በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የሪሚዲያል ፕሮግራም #የማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች ፦
1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
4. ሲቪል ሰርቪርስ ዩኒቨርሲቲ
5. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
6. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
7. ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ናቸው።
ተማሪዎች የሞሉትን ምርጫ በ student.ethernet.edu.et በኩል ማረጋገጥ የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
Via
Bulbula Secodary & Preparatory School
join this page
01/10/2025
የተሻሻለው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት…
አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤትን ከ300 ወደ 297 ዝቅ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ እንደገለጸው ÷ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተማሪዎች ወደቀጣይ የትምህርት ደረጃ ለመዛወር 50 በመቶና ከዚያ በላይ ማምጣት እንዳለባቸው ይደነግጋል።
በዚህ መሰረትም በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና አማካይ ውጤታቸው 49 ነጥብ 50 እስከ 49 ነጥብ 99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ወደ 50 በመቶ እንዲጠጋጋ መወሰኑን አመልክቷል፡፡
ውሳኔውን ተከትሎም 49 ነጥብ 5 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ እንዳሟሉ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ስለሆነም 49 ነጥብ 5 እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል፡፡
በመሳፍንት እያዩ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Fana Television This is the official Fana Media Corporation S.C (FMC) YouTube Channel - where you can get all the latest videos in Amharic, Afan Oromo, Tigrigna and Arabic. You can visit us on: https://fanamc.com You can follow us on: https://t.me/fanatelevision https://t.me/afanoromofana https://t.me/tigrignafana....
09/10/2024
የትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቢያ!..
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል፣
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 2017
2. ማስታወቂያ
በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 2017
Benefit Application Benefit Application
09/09/2024
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት
በፖርታል እና በቴሌግራም ቦት ይመልከቱ
| የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነ፡፡
የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን በሚከተሉት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የውጤት መግለጫ አማራጮች ከጳጉሜ 4 ቀን ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ማወቅ ይችላሉ።
በዚህ መሰረት
1. ፖርታል፡- https://result.eaes.et
2. በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- https://t.me/EAESbot
3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284 ላይ ‘R’ን በማስቀደም የመለያ ቁጥር በማስገባት (ምሳሌ R1234567) መልዕክት በመላክ ውጤትዎን ማወቅ ይችላሉ፡፡
ይህ አማራጭ ኢትዮ ቴሌኮም የሚያስከፍለው መደበኛ የSMS ክፍያ ይኖረዋል።
ከውጤት መግለጫ ፖርታልና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማታም ይችላሉ፡፡
መልዕክት- ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች!...
በበይነ መረብ (Online) የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና በተመለከተ የተሰጠ ማብራሪያ
በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በበይነ መረብ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወረቀት አልባ በማድረግ የዲጂታል ጉዞውን አንድ ምዕራፍ ጀምሯል። ይሄንንም ጉዞ የተሳካ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ ለተፈታኞች በክላስተር የተዘጋጀው ማስፈንጠሪያ (URL) ከፈተናው በፊት ገብተው የሚለማመዱበት ሲሆን የፈተናው እለት ደግሞ መፈተኛ ይሆናል። ስለሆነም ከዚህ በታች በምትፈተኑበት የፈተና ክላስተር ፊትለፊት በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመግባት መለማምድ ትችላላችሁ፡፡ እስካሁን username እና password ያለገኘ ተፈታኝ ካለ፣ ከዚህ በፊት ለትምህርት ቢሮዎች ስለተላከ፣ ከየትምህርት ቤቱ አስተባባሪዎች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ክላስተር አንድ
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር፡ https://c2.exam.et
ሲዳማ ብሄራዊ ክልል፡ https://c2.exam.et
ትግራይ ብሄራዊ ክልል፡ https://c2.exam.et
ክላስተር ሁለት
ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፡ https://c3.exam.et
ጋምቤላ ህዝቦች ክልል፡ https://c3.exam.et
አማራ ብሄራዊ ክልል፡ https://c3.exam.et
ክላስተር ሶስት
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል: https://c4.exam.et
ሀረሪ ብሔራዊ ክልል: https://c4.exam.et
አፋር ብሔራዊ ክልል: https://c4.exam.et
ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል - 1
• አዳማ ከተማ: https://c4.exam.et
• አጋሮ ከተማ: https://c4.exam.et
• አምቦ ከተማ: https://c4.exam.et
• ምሥራቅ አርሲ: https://c4.exam.et
• ምዕራብ አርሲ: https://c4.exam.et
• አሰላ ከተማ: https://c4.exam.et
• ባሌ: https://c4.exam.et
• ባቱ ከተማ: https://c4.exam.et
• ቤሾፍቱ ከተማ: https://c4.exam.et
• ቦረና: https://c4.exam.et
• ቡሌ ሆራ ከተማ: https://c4.exam.et
• ቡኖ በደሌ: https://c4.exam.et
• ዶዶላ ከተማ: https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ባሌ: https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ቦረና: https://c4.exam.et
• ጉጂ: https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ሐረርጌ: https://c4.exam.et
