ዳዕወቱል አንቢያ Da'watul Anbiya

ዳዕወቱል አንቢያ Da'watul Anbiya የነቢያት ጥሪ በሁሉም ቦታ፣ ጊዜ እና ሁኔታ!

23/08/2026

አስደሳች ዜና ለዕውቀት ፈላጊዎች በሙሉ

ዳዕወቱል አንቢያ ኢሥላማዊ ድርጅት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች አዲስ አበባን ጨምሮ መድረሳዎችን እና የሂፍዝ ማዕከሎችን በመገንባት ለህዝበ ሙስሊሙ የሸሪዓህ እውቀቶችን በማስተማር፣ የሚድያና የጎዳና ዳዕዋ በማካሄድ፣ የሃይማኖት ንጽጽር ኮርሶች እና የተለያዩ ሳይንሳዊ ስልጠናዎችን በመስጠት ሙስሊሙን ማህበረሰብ በማገልገል ላይ ያለ ተቋም ነው።

በቀጣይ በ2019 ዓ.ል አድማሱን በማስፋት በአዲስ አበባ ባዘጋጀው ምቹ ቦታ በሆነ መልኩ ለወንዶች በአዳሪነት ብቁ በሆኑና ልምድ ባላቸው መሻይኾች በአቂዳ፣ በሐዲስ፣ በፊቅህ፣ በነሕው፣ በሶርፍ፣ በሃይማኖት ንጽጽር ትምህርት እና ሌሎችም የትምህርት ዘርፎችን በመቅረጽ በሁለት ዓመት የሚጠናቀቅ የዲፕሎማ መርኃ ግብር በማሰናዳት ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቆ ይገኛል።

ስለሆነም ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛዉም እውቀት ፈላጊ በተቀመጠው አድራሻ በአካል በመምጣት ወይም በስልክ በመደወል መመዝገብ የምትችሉ መሆናችሁን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው !

የመመዝገቢያ መስፈርቶች
❶) ሙሉ 30 ጁዝ ቁርአን የሀፈዘና ሽሀዳ ማቅረብ የሚችል
➋) በአካባቢው ከሚታወቁ መሻይኾች መሰረታዊ ሙኽተስር /አጫጫር/ ኪታቦችን የቀራ
➌) እድሜው ከ 15 እስከ 20 የሆነ
➍) አረበኛ ቋንቋ መጻፍ፣ ማዳመጥና መናገር የሚችል
➎) መልካም ስነምግባር እንዳለው የሚያረጋግጥ፣ ከአካባቢው መሻይኾች ወይም ከኢስላማዊ ተቋም የድጋፍ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
➏) ከወላጅ ወይም ከአሳዳጊ ፍቃደኝነታቸዉን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
➐) ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነና ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
➑) የመዕሐዱን ህግና ደንብ የሚያከብር
➒) የመቅራት አላማና ቁርጠኛነት ያለው
➓) ስምንተኛ ክፍል እና ከዛ በላይ ያጠናቀቀ

ማሳሰቢያ
❶) ከምዝገባ ቡሗላ አዲስ አበባ በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መስርያ ቤት ተቋሙ ያዘጋጀዉን የመግቢያ ፈተና በአካል መቶ መፈተን ግዴታ ነው
➋) ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ያለን ቦታ ዉስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ

ለበለጠ መረጃ

አድራሻ ሸገር ከተማ ፉሪ ክ/ከተማ ጃዕፈር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ

ስ.ቁ 0921637766 0907416666

22/08/2026

በመውሊድ ስም ሽርክ እየተንሰራፋ ነው❤️‍🩹 || ኡስታዝ አህመድ አደም

21/08/2026

ما تيسر من سورة مريم || القارء حذيفة زكي

الجزء ➋

ዳዕወቱል አንቢያ መዓሐድ                   ክፍት የስራ ማስታወቅያ በዳዕውቱል አንብያ መዓሐድ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን መቅጠር ይፈልጋል ፡፡ ስለዚህ ...
19/08/2026

ዳዕወቱል አንቢያ መዓሐድ

ክፍት የስራ ማስታወቅያ
በዳዕውቱል አንብያ መዓሐድ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን መቅጠር ይፈልጋል ፡፡ ስለዚህ ከታች የተዘረዘሩት መስፈርት የምታሟሉ ማንኛዉም ተወዳዳሪዎች ከታች ባለው አድራሻ በአካልም ይሁን በስልክ በመደወል ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ7 ቀናት የሚቆይ ሲሆን መረጃ በሟሟላት ፈጥነው በመመዝገብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

