ሀገርኛ ቲዩብ - Hagergna Tube

ሀገርኛ ቲዩብ - Hagergna Tube

Share

ስነ ጾታዊ ሚስጥሮቾ የሚጋለጡበት ፣ በሀገርኛ ለዛ ተከሽኖ የ?

03/10/2025

መንግስት ደሞዝ ጨመረ? ኢኮኖሚስት ባልሆንም
ጭማሪ የተባለው የመንግስትን እንጅ የደሞዝተኛውን ችግር የሚቀርፍ አይመስለኝም ለምን እንበል።
ማሳያ 1
ደሞዙ 13,998 የነበረ ሰው በአዲሱ ጭማሪ 25,285 ሆነ። ደስ አይልም? እጥፍ በሉት። ነጋዴው፣ አከራዩ ወዘተ ደስታ ደግሞ ይለያል። ጭማሪያቸው እጥፍ ድርብ ይሆናል። (በቅርቡ እንኳን የሽንኩርት ዘይትና ቲማቲም ዋጋ ጭማሪው ያስተዛዝበናል።) በፐርሰንት ስንት እንያዝበት?...
ደሞዝተኛውስ?
ብሩን ሊወስድ ሲሄድ የስራ ግብር ከ25% ወደ 35% ፐርሰንት አድጓል። ይለዋል። ጋሽ ጡረታም 7% ፐርሰንት አለሁ ይለዋል። ለሸመታ ስትወጣ በድጋሚ እንደነጋዴው የማይመለስልህ (የቫት ተመላሽ) የማይደረግለትን 15% ወዬ ይለዋል። ወይኔ በላቸው!
እንደምረው
የስራ ግብር 35%
ጡረታ 7%
ቫት 15%
ወቸው ጉድ የደሞዝተኛው ደሞዝ 57% (14,412.45) ሆኖ ለከፈለን አካል ተመላሽ ሆኖ ያርፈዋል። በእጁ ስንት ገባ? 10,872 (አስር ሺህ ስምንት መቶ ሰባ ሁለት) ሆኖ አረፈው። አስቡት አሳይቶ መንሳት አይሆንም? ብዙ የተወራለት ደሞዝ ጭማሪ ትርፉ በነጋዴዎች የባሰ መመዝበርና ከድጡ ወደ ማጡ ይሆነዋል። እሽ እንቀጥል...።
የሚደንቀኝ ፖለቲከኞቹ ሳያውቁት የሆነ ክስተት አይደለም። የቲኦቲን ጉዳይ ሰምታችኋል። ቅድሚያ ከ2% ወደ 15% አስረው ይህን አስከተሉት። የህዝቡ በተለይ የደሞዝተኛውን ኑሮ ለማሻሻል ያለመ ሳይሆን በዘዴ የተቀመረ ለፖለቲካ አላማ ስኬት ሐምሳ ዜና የተሰራለት መንግስታዊ ሿሿ መሆኑ ልብ ይሏል።
እንቀጥል....
በቀድሞው ደሞዝ 13,998 የተጣራ በእጅ የሚገባው 10,998 አከባቢ ነበር። በአዲሱ ደግሞ 14,412 ልዩነቱ 3600 አከባቢ ነው። እሱንስ ማን አየብን የሚል አይጠፋም! ከዶሮው ሲባጎው በለጠ ከጥቅሙ ጉዳቱ በዛ። ዜናው ወከባና ግርግር አበዙ። የተጨመረው 3600 በዜናው ምክንያት ከሚከተለው ከፍተኛ የዋጋ ንረት አንፃር ነጌቲቭ ላይ ማረፉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።
ይቀጥላል...

Photos from ሀገርኛ ቲዩብ - Hagergna Tube's post 02/10/2025

መንግስት ደሞዝ ጨመረ? ኢኮኖሚስት ባልሆንም
ጭማሪ የተባለው የመንግስትን እንጅ የደሞዝተኛውን ችግር የሚቀርፍ አይመስለኝም ለምን እንበል።
ማሳያ 1
ደሞዙ 13,998 የነበረ ሰው በአዲሱ ጭማሪ 25,285 ሆነ። ደስ አይልም? እጥፍ በሉት። ነጋዴው፣ አከራዩ ወዘተ ደስታ ደግሞ ይለያል። ጭማሪያቸው እጥፍ ድርብ ይሆናል። (በቅርቡ እንኳን የሽንኩርት ዘይትና ቲማቲም ዋጋ ጭማሪው ያስተዛዝበናል።) በፐርሰንት ስንት እንያዝበት?...
ደሞዝተኛውስ?
ብሩን ሊወስድ ሲሄድ የስራ ግብር ከ25% ወደ 35% ፐርሰንት አድጓል። ይለዋል። ጋሽ ጡረታም 7% ፐርሰንት አለሁ ይለዋል። ለሸመታ ስትወጣ በድጋሚ እንደነጋዴው የማይመለስልህ (የቫት ተመላሽ) የማይደረግለትን 15% ወዬ ይለዋል። ወይኔ በላቸው!
እንደምረው
የስራ ግብር 35%
ጡረታ 7%
ቫት 15%
ወቸው ጉድ የደሞዝተኛው ደሞዝ 57% (14,412.45) ሆኖ ለከፈለን አካል ተመላሽ ሆኖ ያርፈዋል። በእጁ ስንት ገባ? 10,872 (አስር ሺህ ስምንት መቶ ሰባ ሁለት) ሆኖ አረፈው። አስቡት አሳይቶ መንሳት አይሆንም? ብዙ የተወራለት ደሞዝ ጭማሪ ትርፉ በነጋዴዎች የባሰ መመዝበርና ከድጡ ወደ ማጡ ይሆነዋል። እሽ እንቀጥል...።
የሚደንቀኝ ፖለቲከኞቹ ሳያውቁት የሆነ ክስተት አይደለም። የቲኦቲን ጉዳይ ሰምታችኋል። ቅድሚያ ከ2% ወደ 15% አስረው ይህን አስከተሉት። የህዝቡ በተለይ የደሞዝተኛውን ኑሮ ለማሻሻል ያለመ ሳይሆን በዘዴ የተቀመረ ለፖለቲካ አላማ ስኬት ሐምሳ ዜና የተሰራለት መንግስታዊ ሿሿ መሆኑ ልብ ይሏል።
እንቀጥል....
በቀድሞው ደሞዝ 13,998 የተጣራ በእጅ የሚገባው 10,998 አከባቢ ነበር። በአዲሱ ደግሞ 14,412 ልዩነቱ 3600 አከባቢ ነው። እሱንስ ማን አየብን የሚል አይጠፋም! ከዶሮው ሲባጎው በለጠ ከጥቅሙ ጉዳቱ በዛ። ዜናው ወከባና ግርግር አበዙ። የተጨመረው 3600 በዜናው ምክንያት ከሚከተለው ከፍተኛ የዋጋ ንረት አንፃር ነጌቲቭ ላይ ማረፉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።
ዝርዝሩን ይዤ ቀርባለሁ... ከተስማማችሁ 2 ቁጥርን ፃፉ

