ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

Share

"የአሏህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ አትለያዩም" አል-ዒምራን - 103

03/04/2026

የአሏህ ነን አሏህ የወደደውን እንወዳለን ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ ነጅብ ረመዷን ማገባደጃ ላይ ልዘይራቸው ባቀናሁበት ጊዜ ልዩ አቀባበል አድርገውልኝ የማረሳ ቆይታም አድርገን ነበር እነሆ ዛሬ ወደማይቀረው ሀገር መሻገራቸውን ሰማሁ ሐዘኑ እግጅ የበረታ ነው። በቆይታችንም ስለ ታላላቅ የዳና ከዋክብቶች ታሪክ ፤ ስለ ዑለሞቻችን አይተኬ የዲን ሚና ፤ ስለከፈሉት ተጋድሎና አበርክቶ በሲፊው አጫውተውኝ ነበር።

ሸይኽ ሙሐመድ ነጅብ የታላቁ ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ዳና ልጅ ሲሆኑ የታላቁ ዳና ሐሪማ አምስተኛ ኸሊፋም ነበሩ የዑለማዎች ማለፍ ለዑማው ትልቅ ህዘን ብሎም የዕውቀትና የተርቢያ አባቶችን ማጣት ነውና ሁላችንም ዱዓእ እንድናደርግ እያስታወስኩ ለሸይኻችን አሏህ የመልካም ስራዎቻቸውን ምንዳ እጥፍ ድርብ አድርጎ በሰፋው እዝነቱ በጀነት ያስደሳልን ዘንድ እማጸናለሁ። ለቤተሰቦቻቸው ፤ ለደረሶቻቸው ፤ ለወዳጅ ዘመድና ለመላው ሙስሊም መጽናናትን እመኛለሁ።

የደጋጎጎች የታላላቆች መሸኘት ለኛ ትልቅ መልክት አለውና ወደ አሏህ እንመለስ ምትካቸው ይበዛ ዘንድ ወንድም እህቶቼም ጣት ማታ በዱዓእ እንበረታ።
أعظم الله أجرنا وأحسن عزائنا وغفر لميتنا.إنا لله وإنا إليه راجعون .
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

30/03/2026

"እራሳችሁን ጠብቁ"
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

Photos from ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam 's post 20/03/2026

بِسم الله الرّحمن الرّحيم

(( فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ۚ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا.)) النّساء ٥٩

"በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአሏህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ (የተከራከራችሁበትን ነገር) ወደ አሏህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡" አን-ኒሳእ 59

የተለያዩ ወንድሞች ለሙስሊሞች ስለሚደረጉ ጠቅላይ ዱዐዎች በተመለከተ ማብራሪያዎችን ጠይቀዉኛል። ማብራሪያው ለሌሎችም ይጠቅም ዘንድ በማሰብ
“رِسالَةٌ مِن الشَّهدِ لِمَن القَى السَّمعَ وهُو شَهِيدٌ”
በሚል መጠሪያ ለሁሉም ለማድረስ ወድጃለሁ። በአሏህ ፍቃድ የህትመት ብርሃንን አግኝቶ ለሁሉም እንደሚደርስ ተስፋ አደርጋለሁ።

በስተመጨረሻም ከረመዷን በማስከተል ከሸዋል ወር ስድስት ቀናቶችን በመፆም እያስታወስኳችሁ በድጋሜ ዒድ ሙባረክ ለማለት እወዳለሁ ።
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

19/03/2026

እንኳን ለዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ረመዷንን በሰላም አስጨርሶ ለዚህ ደስታ ላበቃን አሏህ ምስጋና ይግባው። በዓሉ የደስታ፣ የጤና እንዲሁም የሰላም እንዲሆንልን እመኛለሁ።

عيد مبارك ! وكل عام وأنتم بخير. تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال.

14/03/2026

"የአሏህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ አትለያዩም" አል-ዒምራን - 103
*******
አሰላሙዓለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ ወድና የተከበራችሁ ወንድም እህቶች ይህ ትክክለኛው የሸይኽ ዑመር ኢማም ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ሁላችሁም ከመዋዳጀት ባሻገር ለወዳጅ ዘመድ በማጋራት በየጊዜው የምንለቃቸውን ትምህርቶችና ጠቃሚ መጣጥፎች ተደራሽ ይሆኑ ዘንድ የበኩላችንን እንወጣ።
አሏህ መልካሙን ሁሉ ይወፍቀን አሚን።
https://t.me/SheikhUmerImamofficial

11/03/2026

በረመዷን መጨረሻ ዓስርት ሌሊቶች ፈልጓት !

