25/07/2016
በሕይወት ዘመናቸው ወደዚህ ምድር ሲመጡ የተሰጣቸውን ጸጋ ወደ ፍሬ ለቀየሩ ሰዎች ሞት የእረፍት ብርድ ልብስ እንደመልበስ ነው፡፡
የኖርንባቸው ዓመታት ብዛት አይደለም ቁም ነገሩ፤
ምን ያህል በጥልቀትና በውጤት መኖራችን ነው፡፡
ለመጪዋ ኢትዮጵያ አንባቢ እና ተገንዛቢ ትውልድ እንዲበዛላት ማድረግ፡፡ ደራሲያንን ከተደራሲያ ጋር የበለጠ እንዲዋሀዱ አገናዛቢ (አንቂ) ድልድይ መሆን፡፡
25/07/2016
በሕይወት ዘመናቸው ወደዚህ ምድር ሲመጡ የተሰጣቸውን ጸጋ ወደ ፍሬ ለቀየሩ ሰዎች ሞት የእረፍት ብርድ ልብስ እንደመልበስ ነው፡፡
የኖርንባቸው ዓመታት ብዛት አይደለም ቁም ነገሩ፤
ምን ያህል በጥልቀትና በውጤት መኖራችን ነው፡፡
24/06/2016
“I always like walking in the rain,
so no one can see me crying.”
― Charlie Chaplin
“በዝናብ ውስጥ መሄድን እወዳለሁ
ለቅሶዬን፣ የሚፈሰውን እንባዬን ስለሚደብቅልኝ፡፡”
--ቻርሊ ቻፕሊን
14/04/2016
ሰነባብቼ ተመለስኩ ለመዘግየቴ ይቅርታ እየጠየኩኝ ለማስታወስ ያህል ከባለፈው ፅሑፍ ላይ ትንሽ….
የካቲት 28 በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ዓለም አቀፍ ስብስባ (International Conference) ነበረ፤ ሁለት ቀን በሚቆየው ኮንፈረንስ የተለያዩ ጥናት አቅራቢዎች አገር በቀል የሙዚቃ ዕውቀቶች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ሊኖራቸው ስለሚገባ ሚና ተቋማቱም እነዚህን ሀገር በቀል የሙዚቃ ዕውቀቶች ለማሳደግ ሊኖራቸው ስለሚገባ ሚና በስሱም ቢሆን ለመዳሰስ የታቀደ ነበር ማለት እችላለሁ፡፡
በስብሰባው ሊቀ ጉባዔ ጌታሁን ደመፀ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ “የግዕዝ ቋንቋ በአማርኛ ቋንቋ እየተሸፈነ ስለመጣ የግዕዝ ቋንቋ ምን ያደርጋል” ከሚለው ሐሳብ ቀጥሎ “ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ዱላ ይበዛበታል” “4ና 5 ዓመት ይሰጥ የነበረው የያሬድ ዜማ ትምህርት ለምን ወደ አንድ ዓመት ወረደ ተብለን አልተጠየቅንም” “አዛዥ የሚለው ስያሜ ለቤተ ክርስቲያኗ ሰዎች የሚሰጥ ማዕረግ አይደለም….” የሚለው ሀሳብ በአንድ ግለሰብ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ለተነሱት ሀሳቦች አጠር አድርጌ ሀሳቤን የምሰጥ ሲሆን እናንተ ግን አሁንም እንደባለፈው እንደማኝኛውም ኢትዮጵዊ ሰፋ አድርጋችሁ አስቡት፡፡
1ኛ “ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ዱላ ይበዛበታል” ገበሬ እህሉና አጭዶ ከምሮ ፍሬውን ከገለባው ለመለየት እንደሀገሩ ባሕል እንዳለው መሳሪያ ያበራየዋል ይህ ማለት እንሰሶች ካሉ ከብቶች ፈረሶች ወይም አህዮች በእነሱ ኮቴ እንዲረገጥ ይደረጋል፤ ከእንስሶቹ ኮቴ ያመለጠ ከገለባው ጋር ታፍኖ የቀረ ካለ ደግሞ በዱላ ይወቃል እንግዲህ ይህ ሁሉ የሚሆነው እህሉ ዱላ የሚበዛበት የሁላችንንም ሆድ የምግብ ጥሪ ዝም የሚያስብለውን ፍሬ ከገለባው ለመለየት ነው፡፡ ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት በተለያየ ጊዜ እንደ ሀሳብ ገላጩ አባባል ዱላ የሚበዛበት ሲጀመር በውስጡ ላሉ ተማሪዎች ከዛም ወጥቶ ለሀገሪቷ ከዛም አልፎ ለዓለም የሚሆን ፍሬ ከገለባው ለይቶ ማውጣት ስላልቻለ ነው፡፡ ዱላ ይበዛበታል ብሎ ማለቃቀስ ይሻላል? ወይስ ለምንድን ነው ዱላ የበዛብን ብሎ በመጠየቅ ፍሬ ለማፍራት መጣር?