14/12/2023

| እያሉ እናክብር| እንዳንቆጭ
| ዘውትር ሐሙስና እሁድ
|ባለውለታዎቻችን_የት_በምንሁኔታ_ውስጥ_ናቸው?|
አንድ ማሻሻል ያለብን ጉዳይ አለ። ሰው በህይወት እያለ ላበረከተው አስተዋፅኦ ክብር፣ እውቅናና ምስጋና ከማቅረብ ይልቅ፤ ሲለዩን ስለማንነታቸው የመጎሰም ልማድ ነው። ይህ ለተለየን ሰው ምን ፋይዳ አለው?
ይህ ማህበራዊ ሚዲያ ከተቋቋመ ጀምሮ የሰሩትን ማመስገን፤ የሚሰሩትን ማበረታታት፣ የመሳሰሉ መልካም እሴቶችን ለማዳበር ጥረት ያደርጋል። ሁሉም በፈጣሪና በናንተ ቀናነት ተሳክቶ ብዙዎችን አፍርተናል።

በስራቸው ሃገርን፣ ትውልድን እና ተቋማትን የታደጉ እድሜና ህመም ገድቧቸው በየቤታቸው የከተሙ ባለውለታዎችን በልጅ ወግ ልንጎበኝ፣ ታሪክና ተሞክሯቸውን ልንዘክር፣ ከወዳጆቻቸው ጋር ለማገናኘትና ዋጋቸው ምንኛ ታላቅ እንደሆነ ለማሳየት በሚል የመጀመሪያ ዙር የምስጋና ፕሮግራም አሰናድተናል።
አዎን የሰራ ሲከበር፣ ለራስ ደስታን፣ ለቤተሰብ ኩራት ለሚሰራ ትውልድ መነሳሳትን ይፈጥራልና አብራችሁን ስለሆናችሁ ከልብ ለማመስገን እንወዳለን።
የመጀመሪያዎቹን 30 ባለውለታዎች ከዚህ ቀደም ከናንተ ባገኘነው ጥቆማ መሰረት በማድረግ እኛም ከተለያዩ ምንጮች ባሰባሰብነው መረጃ በህይወት ያሉ አባትና እናቶች ተመርጠዋል። ይሁን እንጅ በከተማችን በርካታ ባለውለታዎች ከተለያየ መስክ በመኖሩ የመጀመሪያው ዙር እንዳበቃ በሁለተኛው ዙር የሚካተቱ ይሆናል።
እነማን የሚለውን እና ታሪካቸውን ጭምር በቅርብ ቀን (ታህሳስ 7 እሁድ) ወደናንተ የምናቀርብ ይሆናል።
ለዚህ ዝግጅት በገንዘብ፣ በሐሳብ፣ መረጃ በመስጠት አብረውን ለነበሩ እናመሰግናለን። እንዲሁም በቤታቸው ስንሄድ አላማችንን ተረድተው በክብር ላስተናገዱንና ታሪካቸውን ለትውልድ በማጋራት ለተባበሩን የባለውለታዎቻችን ቤተሰብና ባለውለታዎቻችንን ከልብ እናመሰግናለን።
ይህን እቅዳችንን ስንነግራቸው በባህር ማዶ ኑሯቸውን ያደረጉት (ፍቅሩና ጓደኞቹ) ቅን የከተማችን ልጆች የዛሬ አመት ነበር አፋጣኝ ምላሽ የሰጡን። እኛም እነዴት መስራት እንዳለብን ከእናንተም ከአዋቂ አባቶችም ባገኘነው መረጃ ብንሰናዳም ወቅቱ አልፈቀደም ነበር። በዚህ መሐልም ጥቂት የማይባሉ በድንገት ተለይተውናል። አሁንም አልረፈደምና ቀኑ ደርሶ የመጀመሪያ ዙር 30 በህይወት ያሉ ባለውለታዎቻችንን ቤት ለቤት በመሔድ አክብሮታችንን በመላ የከተማችን ነዋሪ ስም እናበረክታለን። ታላላቆቻችንን ጠርተን ሳይሆን እኛው በቤታቸው በድንገት እንከሰታለን።
ውድ የሐዋሳ ትዝታ ቤተሰቦች ለዚህ ዝግጅት ስምረት በሐሳብ፣ ስጦታዎችን በማቅረብ እንዲሁም ፍቅርና ምስጋናዎቻችንን ለማቅረብ አብራችሁን ትሆኑ ዘንድ በድጋሚ ለማስታወስ እንወዳለን። አዎን ፍቅራችንን ዛሬ እንግለፅ፤ እንዳንቆጭ!
ለመሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም አብራችሁን ለመገኘት የምትፈልጉ ቅን ልቦች በኢንቦክስ አናግሩን።
የመጀመሪያው ጉብኝት የፊታችን እሁድ ይጀመራል!
|በነገራችን ላይ ከዚህ በታች የምትመለከቱት ምስል የማን ይመስላችኋል?|
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!

Photos from ሀገርኛ ቲዩብ - Hagergna Tube's post 01/06/2023

#ጠለፋ 21ኛው ክፍለ ዘመን
ሰዎች ጠለፋ ማለት አንድ ሰው የፈለጋትን ሴት ያለ ፍላጎቷ በኀይል ይዞ መኮብለል ማለቴ መፈርጠጥ ነው። እኔ በስራ አጋጣሚ በኖርኩባቸው የሐገራችን ገጠራማ ቦታዎች (መምህር እይደመሆኔ) ጠለፋ ኖርማል ነው። የአንድ የ6ኛ ክፍል ተማሪ ከክላስ ስትጠፋ ተጠልፋ መሆኑ ይነገርካል። ግን የሚጮህላቸው የለም።
ጠለፋ በሁለት ይከፈላል። አንደኛው ወዶ መጨለፍ ነው። ይህ ልጅትና ልጁ ከውጭ ተስማምተው ብዙ ደረጃዎችንም አልፈው ቤተሰብ ግንኙነታቸውን የማይፈቅደው ከሆነ፣ ወይም እርግዝና ከተከሰተ ነውሩን ለመሸፈን ሲባል ተነጋግረው አራጋቢ ተሰናድቶ ትጠለፋለች።
ሁለተኛው ደግሞ ተገዶ መጠለፍ ነው። ይህ ስሙን የሚወክል ነው። ልጅት ጠላፊውን ላታውቀውም ልታውቀውም ትችላለች። ወይ ጠይቋት እምቢ ብላለች ወይ ጭራሽ መፈጠሩን አታውቅም። ልጁ ቀን አመቻችቶ ተባባሪ ጀሌዎቹን ከነመጫኛውና አራጋቢው ከሰናድቶ ይዞ መፈርጠጥ/መኮብለል ነው።
በሁለቱም ጠለፋዎች በሽምግልና ህጋዊነቱ ይመሰከራል🤔 ልጅት ተጠልፋ በማገጥማት ተገዶ ደፈራ እንድታረግዝ ለወራቶች በመቆየቷ አማራጯ የሚሆነው ያልወደደችውን ሰው፣ አስገድዶ ደፍሮ ያስረገዛትን ግለሰብ ባሏ አድርጋ እንድትቀበል ትገደደዳለች። ይህ ከባድ የአስገድዶ መድፈር ወንጀልም ጭምር ነው!

