ሰላም ለሁላችሁ
ይህ ፌስ ቡክ ከብዙ የሀሳብ ውጣ ውረድ በኋላ የተከፈተ ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ ጊዜያት ፈተናዎች ገጥሟታል በዚህም በጸሎት በምህላ በምእመናን እና በአገልጋይ በቅዱሳን ጸሎት በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት በመላእክት ጥበቃ በአምላካችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ምህረትና ቸርነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ከነሙሉ ክብሯ እዚህ ዘመን ደርሳለች በአለም ፈተና የማይቀርና የክብር አክሊልን እንደሚያስገኝ ብናውቅም እጅግ አደገኛ የሆኑ ፈተናዎች ግን ትውልድን የሚመርዙ ስርዓት የሚያፋልሱ የሰው ልጅን ከተፈጠረበት ዓላማ የሚያስወጡ ከጽድቅ መንገድ የሚያርቁ ብዙ የሰው ልጅን ለሲኦል የሚያዘጋጁ ሆነው ሲገኙ እጅግ ከባድ ናቸው ስለዚህ በአፈታሪክ፣በመጽሐፍ፣በቃል የተሰበከልንን አንድ ሃይማኖታችንን ኦርቶዶክሳዊት ቀጥተኛዋና ዘላለማዊ ሕይወት የምታሰጠዋን እምነታችንን የውጭ ፈተናን ተቋቁማ እያለች በራሷ ልጆች እና ልጆቿ መስለው ውስጧ ባሉ አገልጋዮችና ምእመናን መፈተን ግን ከሁሉም የከፋ ነው ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት የቤተክርስቲያናችንን ሥርዓት ቀኖና በተቻለን መጠን ከሊቃውንት አባቶች ጋር በመመካከር ከመጽሃፍ ቅዱስ በማመሳከር አካሄዳቸው ከስርዓተ ቤተክርስትያን ያፈነገጡ አገልጋዮችንና ምዕመናን የምንገስፅበት የምንማማርበት እንዲሆን በማሰብ ከፌስቡክ በተጨማሪ ‘’ስለ ጽዮን ዝም አልልም” በሚል ቲክ ቶክ የተለያዩ ምስሎችንና ድምጽን በማጋራት በመረጃ በቅንነት ለቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መከበር ለሚያስቡ ሁሉ አካውንቱ ክፍት ሆኖ ያገለግላል አብሮነታችሁ አይለየን።
ስርዓተ ቤተክርስቲያንን አክብረን እናስከብር ዘንድ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን አሜን።
ስለ ጽዮን ዝም አልልም Sile Tsion Zim Alilm.
ስርዓተ ቤተክርስቲያን
"ስለ ጽዮን ዝም አልልም ስለ ኢየሩሳሌምም ጸጥ አልልም ጽድቋ እንደ ጸዳል መዳኗም እንደሚበራ ፋና እስኪወጣ ድረስ" ኢሳ ም 62:1
06/01/2025
"እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ "
Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
Addis Ababa