2ኛ “4ና 5 ዓመት ይሰጥ የነበረው የያሬድ ዜማ ትምህርት ለምን ወደ አንድ ዓመት ወረደ ተብለን አልተጠየቅንም” ይህ ሀሳብ ጥናት አቅራቢው የቅዱስ የሬድ ዜማ ድርሰቶች በሚገባ በት/ቤቱ እየተሰጡ አይደለም ለሚለው ሀሳብ የቀረበ ነበረ፡፡ እዚህ ጋር ሀሳብ ሰጭው ለማለት የፈለጉትን የተረዱት አልመሰለኝም አንድ ዓመት ይሰጥ የነበረውን የቅዱስ ያሬድ ዜማ ትምህርት እኮ በሁለት ሦስት ዓመት አሳድገናል አይደለም እያሉ ያሉት ከ4ና ከ5 ዓመት ዘፍ አድርገን አውርደን አንድ ዓመት አድርገነዋል ነው፤ ይህ አባባል የቅዱስ ያሬድ ዜማ ትምህርት ጨርሶ ወደ መጥፋቱ ዋዜማ ላይ ነን ማለት ነው፡፡ ለዚህ ሒደት ለምን? ብሎ ጠይቆ የሚቀርቡትን መልሶኝ እንደማስተዛዘኛ መውሰድ ፈጽሞም አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ትምህርት ከ5 ዓመት ወደ አንድ ዓመት መዝቀጡ በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ያሉ ኃላፊነቱ ያላቸው ሰዎች ኃላፊነታቸው በሚገባ አለመዋጣታቸውን ነው የሚያሳየው፤ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምንም መፍትሔ ፈልገው እንደውም ከበፊቱ በተጠናከረ መልኩ እንዲሰጥ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
3ኛ “አዛዥ የሚለው ስያሜ ለቤተ ክርስቲያኗ ሰዎች የሚሰጥ አይደለም….” እዚህ ጋር ልብ አድርጉልኝ የኢትዮጵያን ታሪክ በተለያየ አጋጣሚ የተማራችሁ የሰማችሁም፡፡ እኔ እዚህ ጋር እነ አዛዥ ጌራና አዛዥ ራጉኤል የቤተ ክርስቲያኗ ምሁራን ናቸው አይደሉም የሚለውን ሀሳብ አይደለም የማነሳው ግን እንደማንኛው ተራ ኢትዮጵያዊ በመሆን ታሪካችንን እንዲሁ በኅሊናዬ ቃኘት ሳደርግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የዕውቀት ጸበል ያልቀመሱ ከጠበብብ ማዕዷን ያልተቋደሱ ነገሥታት እጅግ በጣም ጥቂቶች ናቸው ብል ደፋር አያስብለኝም፡፡ በሀገራችን ጎልተው የሚታዩ ዓለምንም ድንቅ ያስባሉ በነገሥታቶቻችን ተሠሩ ተደረጉ የሚባሉ ታሪኮች ስንመለከት ምንጫቸው ከቤተ ክርስቲያኗ በተገኙ ጥበባት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ታሪክ የሠሩ ነገሥታቶቻችን የእውቀት ምንጫቸውን የትምህርት ደረጃቸውን ስናይ ከድቁና ጀምሮ እስከ እስከ የቅኔ፣ የዜማ፣ የመጻሕፍት ሌሎችም ሊቅነት ድረስ ከሕይወት መዝገባቸው ላይ አይጠፋም፡፡ በሀገራችን ዘመናዊ ትምህርት እስከጀመረበት ጊዜ ድረስ ሕዝቡን በዕውቀት ታንጽ የነበረች ቤተ ክርስቲያኗ ነበረች ለዚህ ደግሞ አሁንም በሕይወት ያሉ የሀገራችን ምሁራን ሥራቸውም ጭምር ይመሰክራል፡፡
እኔ እዚህ ጋር ለማስቀመጥ የፈለኩት ለሁላችንም የዚህ ጽሑፍ አንባብያን የመወያያ ሀሳብ ለመስጠት ነው፡፡ ስለ አዛዥ ጌራና አዛዥ ራጉኤል ማንነት በሚቀጥለው ለማቅረብ ቃል እየገባሁ ቸር እንሰንብት እላለሁ፡፡
16/03/2016
“የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች በከፍተኛ ተቋማት በአሁኑ ጊዜ ያለበት ደረጃ ዕውቅና” “The current status of St. Yared music works in higher institutions and its promotions.”