ከሰሞኑ ተጠለፈች የተባለችው ወይዘሪት ፀጋ በሁለተኛው የጠለፋ አይነት ሊመደብ የሚችል ነው። በጣም ኋላ ቀር ተግባር።

ጠለፋ! በፍቅር ማሸነፍ የከበደው ሰው የጉልበት እርምጃ ነው። ጡንቻ፣ ስልጣን እና እድሜ ቀን በሔደ ቁጥር የሚሽቆለቆሉ ኩነት/አውዶች ናቸው።
ሰውን በጉልበት የራስህ ለማረግ ከወሰንክ ስለነገ ማሰብ የተሳነህ ነህና ከንቱ ህልምህ በጊዜ ይረግፋል።
ሐገራችን በአደገኛ ሁኔታ ውስጥ ስለመሆኗ ምሳሌ ጠቅሶ ማስረዳት አይጠበቅብኝም። ሰው ኑሮ ከብዶታል። የዋጋ ግሽበት አንገሽግሾታል! ከሁሉ የላቀው ግን ቢበላም ባይበላም ጎኑን የሚያሳርፍበትን ተነጥቆ ረሐቡን ዘንግቷል። የሰው ልጅ የመኖር ህልውናው አደጋ ውስጥ መግባቱ ቀላል ሁኗል። በየእለቱ ሰዎች እየሞቱ መሆኑን በዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ የሚዘመር ሐቅ ነው። ተላምደነው ስክሮል ለማድረግ ከልከበደንም።
ስለ ችግሩ አልያም ችግር የፈጠረውን ሳይሆን "የማን ብሔር ነው?" የሚለው ዋናው የጭንቀታችን አካል ከሆነ ሰነበተ። ስለሞተው ቸል ብለን እንቅፋት ስለመታው አብልጠን እንጨነቃለን።
አንጨነቅ አይደለም! እንጨነቅ። ግን ጭንቀታችን "ተጨንቀዋል" ለመባል ብቻ ሳይሆን ለእውነተኛ ስሜታችን ይሁን። ይህን ለማለት ያነሳሳኝ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ሲተላለፉ ከነበሩት የበርካቶች ሞትና መፈናቀል ገዝፎ ስለ አንዲት እህታችን ወ/ት ፀጋ የዘነበው የሚዲያ ማዕበል የተሰማኝን በውስኑ ለመጥቀስ ብዬ ነው።
በዚህ ዘመን ጥልፊያን የምደግፍ አይደለሁም። በጣም አሳፋሪ ተግባር ነው። ወንጀለኞቹም ታድነው ለፍርድ መቅረብ እንደሚገባቸው አምናለሁ። ጠለፋ በገጠር አከባቢ እንደድሮው ውሐ ለመቅዳት የወጣችን ሴት ጫካ ጠብቆ እንስራዋን ሰብሮ ተሸክሞ መጥፋት የሚመስለው አለ። ይልቅ ዘምኗል። ተቀጣጥሮም መጠላለፍ ከተጀመረ ሰንብቷል። ነገር ግን ያለ ውሏ ለሰርግ ሽርጉድ እያለች ያለችን እንስት በድንገት ጠልፎ መኮብለል ለሱስ ምን ሊበጀው? ሊያገባት ያለው ሰው ቦታ ሁነን እናስብ... ልጅቷ እህታችን ብትሆን... ብለን ስናስብ ህመሙ ይገባናል። ወዶ መጠለፍና ተገዶ መጠለፍ ለየቅል ነው። በከተማ ሲሆን ግን እንግዳ ነውና ሊቆም ይገባዋል።
ይህ እንዳለ ሁኖ ጉዳዩን የከተማው አጠቃላይ ገፅታ አስመስሎ ብሔር ላይ ፊጥ ማለቱ ተገቢ አይመስለኝም። ሰውዬው "ጠላፊው" የከንቲባው ጋርድ እንጅ ወንድም ወይ ምክትል ከንቲባ አይደለም። እያሰብን እንጅ ወገን!
ሐዋሳ ለፍቅር ለሰላም ለአብሮነት የሚደርሳት እንጅ የሚበልጣት ያለ አይመስለኝም። የግለሰብ ወንጀል የከተማው ህዝብ ወንጀል፤ የግለሰቡ ብሔር በሙሉ ወንጀለኛ፤ ግለሰቡ የሚሰራበት ከተማ በሙሉ ደመ መራር አድርጎ ማራገቡ የሚያስተዛዝብ ነው። ከዚህ የባሰ ስንት ጣጣ በዝምታ እየታለፈ በዚህ ጉዳይ መረባረቡ "ሊበሏት የከጀሏትን ጅግራ ቆቅ ነች ይሏታል" ከሚል ጥርጣሬ ያደርሳል።
ለማጠቃለል ያህል የፀጋ ጉዳይ የበርካታ ሴቶች በተለይ በገጠር የሚኖሩ የለት ተለት ሰቆቃ ነው። ጠለፋን ለማስቀረት ውስጥ ድረስ መሰራት አለበት። ይሁን እንጅ የሐዋሳ ገፅታ አድርጎ ማራገብ ለልጅቷ ወይ ለወንጀሉ ከመንገብገብ ይልቅ በሰበብ ተነስቶ ጥላቻን እንደማንፀባረቅ ይቆጠራል።
ህግ፣ ህዝብና ከተማችን ይከበር! በስማ በለው እና በይሉኝታ ወሬ ማራገብም ይብቃ!