አሏሁ ተዓላ በዚህ ኡማ ላይ ከቸረው ታላላቅ ችሮታዎች ውስጥ የተከበረው ወርሀ ረመዷን አንዱና ትልቁ ሲሆን በዚህ ወር ውስጥም 1 ትልቅ አበበማ ሌሊት አለች።

አሏህም ስለ እርሷ በሱረቱል ቀድር ሲነግረን (የለይለቱል ቀድር ከ ሺህ ወር በላጭ ናት።) ብሎናል ማለትም ለይለቱል ቀድር የታየችበት 1 ሌሊት ሌላ ለይለቱል ቀድር ያልታየባቸውን 1 ሺህ ወራቶች ትበልጣለች ማለት ነው። ይህም ወደ 83.3 አመታት ገደማ ነው። አሏሁ ተዐላ እርሷን ይወፍቀን።

በእርግጥ ይህች አበባማ ሌሊት በየትኛውም የረመዷን ቀናት ውስጥ ልትሆን ትችላለች። ይህም አንድ ሙስሊም እርሷን በመሻት ሁሉንም የረመዷን ቀናት በዒባዳ ተግቶ እንዲያሳልፍና የአሏህን ማሀርታ እንዲጠይቅ ነው። ከመሆኑም ጋር አዛኙ ነቢይ በይበልጥ ወደ መጨረሻው የረመዷን ቀናት እንድንጠባበቅ አመላክተዋል።

ታላቁ ነቢይ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም በሐዲሳቸው ለሶሐበቶቻቸው ስለ ለይለቱል ቀድር ሲናገሩ እንዲህ አሉ "በመጨረሻዎቹ ዓስርት ሌሊቶች ፈልጓት" ከመጨረሻዎቹ ዓስርት ሌሊቶች ደግሞ ዊትሮችን (ጎዶሎ) ሌሊቶች ላይ በይበልጥ ለይለቱል ቀድር ሊገኝ እንደሚችል ነገሯቸው! ማለትም በ21፣ 23፣ 25፣ 27 እና 29 የረመዷን ሌሊቶች ላይ ለይለቱል ቀድር የመታየት እድሉ እጅግ ሰፊ ነው!

"ጌታችን ሆይ ! በምድረ ዓለም ደግን ነገር (ጸጋን) በመጨረሻይቱም አገር ደግን ነገር (ጀነትን) ስጠን ፤ የእሳትንም ቅጣት ጠብቀን" አል በቀራህ 101 || አሏህ ሆይ ! በስምህ ልቅና ይሁንብህ በእዝነትህ አካበን ፤ ከመጥፎው ሁሉ ጠብቀን ፤ አንተን በማምለክ ላይ ብርቱዎች አድርገን አሚን።
بسم الله الرّحمٰن الرّحيم
اللهُمّ إني أسألُكَ باسمِكَ العظيمِ الأعظم وبأسمائكَ الحُسنى أنْ تلطُفَ بنا وبإخوانِنا وبالمسلمين يا أرحمَ الراحمين، يا أرحمَ الراحمين، يا أرحمَ الراحمين،
يا حيُّ يا قيّوم، يا حيُّ يا قيّوم، يا حيُّ يا قيّوم، يا ذا الجلالِ والإكرام، يا ذا الجلالِ والإكرام، يا ذا الجلالِ والإكرام، اجعلنا في أمنٍ وأمان، اجعلنا في أمنٍ وأمان، اجعلنا في أمنٍ وأمان،
اللهم سلِّمنا والطفْ بنا وبالمسلمين، برحمتِكَ يا أرحمَ الراحمين
وصلى الله على سيِّدِنا محمّد وعلى ءاله وصحبه وسلَّم
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

09/03/2026

የላቀውና የተጥራራው ጌታችን አሏህ ጊዜያትን የተለያዩ ምዕራፎችና የመልካም ስራ መሸመቻ ቀናቶች አድርጓቸዋል። ለኛም ትልቅ ትሩፋት ያዘለውን የወርሀ ረመዷንን እንድንፆመው ደንግጎብናል።ይህ ወር ከሌሎች ወራት በሙሉ የላቀና እርሱን የመሰለ የታጣለት ነው።

በዚህ ታላቅ ወር በዒባዳ መትጋት ትልቅ እድያና እጣ ነው!
እንቁ የሆኑ የረመዷን ቀናቶችን መጠቀም (በዒባዳ ተግቶ ማሳለፍ) የታላላቅ አሏህን ፈሪ ባሪያዎች መንገድ ነው። ታዲያ ውድ እህትና ወንድሞቼ ይህንን ታላቅ ወር በከንቱና በቸልተኝነት ማሳለፍ ተገቢ አይደለም። ቀንና ሌሊቶቹን እንዲሁ ያለ ምንም ኸይር ሸመታ ማሳለፋ ትልቅ መከልከል ና ከኸይር መራቅ ነው።

ይህ ታላቅ ወር የፆምና የሶላት፣ የምፅዋትና የበጎ ተግባር፣ ቁርአንን ሐርፎችንና ህግጋቶቹን ጠብቀን በእርጋታ የምንቀራበት (ተርቲል) የምናደርግበት ወር ነው። በዚህ በወርሀ ረመዷን ከወትሮው በተለየና በደመቀ መልኩ መሳጂዶች በምዕመናን የሚዋቡበት፣ ከሌሎች ወራቶቾ በበለጠ እራሳቸውን ወንጀል ውስጥ የዘፈቁ ምእመናን ወደ አሏህ የሚመለሱበት፣ በወንጀል ላይ የሚያዘወትሩትም ቆም ብለው የሚያስተነትኑበት፣ አሏህን አምርረው የሚጠይቁበትና ወደርሱ የተዋደቁ ባሪያዎች የልባቸው የሚሞላበት ታላቅ ወር ነው! ይህንን ወር በኸይራት የጨረሰው እና ጊዜያቶቹን በዒባዳ ያሳለፈ ሰው ለርሱ ትልቅ ብስራት አለው!