የካቲት 28 በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ዓለም አቀፍ ስብስባ (International Conference) ነበረ፤ ሁለት ቀን በሚቆየው ኮንፈረንስ የተለያዩ ጥናት አቅራቢዎች አገር በቀል የሙዚቃ ዕውቀቶች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ሊኖራቸው ስለሚገባ ተቋማቱም እነዚህን ሀገር በቀል የሙዚቃ ዕውቀቶች ለማሳደግ ሊኖራቸው ስለሚገባ ሚና በስሱም ቢሆን ለመዳሰስ የታቀደ የታለመ ነበር ማለት እችላለሁ፡፡ ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ በዕለቱ የቅዱስ ያሬድ ዜማ እንዲሁም የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ከሃይማኖታዊ ዕይታ ውጪ በዕለት ተዕለት የማህበረሰቡ ኑሮ ውስጥ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ እጅግ በጣም ሰፊ ሆኖ በመሆኑ በስሙ የተሰየመው የያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ለቅዱስ ያሬድ ዜማ ስለሰጠው ቦታና ሊሰጠው ስለሚገባው ቦታ የትምህርት ቤቱን የቅርብ ጊዜ ሥርዓተ ትምህርት (Curriculum) በመገምገም ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበው ነበር፡፡
በጥናታዊ ጹሑፉ አቀራረብ እጅግ ስሜትን በሚፈነቅል ሁኔታ የተደሰቱም እንዳሉ ሁሉ ስሜታዊ በሚያደርግ መልኩም ያዘኑም አልጠፉም፡፡ እስኪ የተሰጡትን ሀሳቦችና የተነሡትን ጥያቄዎች በዕለቱ ከሰዓት ጥበት የተነሣ ሊቀ ጉባዔ መልስ ባይሰጡባቸውም እኔ እንደ የትኛውም ምሑር ማለትም እንደ ዘመናዊ የሙዚቃ ሰው ወይም እንደ ቤተ ክርስቲያን የዜማ ሊቅ ሳይሆን እንደ ማንኛው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሀሳቦቹ ሲነሡና ጥያቄዎቹ ሲቀርቡ የተሰማኝን ልናገር፡፡
1ኛ፡ እጅግ በጣም ያስደነገጠኝ ሀሳብ “የግዕዝ ቋንቋ በአማርኛ ቋንቋ እየተሸፈነ ስለመጣ ለምን የቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓቶች ከግዕዝ ወደ አማርኛ አይለወጡም የግዕዝ ቋንቋ ማወቅ ምን ያስፈልጋል” ቃል በቃል ሳይሆን ሀሳቡን ጠቅለል በማድረግ ነው ያቀረብኩት፡፡ ግዕዝ ቋንቋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋንቋ ብቻ ነው ያለው ማነው? ግዕዝ ቋንቋ የሀገሪቷ ሀብቶች ተቀርጾ ተመዝግቦ የሚገኝበት ታላቅ ቋንቋ ነው፡፡ እንኳንስ የማንነት አሻራ የሰፈረበት የበለጸገ የቋንቋዎች ሁሉ ቅድም አያት ተብሎ በምዕራቡ ዓለም ትልቅ ክብር የተሰጠው ግዕዝ ቋንቋ ቀርቶ ማንኛው ቋንቋ ይቅር ብሎ ሀሳብ መስጠት አንድን ሀገር በአቶሚክ ቦምብ ከመደብደብ በምን ይተናነሳል? ቋንቋ በውስጡ ማንነትን፣ ታሪክን፣ ባሕልን፣ ዜማን፣ ሀብትን፣ ብሔራዊ ሉዓላዊነትን የመሳሰሉትን የያዘ ነው፡፡ የምዕራቡ ዓለም ከሀገራችን በተለያዩ ጊዚያት የወሰዱዋቸውን የጤና፣ የስነ ከዋክብት፣ የፍልስፍና እጅግ በጣም ብዙ የሚባሉ ሌሎችም መጻሕፍት መዛግብት መንዝሮ ዘርዝሮ ወደ ሀብት ለመቀየር ግዕዝ ቋንቋን በከፍተኛ ተቋማት እንዲሰጥ ጥረት በሚደረግበት ጊዜ እኛና ምሁሮቻችን ግን ምን ያደርጋል በሚል የሞተ ሀሳብ መታነቃችን ለቃላት በሚከብድ መልኩ አሳፋሪ ነው፡፡ እውን ግዕዝ ቋንቋን እንደ ቋንቋችን ከልጅነት እስከ ዕውቀት ብንማረውና የሕይወታችን አካል ብናደርገው ኋላ ቀርነት ነውን? ወይስ አንዳንዶቻችን ሳይታወቀን የአጥፊነት ክፉ አስተሳሰብ ውስጥ ገብተናል? እስኪ አስቡት፤ አንድ ኢትዮጵያዊ በመድኃኒት ቅመማ ትምህርት እጅግ በላቀ ውጤት ተመርቆ ቤተሰበቹ የቋንቋዎቹ አስፈላጊነት ተገንዝበው ከልጅነት እንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ አልፎም ጀርመንኛ ስላስተማሩት ልጁ ሁለገብ ተብሎ ጀርመን ሀገር ከሚገኘው ባየር የመድኀኒት ቅመማ ማምረቻ (Bayer Pharmaceutical Company) ተቀጥሮ ሄደ እንበል፤ እዚያ እንደ ደረሰ ሦስት የሌሎች ሀገሮችን ቋንቋ የሚያቀላጥፍ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ ግዕዝንማ ያመሠጥረዋል ብለው አባቶቻችን ከፍየል ቆዳ ብራና ዳምጠው፣ ከዕፀዋት ቀለም በጥብጠው፣ ከሸምበቆ ብዕር ቀርጸው የጻፉትን የግዕዝ መጽሐፍ ሲያመጡለት ቁልጭ ቁልጭ ቢል “ቅ” ድንቄም ጀርመንኛ ቢሉ ጀርመኖቹ ወይም አንዱ ጀርመናዊ “አድግ ዘትጽዕነት ኢተአምር ከመ ምንት ተጽዕነት አንትሙ ውእቱ ውሉደ ኢትዮጵያ ከመ ዛቲ” ብሎ በግዕዝ ቢተርትበት አያድርስ፡፡ ትርጉሙም “አንድ የተጫነች አህያ መጫናዋ እንጂ ምን እንደተጫነች አታቅም እናንትም የኢትዮጵያ ልጆች እንደርሷ ናችሁ” ኢትዮጵያውያን ናችሁ ታሪክ እንዳላችሁ ታወራላችሁ ግን ታሪካችሁን አታውቁም ክብር እንዳላችሁ ትናገራላችሁ ክብራችሁን ግን አታውቁትም፡፡
2ኛ “ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ዱላ ይበዛበታል” “4ና 5 ዓመት ይሰጥ የነበረው የያሬድ ዜማ ትምህርት ለምን ወደ አንድ ዓመት ወረደ ተብለን አልተጠየቅንም” “አዛዥ የሚለው ስያሜ ለቤተ ክርስቲያኗ ሰዎች የሚሰጥ አይደለም….” ፡-)….. ለሚለው በሚቀጥለው፡፡
09/02/2016
"Beasts of No Nation "
AGU: I saw terrible things... and I did terrible things. So if I'm talking to you, it will make me sad and it will make you too sad. In this life... I just want to be happy in this life. If I'm telling this to you... you will think that... I am some sort of beast... or devil. I am all of these things... but I also having mother... father... brother and sister once. They loved me.
02/10/2015
አባት ልጁ ሲወለድ፣ ሚስቱ ስታምጥ ከጎንዋ መሆን አለበት?