ዮ ዮ ጊፋታ! እንኳን ለመስቀልና ለወላይታ ዘመን መለወጫ በሰላም አደረሳችሁ| የሐዋሳ ትዝታ 22/09/2022

|ጊፋታ

ዮ! ዮ! ጊፋታ (የወላይታ ዘመን መለወጫ)
የወላይታ ብሔር በርካታ የማይዳሰሱ ቅርሶች ባለቤት ነው፡፡ ከእነዚህ ሀብቶች መካከል የብሔሩ ዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ አንዱ ነው፡፡ ጊፋታ የወላይታ ሕዝብ በኦሞ ወንዝ ተፋሰስ ቋሚ ኑሮ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሲከበር የቆየ፣ ከማንኛውም ባህላዊ እምነትም ሆነ ዘመናዊ ኃይማኖትና የአምልኮ ሥርዓት ጋር ምንም ግኑኝነት የሌለው የዘመን መለወጫ ክብረ በዓል ነው፡፡ ጊፋታ ማለት ባይራ(ታላቅ)፣ መጀመሪያ፣ እንደ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ጊፋታ ማለት መሻገር ማለት ነው፡፡ ይህም ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገር የሚለውን ይገልጻል፡፡
ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል ነው ተብሎ ይታመናል፡፡ የወላይታ ብሔር የራሱ የሆነ የዘመን መቁጠሪያ/ካሌንደር አለው፡፡ በወላይታ የዘመን አቆጣጠር ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡
በበዓሉ “Gifaata Gazzee Abuuna Gaylle” ተብሎ ይዘፈናል፡፡ ይህም የበዓሉን ታላቅነት ለመግለጽ ነው፡፡ አሮጌው ዓመት እየተገባደደ ሲሄድ በንጉሱ(በወላይታ ንጉስ) አማካሪዎች አማካይነት የዘመን ቆጠራ ባለሙያዎች ወደ ቤተ መንግሥት ይጠሩ ነበር፡፡ ቆጣሪዎቹ ከዚያም ሌሊት ሌሊት እየወጡ የጨረቃን ኡደት መነሻ ለማወቅ የጨረቃን አራት ክፍሎች ማለትም /ፖኡዋ፣ ጡማ፣ ጤሯ፣ ጎባና/ በየትኛው ክፍል እንደሚውል የማወቅ ስራ ይሰራሉ፡፡ በዚህም የዓመቱን የቆጠራ ምልክቶች ይዘው መጥተው የሙሉ ጨረቃዋን ኡደት ተመልክተው ለንጉሱና ለአማካሪዎቹ ያበስራሉ፡፡
የጊፋታ በዓል ቅድመ ዝግጅት፡- የጊፋታ በዓል ከሌሎች በዓላት በተለየ የረዥም ወቅት ዝግጅት ይደረግለታል፡፡ በጊፋታ ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻ አላቸው፡፡ የአባወራዎች ተግባር፡- የጊፋታ በዓል ዝግጅት የሚጀምረው በቁጠባ/”ቆራጱዋ” ነው፡፡
ይኸውም በዕርዱ ዕለት በእርጥብ ቆዳ ላይ የቀጣዩ ዓመት ቁጠባ አንድ ተብሎ ይጀመራል፡፡ ሌላው በጊፋታ ዕለት ወንዶች በሬ ከታረደ በኋላ ከሁሉም የሥጋ ዓይነት፣ ከየዓይነቱ ትንሽ ትንሽ ቆርጠው በባለተራው ቤት ውስጥ በተዘጋጀው ማባያ፣ ማለትም ቆጮ፣ ቂጣ፣ ዳታ በርበሬ ጋር ተቃራጮቹ፣ የ”አሙዋ” አባላት በጋራ ይቋደሳሉ፡፡
ይህም የአንድነትና የፍቅር ማብሰሪያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሌላው በአባቶችና በወንድ ልጆቻቸው የሚከናወን የአካባቢ እድሳት ሥራ ነው። ይህም በወላይታ ብሔር አዲስ ዓመት የመታደስ ምልክት ስለሆነ ሰዎች በግላቸው የቤታቸውን የሳር ክዳን በአዲስ ሳር መቀየር፣ በቤት ውስጥ እና ከውጪ ደግሞ በቤቱ ዙሪያና በአካባቢው የሚገኙ ቆሻሻዎችን በማጽዳት በዓሉን ይቀበላሉ፡፡ እነዚህ ከአባወራ ተግባራት በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የእማወራዎች ተግባር፡- እማዎራዎች ለጊፋታ በዓል ከሚያደርጓቸው ዝግጅቶች የመጀመሪያው ”ኦይሳ ቆራጱዋ” ወይም የቅቤ ዕቁብ ሲሆን ይህም ዋነኛው የእማወራ ተግባር ነው።
በዚህም መሠረት ዓመቱን ሙሉ ለጊፋታ የቆጠቡትን ቅቤ ‘‘በቦቦዳ’’ አጥቢያ ሰብሳቢያዋ ቤት ተሰብስበው የቅቤ ቡና ከጠጡ በኋላ የየድርሻቸውን ተከፋፍለው ይወስዳሉ፡፡ ጊፋታ ካለፈ በኋላም ለቀጣይ ዓመት በየሳምንቱ ቁጠባውን ይቀጥላሉ፡፡ እናቶች በሰኔ ወር መጨረሻ አካባቢ ለተለያዩ ባህላዊ ምግቦች ማለትም ለቆጮ፤ ‘‘ለሙቹዋ’’፤ ‘‘ለባጪራ’’፤ የሚሆኑ የደረሱ እንሰቶችን የመፋቅ ዝግጅቶች ያደርጋሉ፡፡ እንሰት መፋቅ የእናቶች ተግባር ቢሆንም የሚፋቀውን እንሰት መርጦ ማዘጋጀት ግን የአባወራው ድርሻ ነው፡፡