ይህችን አጭር መልእክት ወደናንተ በማስተላልፍበት ሰአት ደግሞ የረመዷን ቀናቶች ወደ ማብቂያውና መገባደጃው ላይ በመሆናቸው ይበልጥ እንድንነሳሳና የቀሩትን በጣት የሚቆጠሩ ነገር ግን የወሩን ትልቅ በረከት ያዘሉ 10ቱን የረመዷን መጨረሻ ቀናቶች በበለጠ እንድንጠቀምባቸው ለማስታወስም ጭምር ነው።

አሏህ ከከውኑ ሁሉ ያላቃቸውና ያበለጣቸው ያለፈውም የሚመጣውም የተማረላቸው ታላቅ ነቢይ ለነዚህ 10ት የረመዷን መጨረሻ ቀናት የተለየ ትኩረት ይሰጡ ነበር።
እሜቴ ዓኢሻህ (አሏህ መልካም ስራዋን ይውደድላት) ባስተላለፉት ሐዲስ [ነቢዩ የረመዷን 10ት መጨረሻ ቀናት በሚገባበት ጊዜ ትጥቃቸውን ያጠብቃሉ፣ ሌሊቱንም (በዒባዳ) ያነጋሉ፣ ቤተሰቦቻቸውንም ያነቃሉ።] ብዙሀኑ የሐዲስ ሊቃውንት እንዳብራሩት ቀበቷቸውን (ትጥቃቸውን) ያጠብቃሉ ወይም (شَدَّ مِئْزَرَهُ) ሲባል የተፈለገበት ነቢዩ በነዚህ ቀናቶች ከሴቶቻቸወ ያገሉ ነበር ማለት ነው ብለዋል።

በሌላ ዘገባም ከእናታችን ዓኢሻህ እንደመጣልን [ ነቢዩ ከሌሎች ቀናቶች በበለጠ በ10ቱ የረመዷን መጨረሻ ቀናቶች በዒባዳ ይተጉ ነበር። ] ከሚያደርጉት ዒባዳ ውስጥም አብዘሀኛውን ወይንም በከፊል ዑለማዎች አባባል ግማሹን የሌሊት ክፍል በዒባዳ ማሳለፋቸው ይገኝበታል።

አሏህ እንደሳቸው ያላቀው ማንም የለም! የዐለሙ ሁሉ አይነታና መሪ አድርጓቸዋል! ነገር ግን ከዒባዳና አሏህን ከማውሳት ለአፍታም አይታክቱም ነበር። ታዲያ እኛ ደካማና በተለያዩ ወንጀሎች የተዘፈቅን አማኞች በነኝህ በተቀሩት 10ት የረመዷን ቀናቶች ይበልጥ ወደ አሏህ መቅረብና መሀርታን መለመን አይባገባንምን!? አሏህ በነዚህ በየሌሊቱ ከእሳት ነፃ ከሚላቸው ባሪያዎቹ ውስጥ ልንሆን አንከጅልምን!

አዎ በእርግጥም ሞት ወደ ሁላችንም ቅርብና የሚገሰግስ ነው! ለዘላለማዊ ሀገራችን ብርሀንና ነፃ መውጫ የሚሆኑልንን በጎ ተግባራት በይበልጥ እንተግብር። እጥፍ ድርብ ምንዳን የምናገኝባቸውን ቀሪ የረመዷን ቀናቶችም በዒባዳ እንትጋባቸው! ከዱኒያዊ ሰራችንም ከእንቅልፍና ሌሎች አዘናጊ ተግባራት እንቀንስ!

ታላላተቅ የአሏህ ባሪያዎች እንደሚሉት ይህ ረመዷን ምናልባትም የመጨረሻ ፆማችን ሊሆን ይችላል ብለን ማሰብ አለብን ጊዚያቶቹን በአግባቡ ለመጠቀም ይረዳናልና! አሏህ በነኝህ የረመዷን መገባደጃ ቀናት እኛንም፣ መሻይኾቻችንንም እናትና አባቶቻችንንም ከእሳት ቀንበር ነፃ እንዲለን እማፀነዋለሁ። እርሱ በእርግጥ ሰሚታና ዱዐን ተቀባይ ጌታ ነውና!
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

21/02/2026

የጎረቤት ሐቅ

وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا ۖ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا وَبِذِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينِ وَالْجَارِ ذِي الْقُرْبَىٰ وَالْجَارِ الْجُنُبِ وَالصَّاحِبِ بِالْجَنبِ وَابْنِ السَّبِيلِ وَمَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ مَن كَانَ مُخْتَالًا فَخُورًا (النساء ٣٦)

አሏህንም ተገዙ፡፡ በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ በየቲሞችም፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በሩቅ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ንብረት ባደረጓቸው (ባሮች)፣ መልካምን (ሥሩ)። [አን-ኒሳእ 36]

በዚህ የቁርአን አያት የጎረቤትን ሐቅ እንጠብቅ ዘንድ አደራ ተብለናል፣ የጎረቤትን ሐቅ መጠበቅ የሚያመላክቱ የሆኑ አያሌ ነቢያዊ ሐዲሶች ተወስተዋል። የተወሰኑትን እንደሚከተለው ለማየት እንሞክራለን።
እናታችንን አዒሻ ባሰተላለፉት ሐዲስ ሰይዳችን ﷺ እንዲህ ብለዋል ፤

« مَا زَالَ جِبريلُ يُوصِينِي بِالجَارِ حَتَّىٰ ظَنَنْتُ أَنَّهُ سَيُوَرِّثُهُ». متفقٌ عليه.