በሌሎች ሀገሮች በተለይ በምዕራቡ ዓለም ይህ የተለመደ ነው፤ አባት ማዋላጃ ክፍል ገብቶ ልጁ ሲወለድ፣ ሚስቱ ልጃቸውን ለመውለድ “ማማጥ ማለት ሞትን ነክቶ መመለስ ማለት ነው” የሚባልለትን የደስታ ዋዜማ የሆነው ስቃይ ማየት እንደ ባሕልም ጭምር ነው፡፡ ይህ ነገር በእኛ ሀገር ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ባል ውጪ ሆኖ እንዲጠብቅ ነው የሚደረገው፡፡
ማዋለጃ ክፍል ውስጥ ገብቶ በወሬ በስማ በለው የሚሰማውን የመወለድን ታላቅ ምሥጢር በከፊልም ቢሆን የማየት ዕድል ይኖረዋል፡፡ ባለቤቱ ልጃቸውን ለመውለድ የምታሳልፈውን እያንዳንዱዋን ጥልቅ የሆነች ኅመም ከጎኑዋ ሆኖ መካፈሉ፤ እናቱ እንዴት እንደ ወለደችው፣ ልጃቸው እንዲፀነስ ካበረከተው እጅግ በጣም ቀላል የሆነ አስተዋፅዖ ባለቤቱ ዘጠኝ ወርና ከዛም በላይ በማኅፀኗ ተሸክማ ከዛም ወደዚህ ምድር በሚመጣበት ጊዜ የምታልፈውን ጽኑ የሆነ ህመም በቦታው ሆኖ ማየቱ እጅግ ታላቅ የሆነ የዕውቀት፣ የማስተዋልና የመለወጥ ጊዜን ይፈጥርለታል፡፡ እሱም ሆነ ልጁ ከጠባቡ ዓለም ወደ ሰፊው ዓለም የሚሸጋገርበትን ከፈጣሪ ሥራ አስደናቂ ከሚባሉት ዋነኛውና ታላቁን ሁነት እዛው በቦታው ላይ ተገኝቶ ማየትን የመሰለ ነገርም ይኖራል ብለን አንገምትም፡፡
02/10/2015
በእርግጠኝነት የምናስበው ነገር….
ርኁሩኅ ወይም አዛኝ መሆን የሚባለውን ስንሰማ ለብዙዎቻችን ቀላል ይመስለናል፤ አንዳንዴ ደግሞ ርኁሩኅ ወይም አዛኝ መሆን ገንዘብ ኖሮት መስጠት ለሚችል ሰው ብቻ የተሰጠ የሚመስለን፤ መስጠትን ከሀብት ጋር ብቻ የምናያይዝ አለን፡፡
ሁላችንም ስንፈጠር ወደዚህች ዓለም ስንመጣ ሰው ከመሆናችን ጋር አብረው የሚወለዱ በውስጣችን ተቀብረው ከዛም ሰውነታችንን በምንተገብርበት ጊዜ የሚወጡ ስጦታዎች አሉን፤ ፍቅር ትልቁ መሠረት ሲሆን ከፍቅር ጋር ተያይዘው የሚመጡ ርኅራኄ፣ አዛኝነት፣ ደግነት፣ መስጠት ወዘተ… ናቸው፡፡ ነቅቶ ለሚኖር ማንኛው ሰብአዊ ፍጡር እነዚህን ስጦታዎች መተግበር እጅግ ቀላል ነው፤ ነገር ግን በግዴለሽነትና ሁሉጊዜ ስለራስ ብቻ በማሰብ ለሚኖሩ ሰዎች ግን የሰማይ ርቀቱን ያህል ይከብዳቸዋል፡፡
በጎናችን እጅግ ተከፍቶና አዝኖ ለሚያልፍ ሰው ምንም እንኳን ባናደርግለት ርኅራኄ በተሞላበት ሁኔታ ፈገግ ብንልለት ለዛ ሰው በውስጡ አንዲት ሚጢጢዬ ብርሃን የመፈንጠቅ ያህል ሊሆን ይችላል፡፡ እጅግ ተከፍቶ ወይም ተቸግሮ ብሶቱን፣ ኀዘኑን ሊያዋየን ለሚፈልግ ሰው አወቅነውም አላወቅነውም ዝም ብለን ጆሮአችን ሰጥትን በርኅራኄ ተሞልተን ብንሰማው ለዛ ሰው ትልቅ እፎይታ ነው፡፡ ርኅራኄን በዕለት-ተዕለት ሕይወታችን ተግባራዊ ብናደርገው ከማንም የበለጠ ደስተኛ የምንሆነው እራሳችን ነን፡፡ ርኅራኄ እጅግ ጥልቅ የሆነ ኃይል ያለው ከመሆኑ የተነሳ ማየት የተሳናቸው ያዩታል መስማት የተሳናቸው ይሰሙታል፡፡ በርኅራኄ ሥር መሠረት ሆኖ የተነጠፈ ፍቅር አለ፤ በርኅራኄ ውስጥ ትኅትና አለ፤ በርኅራኄ ውስጥ ዋጋው እጅግ ድንቅ የሆነ መስጠት አለ፤ በርኅራኄ ውስጥ አስተዋይነት አለ፤ በርኅራኄ ውስጥ ትዕግስት አለ፤ በርኅራኄ ውስጥ ዛሬን /አሁንነትን/ መኖር አለ፡፡
ርኅሩኅ ለመሆን ዕድሎች በየቦታው በዓይነት-በዓይነታቸው አሉ፤ ርኅራኄ ያለንበት የኑሮ ደረጃ፣ የዕውቀት ደረጃ ማንኛቸውም ነገሮች ሳይለያዩን ለሁላችንም በእኩል መጠን የተሰጠን ነገር ግን በዕለት-ዕለት ሕይወታችን ተግባራዊ ባደረግነው ቁጥር ታላቅ ኃይል የምናደርገው ጸጋ ነው፡፡ በሕይወታችን ውስጥ ካሉት መልካም እና ድንቅ ጉዞዎች ውስጥ አንዱ ርኅራኄ ነው፡፡ ርኅራኄ ብዙ ስብራቶችን ይጠግናል፤ ርኅራኄ ብዙ ድካሞችን ያበረታል፤ ርኅራኄ ብዙ ጨለማዎችን ያበራል፡፡
ርኅሩኅ መሆን ማለት የሌሎችን መጎዳት እንደራስ መጎዳት ማየት ነው፤ ርኅሩኅ መሆን ማለት ሁሉንም በፍቅረና በትኅትና መቀበል ነው፡፡ እኛ የዓለም አንድ አካል ነን ዓለም ደግሞ በሁላችንም ውስጥ አለች፤ የሌሎች መጎዳት ዓለምን እንደሚያጎድላትና እንደሚጎዳት ካሰብን በውስጣችን ያለችው ዓለም፣ አካሏ/ ክፋይዋ የሆነው ሰው መጎዳት የእኛም መጎዳት መሆንን አጥብቀን እንረዳለን፡፡