1) የስራ መደብ= ምግብ አብሳይ
ብዛት= 2
ፆታ= ሴት
2) የስራ መደብ= ፅዳት
ብዛት= 1
ፆታ= ሴት
3) የስራ መደብ= ጥበቃ
ብዛት= 1
ፆታ= ወንድ

✨የምግብ አብሳይ የመወዳደርያ መስፈርት

1 . ምግብ በማብሰልና በማዘጋጀት የስልጠና ሰርተፍኬት ያላት
2 . የሸሪአ አደብ የተላበሰችና ሸሪአዊ አለባበስ የምትለብስ
3. ጥሩ ስነብግባር የተላበሰችና የተሰጣትን ሐላፍትና በታማኝነት በአግባቡ የምትወጣ
4. ተያዥ ማቅረብ የምትችል
5. ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነና ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የምትችል
6 . ለመአሐዱ ቅርብ የሆነች

✨የጽዳት ሰራተኛ የመወዳደርያ መስፈርት
1. የጽዳት ሞያ ያላት
2. የሸሪአ አደብ የተላበሰችና ሸሪአዊ አለባበስ የምትለብስ
3. ጥሩ ስነብግባር የተላበሰችና የተሰጣትን ሐላፍትና በታማኝነት በአግባቡ የምትወጣ
4. ተያዥ ማቅረብ የምትችል
5. ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነ ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የምትችል
6 . ለመአሐዱ ቅርብ የሆነች


✨የጥበቃ ሰራተኛ የመወዳደርያ መስፈርት
1. 8ተኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀ
2. የአካል ብቃት ያለዉና ከዚህ በፊት አንድ ዓመትና ከዚያ በላይ የስራ ልምድ ያለው
3. ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነና ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የምትችል
4 . ተያዥ ማቅረብ የሚችል
5 . ለመአሐዱ ቅርብ የሆነ


ለበለጠ መረጃ

አድራሻ ሸገር ከተማ ፉሪ ክ/ከተማ ጃዕፈር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ
ስ.ቁ 0921637766 0907414646

=======
(ነሐሴ 13, 2018)

የቴሌግራም ቻናል:-
http://t.me/daio_TG07
http://t.me/daio_TG07

ዳዕወቱል አንቢያ መዓሐድ                     ክፍት የስራ ማስታወቅያ በዳዕውቱል አንቢያ መዓሐድ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የሚያሟሉ መሻኢኾችንና ስራ አስኪያጅ /ሙዲር/  መቅጠ...
19/08/2026

ዳዕወቱል አንቢያ መዓሐድ

ክፍት የስራ ማስታወቅያ
በዳዕውቱል አንቢያ መዓሐድ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የሚያሟሉ መሻኢኾችንና ስራ አስኪያጅ /ሙዲር/ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ ማንኛዉም ተወዳዳሪዎች ከታች ባለው አድራሻ በአካልም ይሁን በስልክ በመደወል ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ10 ቀናት የሚቆይ ሲሆን መረጃ በሟሟላት ፈጥነው በመመዝገብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

1) የስራ መደብ= መሻይኽ
ብዛት= 2
ፆታ= ወንድ
2) የስራ መደብ= ሙዲር እና ሙሽሪፍ
ብዛት= 1
ፆታ= ወንድ

✨ለመሻኢሆች የመወዳደርያ መስፈርት

1 የሽሪዐ ዕውቀት በሁሉም ፈኖች ያጠናቀቀ
2. እውቅና ካለው የሽሪአ ትምህርት ተቋም /ጃሚአ/ ሰርተፍኬት ያለው
3. የአካዳሚ ትምህርት የ 12ተኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ ሰርተፍኬት ያለው
4. ሁለት ዓመትና ከዚያ በላይ የማስተማር ልምድ ያለው
5. ቁርአን አስራ አምስትና ከዚያ በላይ የሐፈዘ
6. ጥሩ ስነምግባር ያለዉና በእኔነት ስሜት የሚያስተምር
7. የአህለሱና ወልጀመአ አቂዳ /እምነት / የሚያራምድና ከየትኛዉም ወገተኝነት ነጻ የሆነ
8. ሰአት አክባሪና ሸሪአዊ አዳብን የተላበሰ
9. ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነና ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
10. አረበኛና አማርኛ በጥሩ ሁኔታ መናገር ፣ መጻፍና ማስተማር የሚችል
11. ተያዥ ማቅረብ የሚችል

