ትንቢተ ጦቢት
ቶ ሰባተኛዉ ፊደል
18/05/2021
አርማጌዶን ...
• ፩. የአርማጌዶን ጦርነት ምንድነው ?
አርማጌዶን ቃሉ ( አርም + መጊዶ ) ከሚሉ ሁለት የአብራይጥ ቃላቶች የተዋቀረ ሲሆን ፣ አርም በእብራይስጥኛ ተራራ ማለት ነው ፥ መጊዶ ደግሞ አሁን በፍልስጤም የምትገኝ አንድ ግዛት ነች ።
••• ትርጓሜውም የመጊዶ ተራራ ማለት ነው ።
ይህ ቦታ በአለም ፍፃሜ የእግዚአብሔር ጠላቶች ከበጉ ጋር ለመዋጋት የሚሰባሰቡበት መጊዶና የመጊዶ ተራራ ነው። ይህ ሰፊ ሸለቆ ሀያ ሁለት ኪሎ ሜትር ስፍትና ሰላሳ ሁለት ኪሎ ሜትር እርዝማኔ አለው ። ሰይጣን የክርስቶስን ዳግም ምፅአት ለማደናቀፍ የመጨረሻ አማራጬ ነው ለሚለው የአርማጌዶን ጦርነት የዓለም ነገስታትን ወደ አርማጌዶን ለማስከተት ከዘንዶው ፣ ከአውሬውና ከሀሰተኛው ነብይ አፍ የሚወጡትን ሶስት እርኩሳን
መናፍስት በመላው ዓለም ያሰማራል። (ራዕ 16 ፥ 13 - 15)
በዚህ ግዜ የዓለም ነገስታት ወደ ስፍራው የሚሰባሰቡት በዓለም ላይ ያላቸውን የበላይነት ለማረጋገጥ ቢመስላቸውም ሰይጣን ግን አንዴ አስቷቸዋልና ከዚያ የዘለለ አላማውን ለማስፈፀም ይጠቀምባቸዋል።
ዓለም በፍፃሜዋ ጠርዝ ላይ ቆማ ለማድረግ በምትዘጋጀው በዚህ የአርማጌዶን ጦርነት የምድር መሪዎች ራሳቸውን በትህትና ለእግዚአብሔር ዝቅ
ከማድረግ ይልቅ እግዚአብሔርን ተሳድበው መሞትን ይመርጣሉ ።
••••• (ዩሃንስ ራዕ 19 ፥ 19 - 21) እንዲህ ይላል :-
"በፈረሱም የተቀመጠውን ጭፍራዎችንም ይወጉ ዘንድ አውሬውና የምድር ነገድታት ጭፍራዎችም ተከማችተው አየሁ ።
አውሬውም ተያዘ በእርሱም ፊት ተአምራትን ያደረገ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉም የሰገዱትን ያሳተ ሀሰተኛው ነብይም ተያዘ ፤ ሁለቱም በህይወት ሳሉ በዲን ወደ ሚቃጠለው እሳተ ባህርተጣሉ ። የቀሩትም በፈረስ ላይ በተቀመጠው ከአፉ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ ወፎችም ሁሉ ከስጋቸው ጠገቡ" ይላል ።
የሰይጣን የአርማጌዶን ጦርነት ተልእኮ ከክርስቶስ ጋር ተዋግቶ ክርስቶስን የማሸነፍ ተልእኮ እንዳልሆነ ሰይጣን ጠንቅቆ ማወቁን በራሱ ላይ የተናገረውን
ምስክርነት በቂ ነው ተመልከቱ ፦
••• "ተው የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ ፥ ከአንተ ምን አለን ? ልታጠፍን መጣህን ?
ማን እንደሆንክ አውቄሃለሁ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱስ አለ" ሉቃ 4 ፥ 34
ስለዚህ የሰይጣን የአርማጌዶን ጦርነት ተልእኮ ብዙዎች እንዲድኑ የሚታገሰው ኢየሱስ በምፅአቱ እንዲዘገይ ወይም ምፅአቱ እንዲሰናከል
የማድረግ ከንቱ ሙከራ ነው ።
መፅሀፉ "ጥበብ በዚህ አለ ... አእምሮ ያለው የአውሬውን ቁጥር ይቁጠረው ቁጥሩ የሰው ቁጥር ነው ቁጥሩም 666 ነው" ይላልና ... ራዕ 13 ፥
18
በዩሃንስ ራዕ 22 ፥ 11 - 13 ላይም እንዲህ ይላል ፦
••• " ዓመፀኛውም ወደፊት ያምፅ ፣ እርኩሱም ወደፊት ይርከስ ፣ ፃዲቁም ወደፊት ፅድቅ ያድርግ ፣ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ... እነሆ በቶሎ እመጣለሁ
ለእያንዳንዱም እንደ ስራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ" ይላል።
ማጠቃለያ ከፍም ሃሳብ ...