"ጅብሪል ስለ ጎረቤት ሐቅ ደጋግሞ መከረኝ፤ እንዲያውም [ጎረቤት የጎረቤቱን ንብረት] ያወርሰዋል ብዬ እስክጠረጥር ድረስ።" ።" (ቡኻሪና ሙስሊም )

وعن أبي ذرٍّ رضي الله عنه قال: قال رسولُ الله صلى الله عليه وسلم: «يَا أبَا ذرٍّ، إذا طَبَخْتَ مَرَقَةً فَأَكْثِرْ ماءَها، وَتَعَاهَدْ جِيرَانَكَ». رواه مسلم.

ከአቡ ዘር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተወራው፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺእንዲህ ብለዋል፦

"አቡ ዘር ሆይ! ወጥ[መረቅን] በሰራህ ጊዜ ውሃውን አብዛውና ጎረቤቶችህን አስባቸው (አካፍላቸው)።" -- ሙስሊም ዘግበዉታል

አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሐዲስ ደግሞ ሰይዳችንﷺእንዲህ ይሉናል ፤

مَن كانَ يُؤْمِنُ باللَّهِ والْيَومِ الآخِرِ فَلْيَقُلْ خَيْرًا، أوْ لِيصْمُتْ، ومَن كانَ يُؤْمِنُ باللَّهِ والْيَومِ الآخِرِ فَلْيُكْرِمْ جارَهُ، ومَن كانَ يُؤْمِنُ باللَّهِ والْيَومِ الآخِرِ فَلْيُكْرِمْ ضَيْفَهُ.

"በአላህና በመጨረሻው ቀን ሙሉ ኢማን ያለው ሰው፤ መልካምን ይናገር ወይም ዝም ይበል። በአላህና በመጨረሻው ቀን ሙሉ ኢማን ያለው ሰው፤ ጎረቤቱን ያክብር። በአላህና በመጨረሻው ቀን ሙሉ ኢማን ያለው ሰው፤ እንግዳውን ያክብር።" (ቡኻሪና ሙስሊም )

በአጠቃላይ፣ በእስልምና አስተምህሮ የጎረቤት ሐቅ ዝም ብሎ ማህበራዊ ግዴታ ሳይሆን የሙሉ ኢማን (እምነት) መገለጫና ወደ ጀነት የሚያደርስ ትልቅ በር ነው። ነቢዩ ﷺ ያስተማሩን መመሪያዎች እንደሚያሳዩት፣ ጎረቤትን ማክበር፣ በችግሩ መድረስና ከትንኮሳ መቆጠብ ለአንድ አማኝ አማራጭ የሌላቸው ተግባራት ናቸው።

እውነተኛ ሙስሊም ማለት ጎረቤቱ ከእጁም ሆነ ከአንደበቱ ሰላም ያገኘ ሰው ነው። ባለን ጥቂት ነገር በማካፈልና ለጎረቤታችን ክብር በመስጠት፣ እምነታችንን ማጠናከር ብቻ ሳይሆን በፍቅርና በመተሳሰብ የተገነባ ሰላማዊ ማህበረሰብ መፍጠር እንችላለን። ስለዚህ የጎረቤታችንን ሐቅ መጠበቅ የአላህን ውዴታ የምናገኝበትና የነቢዩን ﷺ ፈለግ የምንከተልበት ተግባራዊ አምልኮ መሆኑን ተረድተን ልንተገብረው ይገባል።

መልካም የረመዷን ወር ይሁንልን

20/02/2026

ቁርአንን በስንት ጊዜ ያኸትማሉ ?

አንድ ሰው ቁርኣን መቅራትን ሊያዘወትርና ሊያበዛ ይገባል። ሰለፎች [አሏህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና] ቁርኣንን በማኽተም የጊዜ ርዝማኔ ላይ የተለያየ ልምድ ነበራቸው።

ኢብኑ አቢ ዳውድ ከአንዳንድ ሰለፎች እንደዘገቡት በየሁለት ወሩ አንድ ጊዜ ያኸትሙ ነበር። አንዳንዶቹ ደግሞ በየወሩ፣ አንዳንዶቹ በየአሥር ቀኑ፣ አንዳንዶቹ በየስምንት ቀኑ፣ አብዛኞቹ ደግሞ በየሰባት ቀኑ ማኸተማቸው ተዘግቧል። እንዲሁም በየስድስት፣ በየአምስት እና በየአራት ቀኑ የሚያኸትሙ ነበሩ።