• ምዕራብ ሐረርጌ: https://c4.exam.et
• ሆለታ ከተማ: https://c4.exam.et
• ሆሮ ጉዱሩ: https://c4.exam.et
• ኢሉባቦር: https://c4.exam.et
ክላስተር አራት
ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር: https://c5.exam.et
ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል - 2
• ጅማ: https://c5.exam.et
• ጅማ ከተማ: https://c5.exam.et
• ቄለም ወለጋ: https://c5.exam.et
• ማያ ከተማ: https://c5.exam.et
• መቱ ከተማ: https://c5.exam.et
• ሞጆ ከተማ: https://c5.exam.et
• ሞያሌ ከተማ: https://c5.exam.et
• ነጆ ከተማ: https://c5.exam.et
• ነቀምት ከተማ: https://c5.exam.et
• ሮቤ ከተማ አስተዳደር: https://c5.exam.et
• ሰንዳፋ በኬ: https://c5.exam.et
• ሻኪሶ ከተማ: https://c5.exam.et
• ሻሸመኔ ከተማ: https
15/12/2023
የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 23 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል።
ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 255 ያመጡ
የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ700 -234 ያመጡ
የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ600- 218 ያመጡ
የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 200 ያመጡ
ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 224 ያመጡ
ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ
ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 - 192 ያመጡ
ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ
አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ
አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ
አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ
አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ
ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ500 -150 ያመጡ
ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ500 -150 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል።
በምንተስኖት ሙሉጌታ
10/10/2023
በውጤት ላይ ቅሬታ ያላቸው የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ቅሬታቸውን eaes.et ድረ-ገፅ ላይ እስከ ጥቅምት 5 ከቀኑ 11:30 ድረስ ማመልከት ይችላሉ
******************
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ከነገ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚከተሉትን ሶስት አማራጭ አድራሻዎች ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፥
• በዌብሳይት፡- eaes.et
• በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284
• በቴሌግራም-
ከላይ ከተገለፁት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌሎች የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን የጠቆመው አገልግሎቱ፤ ተፈታኞች በማመሳሰል ውጤት እንገልፃለን ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክሯል።
ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ምንም ዓይነት ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑንም አክሏል።
ለ 2015 የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች የተላለፈ መልዕክት!
| የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ መስከረም 29/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ተፈታኞች የሚከተሉትን ሶስት አማራጭ አድራሻዎችን ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡
♦ በዌብ ሳይት፡- eaes.et
.♦በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284
♦ቴሌግራም አድራሻ፡-
ጥብቅ ማሳሰቢያ፡-
ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን እያሳወቅን በማመሳሰል ውጤት እንገልጻለን ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራስዎን ይጠብቁ። በተጨማሪም ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን ይወቁ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
#አጠቃቀም
በዌብ ሳይት ለማየት
1. eaes.et ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ
2. በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ
3. Check Result የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ።
♦በአጭር የጽሁፍ መልዕክት
6284 የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር ) ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በማላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ
♦በቴሌግራም ቦት
1. ይፈልጉ
2. የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ።
የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል።
መስከረም 27/2016 ዓ/ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል። በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ይሆናል።
18/09/2023
08/09/2023
የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና #ውጤት በፀጥታ እና በሌሎች ምክንያቶች ፈተናቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከወሰዱ በኃላ ይገለፃል ተብሎ ይጠበቃል።
በፀጥታ ችግር እና ሌሎች ምክንያቶች ፈተናቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች ከመስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናቸውን ይወስዳሉ።
የእነዚህ ተፈታኞች እና የመጀመሪያው ዙር ፈተና ተፈታኞች ውጤት አንድ ላይ እንደሚገለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ከቀናት በፊት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን መስከረም 2016 ዓ/ም አጋማሽ ድረስ ይፋ ለማድረግ እና ጥቅምት ወር 2016 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንዲጀመር እቅድ መያዙን መግለፃቸው ይታወሳል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Telephone
Website
Address
407COD1036