ፍቅር - ርኅራኄ - መስጠት፡፡ ያለምንም መጠይቅና ቅድመ-ሁኔታ ማፍቀር የማይችል ሰው ርኅሩኅ መሆን አይችልም፤ ርኅሩኅ ያልሆነ ሰው ሊሰጥ አይችልም፤ እነዚህ ሦስቱ ነገሮች ሰው የመሆን ምሥጢራት ውስጥ ብርቱዎቹ ናቸው፡፡ እኛ ዛሬ በስሱ ስለ ርኅራኄ ማውራታችን ወደ ፍቅርም ወደ መስጠትም ያንዠዋዥወናልና ነው፡፡
ቸር እንቆይ!
23/05/2015
**** MERAWIT FESEHA ****
Atronsbookclub Wishes You A Very Blessing Year ;-)
You are a very strong, smart, beautiful, sweet, a fighter above all you are a very special girl.
Keep doing it :-)
22/05/2015
An Ethiopian Film, Lamb, is Causing a Stir at Cannes. (BBC)
'Lamb' is a coming-of-age drama about nine-year-old Ephram and his constant companion, a sheep named Chuni, in Ethiopia. Ephram's affection for Chuni deepened after he lost his mother, to famine a year ago. Consequently, his beloved father sends him and Chuni far away from their drought stricken home land to live with distant relatives in a greener part of the country. Ephram soon finds himself to be a homesick outcast who is always getting into trouble. When his uncle orders him to slaughter Chuni for the upcoming holiday feast, Ephraim deviss a divious scheme to save the sheep and return to his home.
Director: Yared Zeleke (Screen-writer and Producer)
17/05/2015
''The Thrill Is Gone''
The thrill is gone
The thrill is gone away
The thrill is gone baby
The thrill is gone away
You know you done me wrong baby
And you'll be sorry someday
The thrill is gone
It's gone away from me
The thrill is gone baby
The thrill is gone away from me
Although, I'll still live on
But so lonley I'll be
The thrill is gone
It's gone away for good
The thrill is gone baby
It's gone away for good
Someday I know I'll be open armed baby
Just like I know a good man should
You know I'am free, free now baby
I'm free from your spell
Oh I am free, free, free now
I am free from your spell
And now that it's all over
All I can do is wish you well..
Riley B. King (B.B King) Sep 16, 1952 - May 14, 2015
14/05/2015
What Happened on May 14th this Day in History?
May 14th, 1897- Great Britain Signs Treaty with Emperor Menelik II of Abyssinia.
14/05/2015
What Happened on May 14th this Day in History?
May 14th, 1961- Bus with 1st Group of Freedom Riders Bombed and Burned in Alabama.