ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት

ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት

Share

ተንቢሀት - የተለያዩ ኢስላማዊ ትምህርቶች የሚቀርቡበት ፔጅ Important Lessons for muslimah
see also
www.facebook.com/fatawa.lmar2a.lmoslima

08/01/2026

حلمكِ بأن تكوني "طالبة في الحرم" أصبح بين يديكِ.. وأنتِ في منزلك! ✨ الحلم الذي لم تعرفه الكثيرات! 🕋
يا أخواتي الكريمات، كثير من البنات يظنّون أن نيل شرف طلب العلم في رحاب الحرم المكي أو النبوي يتطلب السفر أو الإقامة هناك.. لكن المعلومة التي قد تغير حياتكِ ومساركِ العلمي هي أن الحرم الآن يأتي إليكِ أينما كنتِ! 🌍

ما هو موقع "وقار الحرم"؟ 🎓
هو جسرُكِ الإيماني لتصبحي طالبة رسمية، تحضرين الحلقات والدروس العلمية "أونلاين" مباشرة، دون اشتراط الحضور الجسدي في معهد الحرم.

لماذا هذه الفرصة لا تُعوض؟

بالمجان تماماً: العلمُ متاح لكل طالبة حق، بلا أي رسوم.

مرونة تامة: يمكنكِ اختيار المواعيد التي تناسب جدولكِ وحياتكِ اليومية.

شهادة وعلم: تنهلين من دروس كبار العلماء والمحفظات في أطهر بقاع الأرض.

كيف تبدئين الرحلة؟ 📝
التقديم متاح عبر الرابط الرسمي لمنصة "وقار، والرابط في التعليق الأول

💡 ملاحظة هامة جداً: التقديم يفتح رسمياً مع بداية العام الدراسي، لذا كوني مستعدة!

نصيحة من القلب: لا تتركي هذه المعلومة تقف عندكِ، فالدال على الخير كفاعله. احفظي المنشور (Save) وشاركيه مع كل صديقة أو أخت تحلم بالعلم الشرعي لعلّكِ تكونين سبباً في وصلها برحاب الحرم. 🕊️🌿




رابط التسجيل هنا :
https://reg.qm.edu.sa/Minton/Account/NewRegistration

19/11/2025

ሸሪዓዊ ልባስ!
🖌 ኢልያስ አሕመድ
{لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ}
––––––––––––
(ዝርዝር ማስረጃዎችን ለመናድ ጥቅል አንቀፆችን በማቅረብ ፍልስፍናዊ መነሻዎችን ሸሪዓዊ ልባስ የማልበስ ስልት)

🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹

በሰለፎች ምልአተ ድምፅ የተኮነነው የጀህሚያው የተዕጢል መስመር ጠንሳሾችንና አቀንቃኞችን በቁርኣንና በሐዲሥ በተደጋጋሚ የፀደቁትን የፈጣሪ ዝርዝር መገለጫዎችን መልእክት ለመቆልመም ያበቃቸው እውነተኛ መነሻ ፍልስፍናዊ እንጂ ሸሪዓዊ አይደለም። (ዝርዝሩን በሌላ ጊዜ እንመለስበት ይሆናል።)
ሆኖም አብዛኛዎቹ ብዙሃኑን ለመሸንገል በየአጋጣሚው የሚያነሷቸው አንዳንድ ጥቅል ጥቅሶች እንዳሉ ይታወቃል! አንድ የቁርኣን አንቀፅን በምሳሌነት እንውሰድ፦
{ لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ }
[سُورَةُ الشُّورَىٰ: ١١]
⇛«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው።» [አሽ-ሹራ 11]

ለምሳሌ፡‐ አላህ በዐርሹ በላይ ከፍ ያለ መሆኑን የሚያረጋግጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ማስረጃዎች ይዘት ላለመቀበላቸው፣ በአንፃሩም «አላህ ያለ ቦታ ነው ያለው!» ለተሰኘው መጤ መፈክራቸው ማስረጃ ሲጠየቁ ይህን የማይገናኝ አንቀፅ ይጠቅሳሉ!