✨ለሙዲርና ሙሽርፍ የመወዳደርያ መስፈርት

1. መሰረታዊ የሽሪአ እውቀት ያለው
2. ዲግሪና ከዛ በላይ የትምህርት
ሰርተፍኬት ያለው
3 . በማኔጅመንት ምሩቅ የሆነና ከሁለት አመት በላይ በኢዳራነት የስራ ልምድ ያለው
4. ጥሩ ስነምግባር ያለዉና በኔነት ስሜት የሚሰራ
5 .የአህለሱና ወልጀመአ አቂዳ /እምነት / የሚያራምድና ከየትኛዉም ወገተኝነት ነጻ የሆነ
6 . ሰአት አክባሪና ሸሪአዊ አዳብን የተላበሰ
7 . ከተላላፊ በሽታ ነጻ የሆነና ከሚታወቅ የህክምና ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
8. አረበኛና አማርኛ በጥሩ ሁኔታ መናገር፣ መጻፍና ማስተማር የሚችል
9. ተያዥ ማቅረብ የሚችል

ለበለጠ መረጃ

አድራሻ ሸገር ከተማ ፉሪ ክ/ከተማ ጃዕፈር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ
ስ.ቁ
0921637766 0907414646

=======
(ነሐሴ 13, 2018)

የቴሌግራም ቻናል:-
http://t.me/daio_TG07
http://t.me/daio_TG07

18/08/2026

የተከበረው መስጂድ ጭፈራ ቤት ሲሆን በጣም ያሳዝናል❤️‍🩹 || ኡስታዝ አህመድ አደም

ስለ አቂዳ ምን ያህል ያውቃሉ?አቂዳ በአረብኛ ቋንቋ ትርጓሜ መሠረት መቋጠር፣ ማጠንከር የሚል ፍቺ ሲኖረው በኢስላም ምሁራን አተረጓጎም አኳያ ደግሞ ቀልብ እውነት ብላ የተቀበለችው፣ ነፍስ የተ...
08/08/2026

ስለ አቂዳ ምን ያህል ያውቃሉ?

አቂዳ በአረብኛ ቋንቋ ትርጓሜ መሠረት መቋጠር፣ ማጠንከር የሚል ፍቺ ሲኖረው በኢስላም ምሁራን አተረጓጎም አኳያ ደግሞ ቀልብ እውነት ብላ የተቀበለችው፣ ነፍስ የተረጋጋችበት፣ ጥርጣሬ የማይከተለው ቁርጥ ያለ እምነት ማለት ነው። ማንኛውም እሳቤ በዚህ ልክና መጠን ከታመነበት ትክክል ሆነም አልሆነ አቂዳ በሚል ይጠራል። እንደ እስልምና አስተምህሮ አቂዳ የስራዎች ሁሉ መሠረትና መነሻ ነው። አንድ አካል የሚሰራው መልካም ስራ ተቀባይነት እንዲኖረው እና ምንዳን እንዲያስገኝለት የሚያደርገው መሠረታዊ እና ዋነኛው ነገር የተስተካከለ አቂዳ ባለቤት መሆን ነዉ።

ኢስላማዊ አቂዳ ምንድን ነው ?

ካለምንም አጋር ካልነበርንበት ያስገኝንን አምላክ ለርሱ ተገቢ የሆኑ ሀቆችን ለማንም ሳናጋራ መስጠት እና በሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ነብይነት ማመን ላይ ተመርኩዞ በቀሪዎቹ የዲን መሠረቶች እንዲሁም መርሆች ላይ በማመን የሚገነባ እምነት ነው። የጌታችን አላህ ትልቁ ሀቅ ደሞ ተውሒድ ነው። ተውሒድ ማለት አላህን በአምላክነቱ ፣ በጌትነቱ ፣ በስምና ባህሪያቱ ብቸኛ ማድረግ ሲሆን በእስልምና ምሁራን ዘንድ በ 3 ዋና ዋና ክፍሎች በመመደብ ተብራርቷል። ይኸውም ፦
1)
2)
3)