ብዙዎቹ ደግሞ በየሦስት ቀኑ፣ አንዳንዶቹ በየሁለት ቀኑ፣ ሌሎች ደግሞ በቀንና በሌሊት አንድ ጊዜ ያኸትሙ ነበር። በቀንና በሌሊት ሁለት ጊዜ፣ እንዲሁም ሦስት ጊዜ የሚያኸትሙም ነበሩ። አንዳንዶቹ ደግሞ በቀን አራትና በሌሊት አራት (በድምሩ ስምንት) ጊዜ ያኸትሙ ነበር።

በቀንና በሌሊት አንድ ጊዜ ከሚያኸትሙት መካከል ዑስማን ቢን ዓፋን፣ ተሚም አድ-ዳሪ፣ ሰዒድ ቢን ጁበይር፣ ሙጃሂድ፣ ሻፊዒይና ሌሎችም ይገኙበታል።

በሙዓውያ ዘመን የግብፅ ዳኛ የነበሩት ሱለይም ቢን ዐምር በቀን ሦስት ጊዜ ያኸትሙ ነበር። አቡ በክር ቢን አቢ ዳውድ እና አቡ ዑመር አል-ኪንዲ እንደዘገቡት ደግሞ በአንድ ሌሊት አራት ጊዜ የሚያኸትሙ ነበሩ።

ሸይኽ አቡ ዓብዱረሕማን አል-ሱለሚ እንደገለጹት ኢብን አል-ካቲብ በቀን አራትና በሌሊት አራት ጊዜ ያኸትሙ ነበር።

መንሱር ቢን ዛዳን የተባሉት ታቢዒይ በረመዳን ወር በዙህርና በዓስር መካከል አንድ ጊዜ፣ በመግሪብና በዒሻ መካከልም ሌላ ጊዜ ያኸትሙ ነበር። ሙጃሂድና ዓሊ አል-አዝዲም በረመዳን ወር በመግሪብና በዒሻ መካከል ያኸትሙ ነበር።

በሰላት አንድ ረከዓ ውስጥ ብቻ ቁርኣንን የሚያኸትሚ ብዙ ነበሩ ፤ ከነዚህም መካከል ዑስማን ቢን ዓፋን፣ ተሚም አድ-ዳሪ እና ሰዒድ ቢን ጁበይር በካዕባ ውስጥ በአንድ ረከዓ ያኸትሙ ነበር።

አንድ ጊዜ የሚያኸትሙትም በጣም ብዙ ናቸው፤ ይህም ከዑስማን ቢን ዓፋን፣ ከኢብኑ መስዑድ፣ ከዘይድ ቢን ሳቢት እና ከአቢ ቢን ከዕብ ተዘግቧል። ትክክለኛው ምርጫ ግን እንደየሰው ሁኔታ ይለያያል፦ በጥልቀት በማሰብ ረቂቅ እውቀቶችን የሚረዳ ሰው፣ ሙሉ ግንዛቤ እስከሚያገኝበት ድረስ ንባቡን ሊመጥን ይገባል።

እውቀትን በማስተማር ወይም በሙስሊሞች አጠቃላይ ጉዳይ የተጠመደ ሰውም በኃላፊነቱ ላይ ጉድለት እስካላመጣበት ድረስ ንባቡን እንደ ሁኔታው ይወስናል። ከነዚህ ውጭ የሆነ ሰው ግን ሳይሰለችና ንባቡን ሳያበላሽ የቻለውን ያህል ቢያበዛ ይመረጣል።

በሳምንት አንድ ጊዜ ለሚያኸትሙ ሰዎች አጀማመሩና መጨረሻው በተመለከተ፦ ዑስማን ቢን ዓፋን ጁምዓ ሌሊት (ሐሙስ ምሽት) ጀምረው ሐሙስ ሌሊት (ረቡዕ ምሽት) ያኸትሙ ነበር።

ኢማም አል-ገዛሊ በአል-ኢሕያእ ላይ እንደገለጹት፦ የተሻለው አንዱን ኸትም በሌሊት፣ ሌላኛውን ደግሞ በቀን ማድረግ ነው። የቀኑን ሰኞ እለት በፈጅር ረከዓዎች ወይም ከነሱ በኋላ፣ የሌሊቱን ደግሞ ጁምዓ ሌሊት በመግሪብ ረከዓዎች ወይም ከነሱ በኋላ ቢያደርግ የቀኑንና የሌሊቱን መጀመሪያና መጨረሻ በቁርኣን ይቀበላል።

አት-ቲቢያን ከተሰኘው የነወዊ ኪታብ የተወሰደ

መልካም ረመዷን ይሁንልን 🤲🤲
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

19/02/2026

አንድ ሙስሊም የሆነ ባሪያ ወደ አሏህ ከሚያቃርቡት ታላላቅ ነገራቶች መካከል፣ በተለይም እንደዚህ ባለ ታላቅ ወር፣ ቁርኣንን መቅራት ነው። ቁርኣንን መቅራት የሐቀኛ አማኞች ባህሪ መሆኑ ጥርጥር የለውም፤ የአላህን እዝነትና ችሮታ ለማግኘት ከሚያግዙ ትልልቅ ምክንያቶችም አንዱ ቁርአንን ማንበብ ነው።