የዚህን የመረጃ አቀራረብ ግድፈትና የአንቀፁን ትክክለኛ መልእክት የሚያጎሉ በአጭሩ እነሆ፡‐

1⃣ ይህንና መሰል ጥቅል የቁርኣን አንቀፆችን ያወረደው ጌታ ሌሎች ባህሪያቱ የተረጋገጡባቸውን ዝርዝር አንቀፆችንም ያወረደው ጌታ ራሱ ስለሆነ የሚጋጩ መልዕክቶች ሊኖሯቸው አይችልም! ስለዚህ በሁሉም ማመን ግዴታ ነው። ይህ የሚቻለው ደግሞ ሁሉንም ባህሪያቱን ከምንም ጋር ሳያመሳስሉ ለርሱ ማንነት በሚገባ መልኩ በማፅደቅ ብቻ ነው።
ይህን የሚያፀናው ደግሞ፡‐

2⃣ ሰለፎች ከዚህኛውና ከመሰል ጥቅል አንቀፆች ለአላህ በማስረጃ የተረጋገጡትን የትኞቹንም ባህሪያት መልእክት በልዩ ዘይቤ መቀየር እንደሚያስፈልግ አልተረዱም፤ ይህንም አልተገበሩም! የሁሉንም ማስረጃዎች መልእክቶች አጣጥመው እምነታቸውን እንዳራመዱ በሚያሳዩ ዘገባዎች መዛግብት ተሞልተዋል። እነርሱ ስለ ቁርኣን መልእክትና ለአላህ ስለሚገባው መገለጫ ከኋለኞች የተሻለ እንደሚገነዘቡ ግልፅ ነው።

3⃣ ስለባህሪያቱ ሁኔታ ሳያነሱ መልዕክታቸውን ለርሱ ብቻ በሚገባ መልኩ ማፅደቅ አላህ ውድቅ ያደረገው ማመሳሰል (تشبيه) ውስጥ እንደማይካተት የታወቀ ነው፤
📌 አል-ኢማም አት-ቲርሚዚይ (279 ዓ.ሂ) እንደሚያስተላልፉት ታላቁ የሙስሊሞች ኢማም (161 – 238 ዓ.ሂ) እንዲህ ብለዋል፦
إِنَّمَا يَكُونُ التَّشْبِيهُ إِذَا قَالَ: يَدٌ كَيَدٍ أَوْ مِثْلُ يَدٍ، أَوْ سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ. فَإِذَا قَالَ: سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ فَهَذَا التَّشْبِيهُ، وَأَمَّا إِذَا قَالَ- كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى-: يَدٌ، وَسَمْعٌ، وَبَصَرٌ، وَلاَ يَقُولُ: كَيْفَ، وَلاَ يَقُولُ: مِثْلُ سَمْعٍ وَلاَ كَسَمْعٍ، فَهَذَا لاَ يَكُونُ تَشْبِيهًا. وَهُوَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى فِي كِتَابهِ: {لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡبَصِيرُ}
«ማመሳሰል የሚሆነው “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት እጅ”፣ “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት መስማት” ሲባል ነው፤…ነገር ግን አላህ እንደተናገረው “እጅ፣ መስማት፣ ማየት” ብሎ “እንዴት” ካላለ፣ “እንዲህ አይነት፣ እንዲያ ያለ መስማት..” ካላለ ማመሳሰል አይሆንም! አላህ ራሱ በመፅሃፉ እንዳለው ‘እንደርሱ ያልለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው’ »
[“ሱነኑ’ት-ቲርሚዚይ”፤ ኪታቡ’ዝ-ዘካህ፤ ከሐዲሥ ቁጥር (662) ቀጥሎ]