1) ተውሒድ አል ሩቡቢያ
አላህ (ሱ.ወ) አለምን በብቸኝነት ፈጣሪ ፣ አስተናባሪ ፣ ህይወት ሰጪ እና ነሽ ፣ ሲሳይን ለጋሽ ፣ የጠንካራ ሀይል ባለቤት መሆኑን ማረጋገጥ ማለት ነዉ ።
ጌታችን አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል ፦

"አላህ ያ የፈጠራችሁ ፣ ከዚያም ሲሳይን የሰጣችሁ ፣ ከዚያም የሚገድላችሁ ከዚያም ህያው የሚያደርጋችሁ ነው ።” [አል ሩም ፡40]

" አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኃይል ባለቤት ነው።” [አል ዛሪያት ፡ 58]

" ነገሩም አንዳችን በሻ ጊዜ ኹን ማለት ነው። ወዲያውም ይኾናልም። [82] ያ የነገሩ ሁሉ ስልጣን በእጁ የኾነው ጌታ ጥራት ይገባው ። ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ።” (ያሲን 82-83)

2) ተዉሒድ አል ኡሉሂያህ
ማንኛውንም የአምልኮ አይነት ለአላህ ብቻ በማድረግ እና ከሱ ውጭ ላለ ለየትኛውም አካል እንደማይገባ በማመን የሚገለፅ የተዉሂድ ክፍል ነው ። አምልኮ ማለት ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ እንዳብራሩት ለማንኛውም አላህ ለሚወደውና ለሚቀበለው በግልፅም ይሁን በስውር ለሚፈፀም ንግግር ወይም ተግባር የተሰጠ አጠቃላይ ስያሜ ነው ።
በቁርአን ውሰጥ ተውሂደል ኡሉሂያ ከሚያስገነዝቡ አንቀፆች መካከል፦

"እናንተ ሰዎች ሆይ! የፈጠራችሁን እነዚያንም ከናንተ በፊት የነበሩትን (የፈጠረው) አምላካችሁ ተገዙ፤ (ቅጣትን) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና።" [አል በቀራ፡21]

"አላህንም ተገዙ በእርሱ ምንንም አታጋሩ።"[አን ኒሳዕ፡36]

"ስግደቴ ፣ መገዛቴ ፣ ህይወቴም ፣ ሞቴም ለ አለማት ጌታ ለ አላህ ነው" በል።[አል -አንአም ፡12]

3)ተውሂድ አል አስማኡ ወሲፋት
አላህ (ሱ.ወ) በቁርአን ላይ እራሱን የገለፀበትን እና ከመልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) በሶሂህ ሀዲስ ተዘግበው በመጡ የአላህ ስምና ባህሪያት ማመን እና አላህ ና መልዕክተኛው ከአላህ ያራቁትን ባህሪያት ማራቅን በአንድነት ይይዛል።
የላቀዉ አላህ እንዲ ይላል ፦

"ለአላህ መልካም ስሞች አሉት። (ስትፀልዩም) በእርሷ ጥሩት"። [አል አዕራፍ ፡180]

የአላህን ስሞችና ባህሪያት በምናፀድቅበት ጊዜ ከየትኛውም ፍጡር ጋር ሳናመሳስል እና እንዴትነቱን ሳንመራመር እንዲሁም ሳናዛባ/ሳናንሻፍፍ ሊሆን ይገባል።

"የሚመስለው ምንም ነገር የለም። እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው።"[አሽ ሹራ፡ 11]

በሦስቱም የተውሂድ ክፍሎች ማመን በሁሉም የሰው ልጅ ላይ ግዴታ የሆነ ነገር ነው። ምክንያቱም የሰው ልጆችና ጋኔኖች የተፈጠሩበት፣ በየዘመናቱ መፅሐፍቶች የወረዱበትና መልዕክተኞች የተላኩበት ዋና ምክንያት ተውሂድን ማረጋገጥ ስለሆነ፣ ይህም በቁርአን ላይ በግልፅ ተቀምጧል:

"ጋኔንንና ሰውንም ሊገዙኝ እንጂ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም።" [አል-ዛሪያት: 56]