አሏህም በሱረቱል ፋጢር እንዲህ ይላል፦

{ إِنَّ الَّذِينَ يَتْلُونَ كِتَابَ اللَّهِ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَأَنفَقُوا مِمَّا رَزَقْنَاهُمْ سِرًّا وَعَلَانِيَةً يَرْجُونَ تِجَارَةً لَّن تَبُورَ(٢٩)لِيُوَفِّيَهُمْ أُجُورَهُمْ وَيَزِيدَهُم مِّن فَضْلِهِ ۚ إِنَّهُ غَفُورٌ شَكُورٌ (٣٠) }

{ እነዚያ የአሏህን መጽሐፍ የሚያነቡ፣ ሶላትንም አስተካክለው ያደረሱ፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ በምስጢርም ኾነ በግልጽ የለገሱ፣ በፍጹም የማትከስርን ንግድ ተስፋ ያደርጋሉ፡፡ (29)} ምንዳዎቻቸውን ሊሞላላቸው፣ ከችሮታውም ሊጨምርላቸው (ተስፋ ያደርጋሉ)፡፡ እርሱ በጣም መሓሪ አመስጋኝ ነውና፡፡(30)

ከአቡ ሙሳ አል-ዐሽዐሪይ በተወራዉ ሐዲስ የአሏህ መልዕክተኛ(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል ፤

مَثَلُ الْمُؤْمِنِ الَّذِي يَقْرَأُ القُرْآنَ مَثَلُ الأُتْرُجَّةِ : رِيحُهَا طَيِّبٌ وَطَعْمُهَا طَيِّبٌ ، وَمَثَلُ الْمُؤْمِنِ الَّذِي لاَ يَقْرَأُ القُرْآنَ كَمَثَلِ التَّمْرَةِ : لاَ رِيحَ لَهَا وَطَعْمُهَا حُلْوٌ ، وَمَثلُ المُنَافِقِ الَّذِي يقرأ القرآنَ كَمَثلِ الرَّيحانَةِ : ريحُهَا طَيِّبٌ وَطَعْمُهَا مُرٌّ ، وَمَثَلُ المُنَافِقِ الَّذِي لاَ يَقْرَأُ القُرْآنَ كَمَثلِ الحَنْظَلَةِ : لَيْسَ لَهَا رِيحٌ وَطَعْمُهَا مُرٌّ

«ቁርኣንን የሚቀራ አማኝ ምሳሌ እንደ ትርንጎ ነው፤ መዓዛዋ ጣፋጭ ነው፣ ጣዕሟም ጣፋጭ ነው። ቁርኣን የማይቀራ አማኝ ምሳሌ ደግሞ እንደ ተምር ነው፤ መዓዛ የላትም፣ ጣዕሟ ግን ጣፋጭ ነው። ቁርኣን የሚቀራ መናፍቅ ምሳሌ እንደ አሪቲ ነው፤ መዓዛዋ ጣፋጭ ነው፣ ጣዕሟ ግን መራራ ነው። ቁርኣን የማይቀራ መናፍቅ ምሳሌ ደግሞ እንደ እምቧይ ነው፤ መዓዛ የላትም፣ ጣዕሟም መራራ ነው።» ቡኻሪ ዘግበዉታል

እንግዲህ ከላይ በቀረበው የነብያችን(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሐዲስ መሰረት ራሳችንን መገምገም ያስፈልጋል። ከየትኛዉ ደረጃ ላይ እንዳለን ልናዉቅና ተሽሎ ለመገኘት መጣር ይገባናል።

ቁርዐንን መቅራት የረህመት እንዲሁም የእዝነት ሰበብ ነው። ተከታዩን የሰይዳችንን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሐዲስ እስኪ እንመልከት ፤

«ما اجتمع قوم في بيت من بيوت الله يتلون كتاب الله ويتدارسونه فيما بينهم إلا نزلت عليهم السكينة ، وغشيتهم الرحمة ، وحفتهم الملائكة ، وذكرهم الله فيمن عنده» رواه مسلم .

«ሰዎች ከአላህ ቤቶች በአንዱ ውስጥ ተሰብስበው፣ የአሏህን መጽሐፍ እያነበቡና በመካከላቸውም እየተማማሩ አይቀመጡም፤ መረጋጋት ቢወርድላቸው፣ እዝነት ቢሸፍናቸው፣ መላእክት በክንፎቻቸው ቢያከቧቸውና አላህ በዘንድ ከተላቁት መላእክት ዘንድ ስማቸውን ቢጠቅስላቸው እንጂ።» (ሙስሊም ዘግበውታል)

ተከታዩ የሰይዳችን ሐዲስ ደግሞ ለቁርዐንን ያለንን ፍቅር ይጨምራል፤ እንዲህ ይላሉ፤

« مَنْ قَرَأ حَرْفاً مِنْ كِتَابِ اللهِ فَلَهُ حَسَنَةٌ ، وَالحَسَنَةُ بِعَشْرِ أمْثَالِهَا ، لاَ أقول : {ألم} حَرفٌ ، وَلكِنْ : ألِفٌ حَرْفٌ ، وَلاَمٌ حَرْفٌ ، وَمِيمٌ حَرْفٌ» رواه الترمذي

«ከአሏህ መጽሐፍ(ቁርዐን) አንድን ፊደል ያነበበ ሰው ለእርሱ አንድ መልካም ስራ አለው፤ መልካም ስራ ደግሞ በአሥር እጥፍ ናት። {አለም} አንድ ፊደል ነው አልልም፤ ነገር ግን አሊፍ ፊደል ነው፣ ላም ፊደል ነው፣ ሚምም ፊደል ነው።» ቲርሚዚይ ዘግበዉታል።