4⃣ የስያሜ መገጣጠም የሁኔታና የይዘትን መመሳሰል አያመላክትም! አላህ አዋቂ ከመሆኑ ጋር ከፊል ፍጡራንን አዋቂ ሲል ጠርቷል፤ ሰሚና ተመልካች ከመሆኑም ጋር ሌሎችን በእነዚህ ስያሜዎች ጠርቷል… ሌሎች ለራሱ ያፀደቃቸውን ባህሪያትም ለፍጡራኑ አፅድቋል፤ ምሳሌዎቹ እጅግ ብዙ ናቸው።
እነኚህ የተዕጢል ወገኖቻችን በግርድፉም ቢሆን የሚያፀድቋቸው ጥቂት ባህሪያት ፍጡራንም ሊጠሩባቸው የሚችሉ ናቸው።

ታዲያ አላህ አምሳያ የለውምና እነኚህንም መገለጫዎቹን እናስተባብል? ወይስ የፍጡርን ባህሪ ለማንነቱ በሚገባ ሁኔታ እንደምናፀድቀው የፈጣሪን ባህሪይ ለማንነቱ በሚገባ ልዩ መልኩ አረጋግጠን እንለፍ?
በተጨማሪም፦

5⃣ በአንቀፁ مِثۡل «አምሳያ» ውድቅ መደረጉ የባህሪያቱን ጥቅል ቋንቋዊ መልእክት መጋራትን አይከለክልም። አላህ አምሳያ (مِثۡل) እንደሌለው እንደጠቀሰው ሁሉ ከፍጡራን መካከልም አምሳያ (مِثۡل) እንደሌላቸው በቁርኣን የተወሱ ነገሮች አሉ፤ ሆኖም በስያሜና በጥቅል መልእክት የሚጋሯቸው ፍጡራን መኖራቸው አይካድም። ለምሳሌ፦

إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ ۝ ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ ۝

⇛«ባለ ረጃጅም ምሰሶዎች የሆነችዋ ‘ኢረም’፤ #አምሳያዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ የሆነችዋ» [አል-ፈጅር 8-9]

ሌሎች ባለ ምሰሶ አገሮች መኖራቸው ግልፅ ነው። አገራቱ በዝርዝር ይዘት መለያየታቸው የየትኛውንም አገር አገርነት አይሽርም፤ የአገራቱንም መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት ሊሆን አይችልም!

ሌላ ምሳሌ፡‐
وَإِن تَتَوَلَّوۡاْ يَسۡتَبۡدِلۡ قَوۡمًا غَيۡرَكُمۡ ثُمَّ لَا يَكُونُوٓاْ أَمۡثَٰلَكُم [محمد: 38]
⇛ «(በእንቢታ) ብትዞሩ ከናንተ ሌላ ህዝቦችን ይተካል፤ ከዚያም #አምሳያዎቻችሁ አይሆኑም።» [ሙሐመድ 38]

ተኪዎቹም፣ ተተኪዎቹም እጅግ ብዙ ባህሪያትን በጥቅሉ የሚጋሩ ፍጡራን (ሰዎች) ከመሆናቸው ጋር ከፊሎቹ የሌሎቹ አምሳያዎች እንዳልሆኑ በግልፅ ተወስቷል። ሆኖም ይህ ሁሉም ሰዎች የመሆናቸውን እውነታና የሚጋሯቸውን ጥቅል መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት አይሆንም።
ስለዚህ ውድቅ የተደረገው “አምሳያ” (مِثۡل) ወይም “መመሳሰል” ለሁሉም ማንነቱን የሚመጥን ባህሪን እንድናፀድቅ ያደርገናል እንጂ የአንደኛውን ባህሪይ መሰረታዊ መልእክት እንድናዛባ አያስገድደንም።

6⃣ የላይኛው አንቀፅ ሁለት ዋና ዋና መልእክቶችን አዝሏል፦
«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» የሚለው የአንቀፁ የመጀመሪያ ክፍል ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በምንም መልኩ ማመሳሰል ውድቅ መሆኑን የሚያስገነዝብ ሲሆን፤
«እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው» የሚለው መቋጫ ደግሞ መስማትና ማየትን ጨምሮ ለአላህ በመረጃ የተረጋገጡትን ስሞችና ባህሪያት ተቀብሎ ማፅደቅ የግድ መሆኑን ይጠቁማል።