በአባወራው ተለይቶ የተሰጠውን እንሰት ጓደኞቿንና ሴት ልጆቿን በማስተባበር መፋቅና ማዘጋጀት የእማወራዋ ተግባር ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የወላይታ ዳታ በርበሬ ያዘጋጃሉ፤ በዓሉ ሲቃረብ ያዘጋጃሉ፡፡ የጊፋታ በዓል ሲቃረብ የሚውሉ ገበያዎች ከእርድ ቀን ቀደም ብሎ የጊፋታ በዓል መቃረቡን የሚያበስሩ በብሔሩ አባላት የሚታወቁ ገበያዎች አሉ፡፡ እነሱም “ሃሬ ሀይቆ”፤ ”ቦቦዶ” እና “ጎሻ” በመባል የሚታወቁ ሲሆን ሌላው ደግሞ “ ቃኤ ጊያ “ ይባላል፡፡
1. ሃሬ ሀይቆ ”Hare hayiqo”፡- ቀጥተኛ ትርጉሙ የአህያ መሞቻ እንደ ማለት ሲሆን ይህም በወቅቱ አህዮች ያለባቸውን ድካም ለማሳየት ነው፡፡ በዓሉ እየተቃረበ በመጣ ቁጥር ሁሉም ሰው ለበዓሉ ዝግጅት እህልና ሌሎችን ቁሳቁሶች በአህዮች እየጫነ ወደ ገበያ ያወጣል፡፡ ይህንን ጊዜ ከሌላዉ የሚለየዉ አንድ አህያ በቀን ከሦስት ጊዜ በላይ እየጫነ ወደ ገበያ መመላለሱ ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም ይህ ወቅት በሕብረተሰቡ የጊፋታ በዓል ዝግጅት ሸመታና ሽያጭ የሚጀመርበት ነው፡፡
በመሆኑም ከሌሎች ገበያዎች በጣም የተረጋጋ እንቅስቃሴ የሚታይበት ገበያ ነው፡፡ 2. ቦቦዳ “Bobooda”፡- ሁለተኛው በሃሬ ሀይቆ ሳምንት የሚውለው ገበያ ሲሆን ይህ ገበያ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ በአዳዲስ ነገሮች የተሞላ ገበያ ነው፡፡ በዚህ ገበያ ገበያተኛው ቀድሞ ወደ ገበያ የሚመጣበትና በአብዛኛው ሴቶች የሚበዙበት ነው፡፡ ሴቶች ለበዓሉ የሚያስፈልጋቸውን የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች የሚሸምቱበት ሆኖ በዚህ ገበያ የሸክላ ዕቃዎች ሽያጭና ግዥ በእጅጉ ይደራል፡፡ ከዚህም ሌላ በዓሉ እየተቃረበ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ ሰዎች ባር ባር(ፍርሃት ፍርሃት) ይላቸዋል፡፡
የፍርሃቱ ምንጭም ከበዓሉ ትልቅነትና ስፋት አንጻር ምን ይጎልብኝ ይሆን በማለት ቤተሰቡ በሙሉ በፍርሃትና በጭንቀት የሚዋጥበት ወቅት ስለሆነ ነው፡፡ 3. ጎሻ “Gooshsha”፡- ሶስተኛው ሳምንት ገበያ ጎሻ የሚባል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙ እብደት እንደ ማለት ነው፡፡ ሰዎች ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ከንጋቱ 11፡30 ሰዓት ጀምሮ ወደ ገበያ ይሰበሰባሉ፡፡
በገበያ ውስጥ እርስ በርስ የሚገፋፉበት፣ የሚገጫጩበት፣ እንደ እብድ የሚይዙትን የሚጨባጡትን የሚያጡበት ፣ ነገር ግን የማይቀያየሙበት የገበያ ውሎ ነው፡፡ ቃኤ ጊያ፡- ሌላውና የመጨረሻው ፣ ማሳረጊያው ፣ ‘‘ቃኤ ጊያ የሚባለው ሲሆን ይህም በእርዱ ቀን፣ እሁድ ዕለት ማለትም ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ከሌሊቱ 10፡00 እስከ ጧቱ 2፡00 ሰዓት የሚቆም ገበያ ነው፡፡
በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልግ ሆኖ ድንገት የተረሳ ነገር ካለ ይሸመታል፡፡ ለእርድ እሁድ 15 ቀናት ሲቀሩት ጀምሮ ፣ በበዓሉ ወቅትና ከበዓሉ በኋላ በሚኖሩት የመዝናኛ ሳምንታት ምንም ዓይነት ሥራ ስለማይሠራ ለከብቶች የሚበቃ ሳር በወንድ ልጆች ይታጨዳል፡፡
በአሞሌ ጨው የሳር ድርቆሽ ይዘጋጃል፡፡
ከዚህም ሌላ እንጨት በአባቶችና በታላላቅ ወንድ ልጆች ይፈለጣል፤ የቆጮ ቆረጣ በእናቶችና በሴት ልጆቻችው ይደረጋል፤ በድሮ ጊዜ ማሽላና በቆሎ በባህላዊ ወፍጮ ተፈጭቶ ዱቄቱ ይዘጋጃል፤ ዳታ በርበሬ የመለንቀጥ ሥራ በሴቶች ይሠራል፡፡ የጎሻ ሳምንት እየተገባደደ ሲመጣ የሚውለው ሀሙስ “ኮሰታ ሃሙሳ”(ሻጋ ጋላሳ) ይባላል፡፡ ትርጉሙ የእንኩሮ ሃሙስ ማለት ሲሆን ዓርብ ሱልኣ አርባ(ብዛ ጋላሳ) ይባላል፡፡
ይህም በየቤቱ ለቦርዴ የሚሆን እህል የሚዘጋጅበት ሲሆን ለሆድ ማሟሻ ጎዳሬ “Boynaa Cadhdhiyaa” እና ከቦዬ የሚዘጋጅ “Boyinaa Pichaata” የሚበላበት ዕለት ነው፡፡ ቅዳሜ ፣ የባጪራ ቅዳሜ “Baaccira qeeraa” የሚባል ሲሆን በዚሁ ዕለት ለእሁድ(የእርድ) ዕለት ሆድ ማለስለሻ ምግቦች ይበላሉ፡፡ የበዓሉ አከባበር፡- የዕርድ ዕለት ጧት ወፍ እንደተንጫጫ በቤተ መንግሥት 12 ጊዜ ነጋሪት ይጎሰማል፡፡