ቁርዐንን መቅራት በአኺራ ምላጃ እንደሚያገኝ ዉዱ ነብያችን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ነግረዉናል ፤

«اقْرَؤُوا القُرْآنَ ؛ فَإنَّهُ يَأتِي يَوْمَ القِيَامَةِ شَفِيعاً لأَصْحَابِهِ»

«ቁርኣንን ቅሩ (አንብቡ)፤ እርሱ በትንሳኤ ቀን ለባልደረቦቹ (ለሚያነቡት) አማላጅ ሆኖ ይመጣልና።»

ስለ ቁርዐንን ማንበብ የተወሱ ሐዲሶች አያሌ ናቸው። ለማስታወስ ያህል ከላይ ያሉትን ጠቅሰናል። ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ ከመቼው ጊዜ በተለየ በዚህ የረመዷን ወር ቁርዐንን በማንበብ እንድንጠናከር ላስታዉሳችሁ እወዳለሁ።
ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

18/02/2026

የፆም አርካን የሆኑትን ኒያ ማድርግና እና ከሚያስፈጥሩ ነገራቶች መታቀብ ፆማችን ትክክል ይሆን ዘንድ መገኘታቸው ግዴታ ነው። ከእነዚህ ግዴታዎች በኋላ ደግሞ ሱና የሆኑ ተግባራት ይኖራሉ።እነሱም የጾመኛውን ምንዳ ከፍ የሚያደርጉተግባራት ናቸው። ከነቢዩﷺ የተገኙና ሙስሊሙ በረመዳን ወር ከፍተኛ መንፈሳዊነት እንዲያገኝ የሚረዱ ብዙ ሱናዎች አሉ፤ ዋና ዋናዎቹም፦

1. ሱሁርን መመገብ

ሱሁር ሙስሊሙን ለጾም ያግዘዋል፣ ረሃብንና ጥማትን ለመቋቋም ጉልበት ይሰጠዋል፤ እንዲሁም የሙስሊሞችን ጾም ከቀደምት ኪታብ ባለቤቶች ጾም የሚለይ ዋና ነገር ነው።

ነብያችንﷺ እንዲህ ብለዋል፤

“تسحروا فإن في السحور بركة” (متفق عليه).
“ሱሁርን ብሉ፤ በሱሁር ውስጥ በረካ(አጅር) አለና።” (ቡኻሪና ሙስሊም)

2. ሱሁርን ማዘግየት

ከሚወደዱ የጾም ሱናዎች አንዱ ሱሁርን ለፈጅር ጥቂት ጊዜ እስከሚቀረው ድረስ ማዘግየት ነው። ሆኖም ግን የፈጅር ክፍለ ጊዜ ዉስጥ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።

ዉዱ ነብያችንﷺ እንዲህ ይሉናል፡

“لا تزال أمتي بخير ما عجّلوا الفطر وأخّروا السحور” (رواه أحمد).
“ሕዝቦቼ ፊጥርን እስካቻኮሉና ሱሁርን እስካካዘገዩ እስከቆዩ ድረስ በመልካም ነገር ላይ ከመሆን አይወገዱም።” አህመድ ዘግበዉታል።

3. ፊጥርን ማቻኮል

በረመዳን ከነቢዩ ﷺ ሱናዎች አንዱ ጀንበር መግባቷ ከተረጋገጠ በኋላ ፊጥርን ማጣደፍና አለማዘግየት ነው። ነብያችን ﷺበቴምር ያፈጥሩ ነበር፤ ካላገኙ ደግሞ በውሃ ያፈጥሩና የመግሪብ ሶላትን ይሰግዳሉ።

ሰይዳችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

“لا يزال الناس بخير ما عجَّلوا الفطر” (متفق عليه).
“ሰዎች ፊጥርን እስካቻኮሉ ድረስ በበጎ ነገር ላይ ናቸው።” (ቡኻሪና ሙስሊም)።

4. ሲያፈጥሩ ዱዓ ማድረግ፦

ጾመኛ የሆነ ሰው ሲያፈጥር ዱዓ ሊያደርግ ይወደድለታል፤ ምክንያቱም ጾመኛ ሲያፈጥር የሚያደርገው ዱዓ ተቀባይነት እንደሚኖረው በሐዲስ ተወስቷል። ነብያችን ﷺ ሲያፈጥሩ እንዲህ ይሉ ነበር ፤

“ذهب الظمأ، وابتلت العروق، وثبت الأجر إن شاء الله” (رواه أبو داود).
“ጥማት ተወገደ፣ የደም ስሮች ረጠቡ፣ አላህ ቢፈቅድ ምንዳውም ጸና።” አቡ ዳውድ ዘግበዉታል

5. የአካል ክፍሎችን መጠበቅ፦

ምላስን ከከንቱ ንግግር፣ ዓይንን ከተከለከሉ ነገሮች መጠበቅ፤ ጆሮን የተከለከሉ ነገሮችን ከመስራት ፤ እጅና እግርን ከመጥፎ ነገራቶች ማቀብ ይገባል ። ይህም ጾምን እውነተኛ የነፍስ ማጥሪያ ያደርገዋል።

