደረጀ በዛሬው ዕለት ምልከታ ተደርጓል።
በዞኑ የቱርስት መስህብ የሆነዉ ወዳ አርቶ ፍል ዉሃ የሚወስደዉን መንገድ ማለትም ከታች አርሾ - አቦክቾ - አርቶ -ምዕራብ ጎርጣንቾ 8.6 ኪ.ሜ 100% የመንገድ ግንባታ ስራ በፍጥናት እና በጥራት እየተሰራ ይገኛል።
መንገዶች የዉስጥ ለዉስጥ ጥገና ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ ስሆን ህብረተሰቡ ከልማቱ ጎን በመሠለፍ ድጋፍ እና ትብብር ማድረግ እንደሚገባ ተገልጸዋል።
በየደረጃው እየተሰሩ ያሉ የቀበሌ የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ስራዎች መንደርን ከመንደር ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኙ ስለመሆናቸው በምልከታው ወቅት ተጠቁሟል።
በየቀበሌው የሚስተዋሉትን የውስጥ ለውጥ የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን ለመቅረፍ ደረጃ በደረጃ ምላሽ ማግኘት እንዲችሉ በቅንጅት እና በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
የመንገዱን ጥገናውን የዌራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤ ምክትል እና የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጀማል አህመድ የዌራ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ቹቹ መሀመድ ምልከታ መደረጋቸውን ከወረዳው መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
ቴሌግራም፦ https://t.me/+eIbzwXJYyQNlYjVk
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=100083958027668
በቲክቶክበ፦ tiktok.com/
በቲውተር፦ https://x.com/Halabazonecomun?t=jrF0ELvPbOBJOuLT6X3G1A&s=09
ዋትስአፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029Vb3YNPxJZg4GKKQ3Om3v
ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/?si=SJOXf764DKjW1CUe
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/halabazonecomunication?igsh=a3NwdTUwand6NWhn
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
06/06/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም የህብረተሰቡን የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ተገለፀ
29/9/2018 ዓ/ም( ወልቂጤ) በክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም የስራ አፈፃፀም ተገመገመ
በመድረኩ የክልሉ ትራንስፖርት መንገድ ልማት ቢሮ ምክትልና የሁሉ አቀፍ ገጠር ተደራሽ መንገድ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቲዎስ ሎምበሶ እንዳሉት ፕሮግራሙ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልፀዋል።
የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም በክልሉ ለአምስት ዓመት የሚተገበር ፕሮግራም መሆኑንም ጠቅሰው፣ባለፉት ሁለት ዓመታት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች መስራቱንም ገልጸዋል።
በፕሮግራሙ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የስራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱንም ያስታወቁት አቶ ማቴዎስ፣ፕሮግራሙ በክልሉ በሚገኙ ወረዳዎች ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝም አመልክተዋል።
ምክትል ቢሮ ኃላፊው አክለውም ፕሮግራሙ በዋናነት በአዲስ መንገድ ግንባታ፣ በጥገና መንገድ፣ በስፔሻል ስትራክቸር ስራዎች እናተንጠልጣይ ድልድይ ግንባታና የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ላይ ማተኮሩንም ገልጸዋል።
ፕሮግራሙ የክልሉን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝም የገለጹት አቶ ማቴዎስ፣ባለድርሻ አካላት የፕሮግራሙን ዕቅዶች በተሻለ ደረጃ ለማሳካት ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
በመድረኩ የፕሮግራሙ የ2017እና2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም፣የተገኙ ስኬቶችና ያጋጠሙ ችግሮች ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የሪካፕ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ መሀመድ ባሙድ እንዳሉት አጠቃላይ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ማለቅ እንዳለባቸው ጠቅሰው ለቀጣይ ፕሮጀክቶች መዘጋጀት እንዳለባቸው ለኮንትራክተሮችና አማካሪዎች አሳስበዋል።
ፕሮጀክቶችን እንዴት መጨረስ እንዳለብን የሚለውን ሀብታችንን ተጠቅመን አሰሪው፣ አማካሪውና ተቋራጩ ውጤት ለማምጣት በባለቤትነት አቅማችንን አሟጠን መጠቀም አለብን ብለዋል።
በመጨረሻም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተግባብቶና ተስማምቶ የተሻለ አፈፃፀም ለማምጣት በቁርጠኝነት መስራት አለብን ብለዋል።
በመድረኩ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አመራሮች፣የሪካፕ ባለሙያዎች፣ የስራ ተቋራጭችና አማካሪዎች ተሳታፊ ሆኗል።
04/06/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በምግብ ዋስትናና የገጠር ልማት ትስስር ፕሮግራም በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተደደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ ምልከታ አደረጉ ።
በዛሬው ዕለት ግንቦት 27/2018 ዓ/ም በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በ2017 እና 2018 በሪከፕ ፕሮግራም እየተገነቡ ያሉ #ጫንቡላ-ድኖቆሳ-ሙዳ ማያፋ-ጫንቡላና #መያፋ-ድኖቆሳ-ዊሻሞ 18.2ኪ.ሜ መንገድ አድስ ፕሮጀክት እና #ጮሮቆ-አለምጤና-ሀብቦና #ገዳባ- ሀማጣ-አይማሌ 21.4ኪ.ሜ መንገድ ጥገና ሥራዎችን የደረሱበትን ደረጃ ከሚመለከታቸው አካለት ጋር በመሆን ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ ተመልክቷል።
እንዲሁም በ2017 በጀት ዓመት ተጀምሮ እየተገነባ ያለውን አንደኛ አሾካ-ሁለተኛ አሾካ አነስተኛ ስትራከሰቸር(ድልድይ) ግንባታ ሥራ አሁን ያለበት ደረጃ ምልከታ ተደርጓል።
15/05/2026
➼ ማስታወቂያ‼️
➼ለባለ-ሁለት እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች!