በዚህን ጊዜ ከሁሉም የወላይታ አካባቢዎች የ ‘‘አላና’’ ኃላፊዎች ይሰበሰባሉ፡፡ የነጋሪቱን ድምጽ እንደሰሙ በሬ አራጆች ሥራቸውን ይጀምራሉ፡፡ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ የአላና ኃላፊዎች ወደ ግብር አዳራሽ ይገባሉ፡ቀጥሎም የወላይታ ባህላዊ ንጉስ በክብር ወደ አዳራሹ ከገቡ በኋላ ለሰማይ አምላክ ምስጋና ይቀርባል፡፡ ለበዓሉ የተዘጋጀውን ቦርዴ ንጉሱ ከቀመሱ በኋላ እርስ በርስ፣ የፍቅር መግለጫ በሆነው የ”ዳጌታ“ ሥርዓት ቦርዴውን ይጠጣሉ፡፡ ለበዓሉ የታረደው ሥጋ በዳታ በርበሬ፣ በቂጣና በጎዴታ ቆጮ ይቀርባል፡፡ ሁሉም በልተውና ጠጥተው ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ፡፡
ይህም በብሔሩ የጊፋታ “ቃይዴታ” ሥርዓት የሚባል ሲሆን የተጣላ የሚታረቅበት፣ ሰዎች ፍቅራቸውን ከአንድ ማዕድ በመቁረስ የሚያድሱበት ፣ የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ ነው፡፡ በዕለቱ የበሬ ሥጋ በጋራ የሚያርዱ የ”አሙዋ” አባላት በየቤታቸው ጠዋት ሙቹዋ ወይም ባጭራ በቅቤ ቡና ይቀምሱና ቢላዋና ቅርጫት አስይዘው ወንድ ልጆቻቸውን ወንድ ልጅ ከሌላቸው ሴት ልጆቻቸውንይዘው በሬ ወደሚታረድበት ደጃፍ ይሄዳሉ፡፡
የበሬውን ቆዳ ከገፈፉ በኋላ መጀመሪያ ፊኛው ወጥቶ ለልጆች ይሰጣል፡፡ ልጆች ሥጋው ታርዶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፊኛ በእግራቸው እየመቱ ይጫወታሉ፡፡ በሬ በሚታረድበት ቤት ደጃፍ የተሰበሰቡ ሰዎች “ባጭራ” ወይም “ሙቹዋ” ይበላሉ- ከቅቤ ቡና ጋር ፡፡ ባህላዊ መጠጥም ይቀርባል፤ እነዚህ ሰዎች በሬውን በጋራ ያርዳሉ፤ በሬው እየታረደ እያለ ከሁሉም የሥጋው ብልት ይቆረጥና የ”አሙዋ”አባላት የፍቅር መግለጫ ነው ተብሎ ስለሚታመን በጋራ ይቋደሳሉ፡፡
በመቀጠልም ዕጣ ጥለው ሥጋውን ከተከፋፈሉ በኋላ ለሚቀጥለው ዓመት ጊፋታ በዓል በሬ መግዣ ተቀማጭ በታረደው በሬ ቆዳ ላይ መጣል ይጀምራሉ፡፡ ይህ የቁጠባ ሥርዓት ከ”ጎሉዋ ኢጌታ” በኋላ በየሳምንቱ እስከ ዓመቱ መጨረሻ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የአመጋገብ ሥርዓት፡ የግፋታ ዕለት ከንጋት ጀምሮ ቤት ውስጥ የተለያዩ ዝግጅቶች ይደረጋሉ፡፡ እናቶች ከተዘጋጀው ዳታ ለዕለቱ የሚበቃውን ከፍለው ቅቤ በመጨመር በእሳት ያንተከትካሉ፣ ቂጣ፣ ቆጮ ያዘጋጃሉ፡፡
ከዚህም ሌላ “ኤርጊያ” የሚባለው ያልተበሳሳ ኮባ ቅጠል ተቆርጦ ሳሎን ውስጥ መሬት ላይ እንዲዘረጋ ይደረጋል፡ ፡ አባት ካመጣው ሥጋ መካካል በጥሬ የሚበላውን በማዘጋጀት በቢላዋ እየቆረጠ በኮባው ቅጠል ላይ ዙሪያውን ያስቀምጣል፡፡ ቆጮና ቂጣም በተመሳሳይ ሁኔታ ይደረጋል፤ በመሃል በመሃሉ ዳታ በርበሬ በወጪት ተደርጎ ይቀመጣል፡፡ ማዕዱ ከቀረበ በኋላ ከዓመት ዓመት በሰላም ያሸጋገረው አምላክ እንደየአምልኮ ስርዓቱ ይመሰገናል፡፡
አባት ከሁሉም በፊት ከተዘጋጀው ማዕድ እናትን ያጎርሳል፡፡ በመቀጠልም በማዕዱ ዙሪያ የተቀመጡትን ልጆች ሁሉ ያጎርሳቸዋል። ቀጥሎም የቤተሰቡ አባላት የየራሳቸውን መመገብ ይጀምራሉ፡፡ የጉሊያ አቀጣጠል ሥርዓት ፡- ጉሊያ የወላይታ ብሔር የጊፋታ በዓልን በእሳት ብርሃን የሚያከብርበት ሥርዓት ሲሆን የሰኔ “ኩሻ” ወር ማብቂያ ሦስት ቀናት ሲቀሩት የሠፈር ወጣቶች ብዙ አገልግሎት የማይሰጡ እንጨቶችን ከጫካ ውስጥ ቆርጠው እየጎተቱ አንድ ቦታ ይከምራሉ፡፡ የተከመረው እንጨት ለጊፋታ በዓል ሁለት ሳምንት ሲቀረው እንዲቆም ይደረጋል፡፡
የተከመረው እንጨት የጊፋታ ወር መጀመሪያ ጨረቃ በታየች አራት ቀናት መካከል በሚውለው እሁድ (ሹሃ ወጋ) እርድ ተከናውኖ ሥጋ በተበላበት ማታ የሚከበር ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ማታ አንድ ሰዓት አካባቢ የሠፈር ወጣት ወንዶችና አባቶች ከየቤታቸው ቺቦ(ጢፋ) በመያዝ በጉሊያው ዙሪያ ይሰበሰባሉ:: በአካባቢው ታዋቂና ታላቅ የሆነ ሰው ጉሊያውን በእሳት እንዲለኩስ ይጋበዛል፡፡
የእርድ ዕሁድ ማግስት ሰኞ ታማ ሰይኖ ይባላል፡፡ ጥሬ ትርጉሙ የእሳት ሰኞ ማለት ነው፡፡ ይህም እሁድ ዕለት በሁሉም ሰው ቤት እስከ ሌሊት ድረስ እሳት ስለሚነድ በነጋታው ሰኞ ማንም ሰው ወደ ጎረቤቱ እሳት ለመጫር አይሄድም፡፡ ከግፋታ ቀጥሎ የሚመጣው ሁለተኛው ቀን ማክሰኞ “ጪሻ ማስቃይኖ” ይባላል፡ ፡ ይህም የመልካም ምኞት አበባ ስጦታዎች የሚለዋወጡበት ቀን ነው፡፡
በዚሁ ዕለት የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ “ኮርማ ጪሻ” ተብሎ የሚጠራው ነጭ አበባ ፣ እሱም ካልተገኘ ደግሞ አደይ አበባ የተባለው የአበባ ዓይነት ተይዞ እንኳን አደረሳችሁ! ጊፋታ ዮዮ! እየተባለ አማች፣ አበልጅ ቤት እንዲሁም ደግሞ እንደየቅርበቱ ዘመድ አዝማድ ቤት እየተኬደ መልካም ምኞት ይገለፃል፡፡ የአበባ ስጦታው ለቤቱ አባወራ የሚሰጥ ሲሆን ፣ አባወራው በቀኝ እጁ አበባውን ይቀበልና ከምሶሶ ጋር ያስራል፡፡
እነዚህ ሁለት ዓይነት አበቦች በጊፋታ ወቅት ብቻ የሚፈኩ አበቦች ስለሆኑ አባወራው አበባዉን ከተቀበለ በኋላ ጊፋታ እናንተን አይቁጠር ፣ እናንተ ጊፋታን ቁጠሩ፣ “Gifaatay Inttena Qoodoppo Initte Gifaataa Qoodite” ከዓመት ዓመት በሰላም ያድርሳችሁ በማለት ይመርቃሉ፡፡ ስጦታ አምጪዎቹ የሚበላና የሚጠጣ ነገር ተጋብዘው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ በነጋታው ‘‘ጋዜ ኦሩዋ /Gazze Oruwaa” ሲሆን ይህም ሰዎች አጠቃላይ ሀሳባቸውን ወደ መዝናኛ የሚያደርጉበት ሆኖ ታላቁ የጊፋታ ጨዋታ ጋዚያ” Gazziyaa”መድመቅ የሚጀምርበት ዕለት ነዉ፡፡
በዚህ በተከታታይ ለሁለት ሳምንታት በሚቆየዉ ጨዋታ የመንደሩ ወጣት ወንዶችና ወጣት ሴቶች በአካባቢው ታዋቂ ሽማግሌ ደጃፍ ተሰብስበው ወንዶች ‘‘ሃያያ ሌኬ ’’ እያሉ ትከሻ ለትከሻ ተቃቅፈው ሎሚ ከልጃገረዶች በመለመን ለትዳር የሚፈልጓትን የሚመርጡበትና የሚያባብሉበት፣ ሴቶችም እንደ አስፈላጊነቱ ምላሽ እየሰጡ የሚጫወቱት የጨዋታ ዓይነት ነው፡፡ ‘‘ከጋዜ ኦሩዋ’’ ጀምሮ ተቆጥሮ የሚመጣው ሶስተኛ ረቡዕ ‘‘ጎሏ ኦሩዋ /Gooluwaa Oru wa” ይባላል፡፡
ይህም ከአንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ የቆየው የበዓል ዝግጅትና አጠቃላይ የጊፋታ በዓል ሥነ-ሥርዓት አብቅቶ የሚሸኝበት ቀን ሲሆን ከበዓሉ ጋር ተያይዞ በነበረው የመዝናኛ ወቅት ምክንያት በሰዎች ዘንድ ስንፍና እንዳይገባ በማለት ሁሉም ችቦ እያቀጣጠሉ ለሚመጣው በዓል አምላክ በሰላም እንዲያደርሰው በመመኘት ጊፋታን ይሸኛሉ፡፡ ይህም የመዝናኛ የዕረፍት ወቅት አብቅቶ ወደ ሥራ የሚገባበት ወቅት በመሆኑ “Oru waappe Hepinttay Ofintta” ይባላል፡፡ ከዕሮብ በኋላ ዕረፍትና መዝናናት የሉም፤ ሥራ ተጀምሯልና ወደ ሥራ እንግባ እንደማለት ነው፡፡
ይህንን በዓል ከመላው ኢትዮጵያዊያን ጋር አብረው ለማክበር ጥሪ ያቀረቡት የወላይታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ሀብቴ በዓሉን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ከፌዴራል ባህልና ስፖርት: ቅርስ ጥናትና ጥበቃ፡ ከደቡብ ክልል መንግስት እና ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከወላይታ ዞን አስተዳደር ጋር በመሆን ብዙ ጥረት የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም የዘንድሮ ጊፋታ በዓል የሚከበረው መስከረም 14 የቋንቋና ባህል ስምፖዚየምና በሩጫ ውድድር፣ በመስከረም 15 ዋናው የጊፋታ በዓል በደማቅ ይከበራሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የአካባቢው ተወላጆች ኑ በዓሉን በአንድ ላይ እናክብር ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
በደስታ ወጋሶ (ከወላይታ ዞን መ/ኮ/ መምሪያ)