6. ፆመኛን ማስፈጠር፦ ሰይዳችን ﷺ ጾመኞችን በማስፈጠር ላይ አበረታተዋል፤

ነብያችንﷺ እንዲህም ብለዋል፦

“مَن فطّر صائمًا كان له مثل أجره، غير أنه لا ينقﷺص من أجر الصائم شيء” (رواه الترمذي)
“ጾመኛን ያስፈጠረ ሰው የጾመኛውን ያክል(ትልቅ) ምንዳ አለው፤ ከጾመኛው ምንዳ ላይ ምንም ሳይቀነስ።” ቲርሚዚይ ዘግበዉታል

7. የተራዊሕ ሶላትን መስገድ

ከዋና ዋና የረመዷን ጾም ሱናዎች የተራዊህ ሶላትን መስገድ ይገኝበታል። የተራዊህ ሶላት ከኢንሻ ሶላት በኋላ የሚሰገድ ሶላት ሲሆን ሃያ(20) ረከዐ ነው።

አይነታችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፤
“مَن قام رمضان إيمانًا واحتسابًا غُفر له ما تقدم من ذنبه” (متفق عليه).
“በረመዳን ያመነና ከአሏህን ምንዳን በመከጀል የቆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉ ይማርለታል።” (ቡኻሪና ሙስሊም)

8. ሌሊትን በዒባዳ ማሳለፍና ለይለተል ቀድርን መፈለግ

በረመዳን ቀናት ሌሊቱን በዒባዳ ማሳለፍና ለይለተል ቀድርን መፈለግ ትልቅ የሆነ ሱና ነው።

የአይናችን ማረፊያ ﷺ ነቢዩ እንዲህ ይሉናል፤
“مَن قام ليلة القدر إيمانًا واحتسابًا غُفر له ما تقدم من ذنبه” (متفق عليه).
“ያመነና ከአሏህን ምንዳን በመፈለግ ለይለተል ቀድርን በኢባዳ ያሳለፈ ሰው ያለፈው ወንጀሉ ይማርለታል።” (ቡኻሪና ሙስሊም)

9. በመጨረሻዎቹ አሥር ቀናት የበለጠ መጠናከር

ትልቅ ሰው ﷺ በመጨረሻዎቹ አሥር የረመዳን ቀናት በኢባዳ ይጠነክሩ ፤ ቤተሰቦቻቸዉን እንዲሁም መስጂድ ውስጥ ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር።

10. መልካም ስራዎችን ማብዛት፦ እንደ ቁርኣን ንባብ፣ ዝክር፣ ሰደቃና መልካም ስራዎችን ማብዛት።

በድጋሜ ረመዷን ከሪም

ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

17/02/2026

((يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ)) البقرة ١٨٣

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነገገ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡” አል-በቀራ 183

በመጀመሪያ ደረጃ እድሜና ጤና ሰጥቶ፣ ከዓመት እስከ ዓመት በምህረቱ ጠብቆ፣ ለዚህ እጅግ ብሩህና የተባረከው የረመዷን ወር ላደረሰን ለዓለማቱ ጌታ ለአሏህ ምስጋና ይግባው እያልኩኝ፤ እንኳን ለ1447ኛው የረመዷን ፆም በሰላምና በጤና በሰላም አደረሳችሁ።

ይህ ወር በዓመት ውስጥ አንዴ ብቻ የምናገኘው ታላቅ የጸጋ ጊዜ በመሆኑ፣ ከቀናት ቆጠራ በላይ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው፣ ከምግብና መጠጥ መታቀብ በላይ የነፍስ ስንቅ የሚሰበሰብበትና የፈጣሪ እዝነት እንደ አባይ ፈሳሽ በምድር ላይ የሚፈስበት ልዩ ወቅት ነው።

ረመዷን ልባችንን ካለፈው ቂምና ጥላቻ የምናጥብበት፣ የታመሙትንና የተቸገሩትን ወገኖቻችንን በዱዓም ይሁን በተግባራዊ ልግስና የምናስብበት፣ እንዲሁም በቅዱስ ቁርኣን ብርሃን ታጅበን ወደ ፈጣሪያችን በቅን ንስሐ የምንቀርብበት የወራት ሁሉ ንጉሥ በመሆኑ ሁላችንም ልንጠቀምበት ይገባል።

በዚህ በተባረከ ወር ውስጥ የምታደርጓቸው እያንዳንዱ ሱጁዶች፣ የምታነቧቸው አንቀጾችና የምታደርጓቸው ዱዓዎች በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነትን አግኝተው፤ ቤታችሁ በበረከት፣ ጓዳችሁ በሲሳይ፣ ህይወታችሁ ደግሞ በአዲስ ተስፋና በሰላም እንዲሞላ ከልቤ እመኛለሁ። አላህ ፆሙን በሰላም የምንጨርስ፣ ከእሳቱ ነፃ የምንሆንና ለዒድ በዓል በደስታ የምንደርስ ያድርገን።
ረመዷን ሙባረክ! 🌙

ሸይኽ ዑመር ኢማም /Sheikh Umar Imam

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Addis Ababa