በየህዝቡም ሁሉ ውስጥ "አላህን ተገዙ፣ ጣኦትንም ራቁ" በማለት መልዕክተኛን በእርግጥ ልከናል:: [አል-ነህል: 36]

ከላይ እንጸተገለፀውም ለመልካም ስራ ቅቡልነት ሊሟላ የሚገባው ወሳኝ ቅድመ መስፈርት የተውሂድ መስተካከል ነው።

"እነዚያ ያመኑ፣ መልካም ስራዎችንም የሰሩ፣ ሶላትንም ያዘወተሩ፣ ዘካንም የሰጡ ለእነሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው። በእነሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነሱም አያዝኑም።" [አል-በቀራ: 277]

"እነዚያ ያመኑትና መልካም ስራዎችንም የሰሩ ለእነሱ የፀጋ ገነቶች አሏቸው።" [ሉቅማን: 8]

ተውሂድን ከማስተካከል ጋር ተቆራኝቶ የሚገለጽ ወይም ሊታመን የሚገባው ነገር በነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ነብይነት ማመን የሚለው አስተምህሮ ነው። ይኸውም ያዘዙትን በመታዘዝ ፣ የተናገሩትን ሁሉ እውነት ነው ብሎ በመቀበል፣ ከከለከሉት እና ካስጠነቀቁት ነገር በመራቅ እንዲሁም አላህን እርሳቸው ባስተማሩት መንገድ ብቻ በመገዛት የሚገለጽ እምነት ነው።

ይህ ከላይ በጥቂቱም ቢሆን ለመዳሰስ የሞከርነው ኢስላማዊ አቂዳ የመልዕክተኛው ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)፣ የሶሀቦቻቸው ከዚያም የታቢኢዮች እና የነርሱ ተከታዮች መንገድ ነው። እነዚህ አካላት በተጓዙበት መጓዝ ለመመራት ዋስትና እንደሆነ የላቀው አላህ እንዲህ በማለት ይናገራል:

"...በእርሱ ባመናችሁበት ቢጤ ቢያምኑ በርግጥ ተመሩ።"[አል በቀራ፡ 139]

ስለዚህም መመራትን የፈለገ ማንኛውም ግለሰብ ይህን ኢስላማዊ አቂዳ በትክክል በማመን እና በመተግበር ላይ ሊተጋ ይገባዋል።
[ወላሁ አዕለም]
=======
በዳዕወቱል አንቢያ ኢስላማዊ ድርጅት ተማሪዎች ተዘጋጅቶ የቀረበ።
(ነሐሴ 01, 2018)

የቴሌግራም ቻናል:-
http://t.me/daio_TG07
http://t.me/daio_TG07

06/08/2026

........


ከረሱል ﷺ ወርቃማ ንግግሮች መሀከል ✨===========================قال رسول الله صلى الله عليه وسلم ((إن الله يحبُّ العبدَ التقيَّ الغني...
02/08/2026

ከረሱል ﷺ ወርቃማ ንግግሮች መሀከል ✨
===========================

قال رسول الله صلى الله عليه وسلم ((إن الله يحبُّ العبدَ التقيَّ الغنيَّ الخفيَّ))؛ رواه مسلم.
_____
የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል:

"አላህ (ﷻ)
💢 እርሱን የሚፈራ (ያዘዘውን የሚታዘዝ እና የከለከለውን የሚከለከል)፣
💢 የተብቃቃ (አላህ በሠጠው ነገር የነፍስ መብቃቃት ያለው) እና
💢ድብቅ (ለአላህ ብሎ የሚሰራ እና ወጣ ወጣ የማይል) የሆነን ባርያ ይወዳል።"

ሰሒሕ ሙስሊም (2965)

የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ተጠቃሚ ይሁኑ
http://t.me/daio_TG07
http://t.me/daio_TG07

31/07/2026

ሚስቶቻቸው ኪታብ ያቃጠሉባቸው ዑለሞች 😅|| በኡስታዝ አብዱረዛቅ ባጂ
በዳዕወቱል አንቢያ ኢስላማዊ ድርጅት አማካኝነት በወሊሶ ከተማ ላይ ተሰጥቶ ከነበረ የመንዙመቱ ታኢያህ ደርስ የተቀነጨበ።
||


Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዳዕወቱል አንቢያ Da'watul Anbiya posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share