ዮ ዮ ጊፋታ! እንኳን ለመስቀልና ለወላይታ ዘመን መለወጫ በሰላም አደረሳችሁ| የሐዋሳ ትዝታ ጊፋታ የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በአል ሲሆን የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች! የሐዋሳ ትዝታ ለመላው የወላይታ ህዝብና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ በመላው አለም ለምትገኙ እን....

22/09/2022

ይህችን ጀግና ገበሬ ስሟትማ😍

04/08/2022

የወንድ የዘር ፈሳሽን ቶሎ ማፍሰስ

ብዙ ጊዜ ይህ ክስተት የሚፈጠረው በግላዊ አልያም በጋራ ጭንቀት ውስጥ በሚገኙ ወንዶች ላይ ነው ይላሉ ጉዳዩ የሚገባውን ጥናት አድርገናል የሚሉ ባለሙያዎች።

ቶሎ የዘር ፈሳሽን ማፍሰስ እውቅና ያለው የጤና ችግርም ነው። ነገር ግን በህክምና ቋንቋ የተሰጠው ፍቺ ግልጽ ያልሆነ፣ አሻሚ እና ተጨባጭ የቁጥር መስፈርቶች የጎደለው ነው።

ይህ ደግሞ የህክምና ባለሙያዎች ጉዳዩን መርምረው አግባብና ትክክለኛ ነው ብለው የሚያምኑበትን የህክምና መንገድ ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ እጅግ ፈታኝና ግራ አጋቢ እንዳደረገባቸው ይናገራሉ።

እንግዲህ አንድ ወንድ በወሲባዊ ግንኙነት ወቅት የዘር ፈሳሹን ቶሎ የማፍሰስ ችግር በተደጋጋሚ ካጋጠመው ጭንቀት ውስጥ ሊገባ ይችላል። ምክንያቱም በወሲብ ደስታን አለማግኘት ዞሮ ዞሮ የጋራ የሆነውን ግንኙነት መጉዳቱና አደጋ ላይ መጣሉ አይቀርምና።

☑️ ምን ተሻለ?

በዚህ የጤና ችግር እየተፈተኑ ከሆነ በቅድሚያ ወደ ጤና ባለሙያ መሄድ የሚያስፈልግ ሲሆን እስከዚያው ድረስ ግን ከስር የተቀመጡትን ነገሮች በቤት ውስጥ በማድረግ ወሲባዊ ህይወትዎ ላይ የተሻለ ለውጥ ማየት ይችላሉ፡፡

💎 አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ

መደበኛ የሆነ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የዘር ፈሳሽን ቶሎ የማፍሰስ ችግርን ለመቅረፍ ምርጡ ዘዴ ነው።

ውሃ ዋና፣ ሩጫ፣ የኳስ ጨዋታ፣ ጂምናስቲክ ወ.ዘ.ተ እንደመፍትሄ የቀረቡ ሲሆን መደበኛ የሆነ እንቅስቃሴ ማድረግ የማይችሉ ከሆነ ደግሞ ዮጋ መሞከር ጥሩ አማራጭ ነው።

💎 አመጋገብን ማስተካከል

አንዳንድ የጤና ችግሮችን በምግብ ማከም እየቻልን ለምን ብለን መድሃኒት እንወስዳለን? ይህን ቀድሞ የዘር ፈሳሽንም ለማከም ወሲባዊ መነቃቃትን የሚያስከትሉ እንደ እንቁላል፣ የበግ ስጋ፣ ጥቁር ባቄላ የመሳሰሉ በአቅራቢያችን በቀላሉ የምናገኛቸውን ምግቦች መመገብ ይቻላል።

💎 ስነልቦናዊ መፍትሄዎች

ባለሙያዎቹ እንደሚሉት ከሆነ ብዙ ጊዜ ይህ በወንዶች ላይ የሚከሰተው ያለጊዜ የዘር ፍሳሽን የማፍሰስ ችግር በአእምሮ ጭንቀትና ውጥረትም ሊከሰት ይችላል።

አሉታዊ ሀሳቦችን ከአእምሮው ያስወግዱ የተረጋጋ የአእምሮ ሁኔታን ይፍጠሩ። ብሩህ የሆነ አመለካከት ይኑርዎት ለጭንቀት ቦታ አይስጡ። እንዲያ ካደረጉ ወሲባዊ ህይወትዎ ላይ የተሻለ ለውጥ ማየት ይችላሉ።

ምንጭ: healthline

መልካም ጤንነት!!

04/08/2022

✍ ?

👉👉የወሲብ ፊልም ከሱሶች መካከል የሚመደብ እና በሀገራችን እጅግ በጣም ብዙ ሰው የፖርኖግራፊ ተጠቃሚ እየሆነ ወይም በፖርኖግራፊ ሱስ እየተጠቃ ነው። ይህ ሱስ እንደሌሎች ሱሶች በግልጽ በሱሰኛው ላይ የማይታይ በመሆኑ እንዲሁም በማህበረሰባችን ውስጥ ስለ ጉዳዩ አሳሳቢነት በቂ መረጃ ስለሌለ የተጠቂዎች ቁጥር እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ ይገመታል።

👉👉 ማንኛውም የወሲብን ስሜት የሚቀሰቅሱ ወሲባዊ ታሪኮች፣ ፊልሞች፤ ፎቶግራፎች እንዲሁም የቃላት ልውውጥ የወሲብ ፊልም ይባላሉ። በአሁኑ ወቅት ሰዎች ወሲብ ፊልም ለማየት ለዚህ ከተዘጋጁ ልዩ ድህረ ገፆች ባሻገር ለዚህ አላማ ባልተዘጋጁ የማህበረሰብ መገናኛ ድህረ ገፆች ማለትም ቴሌግራም፤ ትዊተር፤ ፌስቡክ የመሳሰሉትን በመጠቀም ለፖርኖግራፊ ሱስ ተጋላጭ ይሆናሉ። በዘመናችንም ፖርኖግራፊ በቀላሉ ሊገኝ የሚችል መሆኑም ሱሱ እንደወረሽኝ እንዲዛመት አድርጎታል። ወሲብ ፊልም ሰዎችን በቀላሉ ሱሰኛ የማድረግ አቅም ያለው ሲሆን ሲጋራ፣ ጫት እና የተለያዩ ዕፆች ሊያደርሱት ከሚችሉት ጉዳት በላይ ከባድ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል በግልጽ ለማየት ተችሏል።

👉👉ስለ ወሲብ ፊልም ጥናቶች ምን ይላሉ?