እንግዲህ ከላይ ከተለያዩ ቦታዎች ያገኘናቸውን መረጃዎች አዋቅረን አንድ ወጥ መረጃ አቅርበናል ... አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር አለም ወደ
"አርማጌዶን እያመራች ይሆን ?" ... ይህ የኛም ጥያቄ ነው።
06/01/2021
"አዳምን ከሞት ለማዳን በገባው ቃልኪዳን መሰረት 5.500 ዘመን ሲፈፀም ከድንግል ማርያም ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ
ሰው ይሆን ዘንድ መጣ።"
መልካም የልደት በዓል
05/01/2021
23/10/2020
"ፅሃይን የምትለብሽ የብርሃን ልጅ ቅድስት ድንግል ማሪያም ልጅሽን ይዘሽ በሸሽ ጊዜ የደረሰብሽን ችግሮች ጨረቃን የሚጫሙ እግሮችሽ በመንገድ ብዛትና በአሸዋ ግለት እንደ ጎበጎቡ ቢሰማ ሰው ይቅርና ድንጋዩም ባለቀሰ ነበር::"
21/10/2020
"ምድሪቱን ይበላ ዘንድ አንበጣን ባዝዘው ፥ ወይም በህዝብ ላይ ቸነፈር ብሰድ ፥ በስሜ የተጠሩት ህዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ ፥ በሰማይ ሆኘ እሰማለሁ ፥ ሃጢያታቸውንም እፈውሳለሁ
.............2ኘሠ ዜነሠ 7 : 13.................
19/10/2020
ሀገር ማለት
ሀገር ማለት ሰንደቅ ናት ፤የቃልኪዳኑ ምልክት
ሀገር ማለት ሃይማኖት ናት ፤በቃሉ የነገረላት
ሀገር ማለት ጥበብ ናት ፤ተራቀው የማይጨርሷት
ሀገር ማለት ዕውቀት ናት ፤ብርሃን የሞላት ፍኖት
ሀገር ማለት ታሪክ ናት፤ማንነትህ የሚታይበት
ሀገር ማለት ቅርስ ናት፤ አሻራህ ቀርጾ ያወጣት
ሀገር ማለት ውርስ ናት፤ጸጋ ሀብት የምታፍስባት
ሀገር ማለት አደራ ናት ፤በእንክብካቤ የምትጠብቃት
ሀገር ማለት እናት ናት፤እጅጉን የምትወዳት
ሀገር ማለት አባት ናት ፤በጣሙን የምትኮራበት
ሀገር ማለት ሚስት ናት ፤ በፍቅሯ የምትሞትላት
ሀገር ማለት ልጅህ ናት ፤ በኃያሉ የምትሳሳላት
ሀገር ማለት ልጅህ ናት ፤ ደጀንነቱ የሆነህ ትምክሕት
ሀገር ማለት ወገን ናት ፤ መጠጊያ የምትሸሽበት
ሀገር ማለት ሕዝብ ናት ፤ብዙውን በአንድ ያዋሐደች ቋት
ሀገር ማለት ወግ ባሕል ናት ፤ ስትኖረው የምትደምቅበት
ሀገር ማለት ዙፋን ናት ፤ሉዓላዊ የሥልጣን ሹመት
ሀገር ማለት ዘውድ ናት ፤ግርማ ሞገስን የምትደፋባት
ሀገር ማለት ማዕረግ ናት ፤ልብ የምትሞላ በሐሴት
ሀገር ማለት ጌጥህ ናት ፤የሚሳሱላት የክት
ሀገር ማለት ክብር ናት ፤ በምንም የማይለውጧት
ሀገር ማለት ኩራት ናት ፤ ደረትህን የምትነፋባት
ሀገር ማለት ጽናት ናት ፤ የማይሠበር የማይወድቅ ቁመት
ሀገር ማለት ጀብድ ናት ፤የሠራት የጀግና ድፍረት
ሀገር ማለት አንድነት ናት ፤መነጣጠሉ የሚያፈራርሳት
ሀገር ማለት ፍቅር ናት ፤መሥዋዕትነት የማይፈሩላት