===============
ግንቦት፤07/2018ዓ.ም
በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በነገዉ ዕለት ቅዳሜ ግንቦት 08 ቀን 2018ዓ.ም በነዳጅ ማደያዎች የሚኖረዉ የቤንዚን ስርጭት አገልግሎት ከዚህ በታች ባለው ፕሮግራም መሠረት ይሆናል።
በመሆኑም ባለ-ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች በሙሉ ወደየተመደቡበት ነዳጅ ማደያ ሲመጡ ጊዜያዊ የመቅጃ ኮፖን ይዛችሁ በስነ-ስረዓት በጊዜ በመሰለፍ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ሲንል የሁልጊዜ መልዕክታችንን ከታላቅ አክብሮት ጋር እየገለጽን በነገዉ ዕለት የሚኖረዉን የቤንዚን ስርጭት ፕሮግራም ከዚህ በታች እንደሚከተለዉ ቀርቧል።
#1ኛ, #ዲስከቨር ጊዜያዊ የመቅጃ_ኮፖን የያዛችሁ ባለ-ሁለት እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች በሙሉ ነገ ግንቦት 08 ቀን 2018ዓ.ም .2 (የቀድሞ ጎመጁ) ኢንስፔክተር እቴቱ አቡሻ ሆቴል ጎን በሚገኘዉ ነዳጅ ማደያ የሚትስተናገዱ ይሆናል፤
#2ኛ, #ቦክሰር ጊዜያዊ የነዳጅ መቅጃ ኮፖን የያዛችሁ ባለ-ሁለት እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች በሙሉ ነገ ግንቦት 08 ቀን 2018ዓ.ም (መሀመድ አ/ረህማን) ወደ ሻሸመኔ መውጫ #አይመሌ ማዞሪያ መንገድ አጠገብ በሚገኘዉ ነዳጅ ማደያ የሚትስተናገዱ ይሆናል።
#3ኛ, ጊዜያዊ የነዳጅ መቅጃ ኮፖን የያዛችሁ ባለ-ሁለት እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች በሙሉ ነገ ግንቦት 08 ቀን 2018ዓ.ም /ዙመርድ ወይም ሼሆች/ ወራቤ መውጫ ጮሮቆ በሚገኘዉ ነዳጅ ማደያ የሚትስተናገዱ መሆኑን እየገለጽን አሽከርካሪዎች በፕሮግራሙ መሠረት ጊዜያዊ የነዳጅ መቅጃ ኮፖኑን በመያዝ ወደ ነዳጅ ማደያ በጊዜ ቀርባችሁ በስነ-ስርዓት በመሰለፍ 1ሊትር ቤንዚን መንግስት ባወጠዉ ታሪፍ መሰረት ግብይትዎን በቴሌብር በመፈጸም ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል እንገልጻለን።
በመሆኑም የነዳጅ ማደያዎቹ በዚህ በወጠዉ ፕሮግራም መሰረት የማያስተናግዱ/የነዳጅ ስርጭት አገልግሎት/ በአግባቡ የማይሰጡበት ሁኔታዎች ስኖሩ ከዚህ በታች የተጠቀሱ የስልክ መስመሮችን በመጠቀም በዕለቱ ለተመደቡ ለተቆጣጣሪ ባለሙያዎች ጥቆመዎትን ወይም ቅሬታዎን ማቅረብ ይችላሉ።
✅ የተቆጣጣሪ ባለሙያዎች ተቆጣጣሪ/ጠርናፍዎች፤
• +251913519367
• +251930784646
✅ የተቆጣጣሪ ባለሙያዎች ስልክ መስመር፤
• +251912807539
• +251931352050
• +251916580336
• +251922238176
ማሳሰቢያ!!
=======
➠ የባለ-ሁለት እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች በሙሉ ቤንዚን ስርጭት አገልግሎት ለማግኛት ወደየተመደባችሁበት ማደያ ስትመጡ ጊዜያዊ የነዳጅ መቅጃ ኮፖን ስለመየዛችሁ ያረጋግጡ እና ያለኮፖን የሚመጠ ማንኛዉም አሽከርካሪ አገልግሎቱን የማያገኝ መሆኑን በድጋሚ እናሳስባለን።