ስለ ወሲብ ፊልም የተሰሩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ብዙውን ጊዜ ሰዎች ለፖርኖግራፊ ተጋላጭ የሚሆኑት ከ11 ዓመታቸው ጀምሮ ነው።በኢንተርኔት ውስጥ ከሚገኘው ወደ ግማሽ የሚሆነው መረጃ ወሲብ ፊልም ወይም ከወሲብ ፊልም ጋር ተያያዥ የሆነ መረጃ ነው።
በየቀኑ ኢንተርኔት ከሚጠቀሙ ሰዎች መካከል 25% የሚሆኑት ወሲብ ፊልም የሚመለከቱ ናቸው።

ከኢንተርኔት ላይ ከሚወርዱ ቪዲዮዎች መካከል 35% የሚሆነው ከወሲብ ፊልም ጋር የሚገናኙ ናቸው ። 34% የሚሆኑት የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሳይፈልጉት በማስታወቂያዎች በራሳቸው ብቅ በሚሉ ሌሎች መረጃዎች ምክንያት ለወሲብ ፊልም ይጋለጣሉ።

አለም ላይ ካሉ ድህረ ገጾች መካከል 12% የሚሆነው የወሲብ ፊልም ገጾች ነው።አለማችን ላይ ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያገኙ ሰዎች መካከል በወሲብ ፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉ ሰዎች ይገኙበታል። በሰሜን ኮሪያ በሐገሪቱ ውስጥ ወሲብ ፊልም ነክ የሆኑ ነገሮችን ማሰራጨትም ሆነ ማየት በሞት የሚያስቀጣ ነው።

👉👉 ሰዎች ለምን👉 አዘውትረው ይመለከታሉ?

1. ደስታን ፍለጋ

ለዚህ ጥያቄ ግልፅ የሆነውና የመጀመሪያው ምላሽ ሰዎች ማንኛውንም አይነት ፊልም እራሳቸውን ለማዝናናት እንደሚመለከቱት ሁሉ ወሲብ ፊልም የሚያነቃቃቸው እና ደስ የሚያሰኛቸው ነገር ከመፈለግ አንፃር ማየታቸው ነው። ከሰው መሰረታዊ ፍላጎቶች ውስጥ አንዱ ወሲብ እንደመሆኑ ሰዎች ይህንን ፍላጎት በተገቢው ሆነ ተገቢ ባልሆነ መልኩ ለማሟላት፤ በገሀዱ አለም እራሳቸው ያላደረጉትን ወይም የማያረጉትን ነገር ግን ስሜታቸው የሚፈልገውን ነገር አይተው በምናባቸው ተሳታፊ ለመሆን ፖርኖግራፊን ይመለከታሉ።

2. ጭንቀት/ድብርት

ብዙውን ጊዜ በድብርት እና በጭንቀት ውስጥ ያሉ ሰዎች በፖርኖግራፊ ሱስ የሚጠቁ መሆናቸውን ጥናቶች ያሳያሉ። በአብዛኛው በ ወሲብ ፊልም ብቻ ሳይሆን በሌላም የዕፅ ሱሶች የሚያዙ ሰዎች ሱስ የሆነባቸውን ድርጊት ደጋግመው እንዲያረጉ ሚገፋፋቸው ወሲባዊን ደስታን ለማግኘት ያላቸው ፍላጎት ሳይሆን ውስጣቸው ከሚሰማቸው የስሜት መዋዥቅ ማለትም ጭንቀት፣ ድብርት፣ ሀዘን፣ ፍርሃት እና ሀፍረት ለማምለጥ ነው።

3. ብቸኝነት

ብዙውን ጊዜ ብቸኝነትን የሚያዘወትሩ በተለያየ ምክንያት ከሰዎች ጋር ህብረት ማድረግ የማይችሉ ሰዎች በዚህ ሱስ ሊጠቁ እንደሚችሉ ጥናቶች ያሳያሉ።

4. በጓደኛ ግፊት

በአብዛኛው ታዳጊዎች እና ወጣቶች ስለ ወሲብ ምንነት ለማወቅ ካላቸው ጉጉት የተነሳ ወደ ፖርኖግራፊ ሊሳቡ ይችላሉ። ብዙዎች ወደ ሚያደርጉት ነገር ወይም ከዚያም ባለፈ በደፈናው ‘አታርጉ!’ የሚባሉ ነገሮችን የመሞከር ዝንባሌ በወጣቶች ይስተዋላል ። ታዳጊዎችና ወጣቶችም በጓደኞቻቸው ግፊት ወደዚህ ህይወት በቀላሉ ሊሳቡ ይችላሉ።

5. ሱስ

አንዳንድ ሰዎች ወሲብ ፊልም በተለያየ ምክንያት አንድ ጊዜ ወይም ከዚያ በላይ ከተመለከቱ በኋዋላ ሱሰኝነትን ያዳብራሉ። ሱስ ማለት ፈልገን የገባንበት ኋላ ግን እየጠላነውም ቢሆን የምናደርገው ነገር ነው። ማንኛውም ሱስ ሲጀመር በፍላጎት ሲሆን የሚቀጠለው ግን ያለ ፍላጎት ሊሆን ይቻላል። ፖርኖግራፊ ልክ እንደማንኛውም አደንዛዥ ዕጽ ሰዎችን ሱሰኛ የማድረግ ከፍተኛ አቅም አለው።

👉👉 #ውድ በተሰቦች እርሶ ከላይ የጠቀስናቸው ዋና ዋና የሚባሉት የሱስ ምልክቶች የሚታዩባችሁ ከሆነ ቆም ብለው ራሶን አይተው ዕርዳታ መፈለግ ይኖርቦታል ካልሆን ግን ለወሲብ ፊልም ሱስ መዘዞች ተጋላጭ ይሆናሉ። #ስለ #ግለ ወሲብ፣ ስለ #ስንፈተ ወሲብ፣ #ከጾታዊ ግንኙነት ጋር ስለተገናኙ ማንኛውም ችግሮች ለማወቅ ለመጠየቅ ዶክተር አለ 8809 ላይ ይደውሉ የተብራራ ሙያዊ መረጃ ያገኛሉ።ከጧት 2 ሰዓት እስከ ማታ 1፡00 ከሰኞ እስከ ሰኞ ቢደዉሉ የዶክተር አለ የስነ-ልቦና ባለሙያ ሊያማክሩዎ በመስመር ላይ ይገኛሉ!!!

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Haile Gebreselasie Avenue
Addis Ababa
HAWASSA,SIDAMO,