ሀገር ማለት እፎይታ ናት ፤ ምቾት የሞላት ዕረፍት
ሀገር ማለት ሥጋት ናት ፤የምትነሳ እንቅልፍ ቀን ከሌት
ሀገር ማለት ማተብ ናት ፤የማትፈታ ከአንገት
ሀገር ማለት ሕመም ናት፤ ስቃይዋ ዜማ ማኅሌት
ሀገር ማለት ጤና ናት፤የሕይወት መድኅን መድኃኒት
ሀገር ማለት ምሥጢር ናት፤ገመናን የምትከትባት
ሀገር ማለት ፊደል ናት ፤የሚገለጥባት የውስጥ ስሜት
ሀገር ማለት ሀቅ ናት ፤የልብ የኅሊና ሀብት
ሀገር ማለት ምግብ ናት ፤ሰውነት የምትራባት
ሀገር ማለት ጥማት ናት፤ ሲጠጧት የምትሰጥ ሕይወት
ሀገር ማለት ሥራ ናት ፤የህልውናህ መሠረት
ሀገር ማለት ዋስትና ናት፤ለሁሉም የምትቆምለት
ሀገር ማለት ደስታ ናት፤ የልብ ሰላም ሥምረት
ሀገር ማለት ሐዘን ናት፤የግድ ምንሠዋላት
ሀገር ማለት እርስትህ ናት፤ማርና ወተት የምታልብባት
ሀገር ማለት ጉልትህ ናት፤ሁሉንም የምትሆንባት
ሀገር ማለት ሁሉንም ናት፤የምናውቅ የማናውቀው
ሀብት አዎ ኢትዮጵያ ማለት መሠረት ናት ፤የምድርን ካስማ የተከለባት
ኢትዮጵያ ማለት የትም የሚያዩዋት ጉልላት ናት ፤የዓለም ጣራ ጠፈራት
ኢትዮጵያ ማለት የገባርት እርሻ ናት ፤የምትመግብ ዘለለት
ኢትዮጵያ ማለት የካህናቱ ጸሎት ናት ፤ከአምላክ የምታወርድ ምሕረት
ኢትዮጵያ ማለት የወታደሩ ትጥቅ ናት ፤የጠላት መቅሰፍት ወመዓት
ኢትዮጵያ ማለት የከያኔያን ጥበብ ናት ፤ዘወትር የሚቀኛት በስሜት
ኢትዮጵያ ማለት የመምህራን ሀሁ ናት፤ቁልፍ ምሥጢሩ ለዕውቀት
ኢትዮጵያ ማለት የነጋዴያን ንብረት ናት ፤እያደር የምትበረክት
ኢትዮጵያ ማለት የጋዜጠኞች እውነት ናት ፤ለክፉው የምትመር ሀሞት
ኢትዮጵያ ማለት የመሐንዲሶች ትልም ናት ፤የምትጠቅስ ሰማየ
ሰማያት
ኢትዮጵያ ማለት የአብራሪዎች ዓለም ናት፤የማትለየው በየሄደበት
ኢትዮጵያ ማለት የዳኞች ፍትሕ ናት ፤ሚዛኑ የሚፈርድበት
ኢትዮጵያ ማለት የሐኪሞቹ መድኃኒት ናት ፤ፈውሳ የምትሰጥ ሕይወት
ኢትዮጵያ ማለት የስፖርተኞቹ ጥረት ናት ፤ድል የምታቀዳጅ ጽናት
ኢትዮጵያ ማለት የሾፌሮቹ መንገድ ናት ፤ቢጓዝ የማይጨርሳት
ኢትዮጵያ ማለት የአናጢዎቹ መለኪያ ናት ፤የምትመጥን እንደ ፍላጎት
ኢትዮጵያ ማለት የግንበኞቹ ውኃልክ ናት ፤የምታስቀምጥ ያለመዛባት
17/10/2020
አየ ጉድ አየ ጉድ ምኑን በላሁት
አያመጣው የለ ሰኔና ግንቦት
አለች አሉ አንዲቱ
ከንቱ ቢሆንባት ያገባችዉ ገልቱ
ምን ያደርጋል አለች ህንፃ ኮንዶምኒየም
አንበጣ ወሮበት ገበሬው ሲታመም
ከንክሻ ስልጣን ሆዴን ከሚሞላ
ይሻል ነበር ፀሎት ውዳሴ መሃላ
Alexs Ye Yotor Lj
03/10/2020
ራቁቴን ከእናቴ ማህፀን ወጥቻለሁ፣
ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ.....
ኢዮብ 1:21
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
Addis Ababa