📌 አቡ መንሱር አል‐አስበሃኒይ (በ418 ዓ.ሂ ያለፉ) የአንቀፁን ትክክለኛውን መልእክት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡‐
فـ{لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ} يَنْفِي كلَّ تَشْبِيه وتمثيل، {وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ} يَنْفِي كلَّ تَعْطِيل وَتَأْويل، فَهَذَا مَذْهَب أهل السّنة وَالْجَمَاعَة والأثر
«{እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤} = ሁሉንም የማመሳሰል ደረጃ (ተሽቢህ እና ተምሢል) ውድቅ ያደርጋል። {እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው} = ሁሉንም የባህሪውን መልእክት ያለመቀበልና የመቀየር ስልትን (ተዕጢልና ተእዊል) ውድቅ ያደርጋል! ይህ የሱንና እና የጀማዓህ እንዲሁም የአሠር (የትክክለኛ ትውፊት) ተከታዮች መንገድ ነው።»
[“አል‐ሑጅ‐ጃህ ፊ በያኒል‐መሐጅጀህ” (1/260)]

ስለሆነም የአንቀፁ መረጃነቱ ለኛ እንጂ ለነርሱ አይደለም! የዚህን አንቀፅ መልእክት ራሱ በትክክል ተግባራዊ አድርገው ቢሆን ወደ እውነተኛው ጎዳና በተመሩ ነበር! ይህን የሚያብራራው ደግሞ የሚቀጥለው ነጥብ ነው፦

7⃣ አንድ ነገር የሚወደሰው በመገለጫዎቹ ምጥቀት እንጂ በባህሪ-አልባነቱ እንዳልሆነ ግልፅ ነው! «እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» ማለቱ ውዳሴ በመሆኑ የመለያ ባህሪያቱን ብዛት እንጂ ተቃራኒውን ሊያመላክት አይችልም! ምክንያቱም ቃሉ የሚያሳየው ባህሪያት እንደሌሉት ቢሆን ኖሮ ባዶነትን የሚጠቁም ይሆን ነበር፤ ባዶነት ደግሞ እንደስያሜው ባዶነትን እንጂ ምሉዕነትን የሚያስጨብጥ አይደለም።

8⃣ እንደነሱ አባባል አላህ እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ በተለያዩ ስልቶች ራሱን የገለፀባቸውን ጉልህ መልዕክቶች መቀበል እንደሌለብን የሚያመላክተን እንዲህ በደፈናው አምሳያ እንደሌለው በመንገር ብቻ ከሆነ ንግግሩ በብዙኃኑ ሙስሊሞች የማይፈታ የቅኔ ቋጠሮ ነው ማለት ነው!! ቃሉ ከእንዲህ ያለ መድበስበስ ፍፁም ለጠራውና ለላቀው ጌታችን ምስጋናና ውዳሴ የተገባ ነው!
ለመሆኑ! የላይኛውን ጥቅል አንቀፅ እንደ መረጃ አጣቅሶ አላህ ራሱን በተደጋጋሚ የገለፀበትን እዝነት፣ ቁጣ፣ መውደድ፣ መጥላት፣ መናገር፣ በዐርሹ ላይ መሆን፣ ፊት፣ እጅ.. እና ሌሎች በጣም ብዙ መገለጫዎችን በአንድ ስንዝር መደምሰስ እኮ አላህ በምድር ላይ ያለውን ነገር ሁሉ ለኛ እንደፈጠረልን የተናገረበትን ጥቅል አንቀፅ (አል‐በቀራህ 29) ተመርኩዞ እንደ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥ፣ የአሳማ ስጋን መብላት.. ያሉ ግልፅ ሸሪዓዊ ክልከላዎችን ከማስተባበል የከፋ ነው። ምክንያቱም አላህ ስለራሱ የገለፀባቸው አንቀፆች ስለ ሐላልና ሐራም ህግጋት ከገለፀባቸው ይበልጥ የጐሉና የበዙ ናቸውና!
……………………

በጥቅሉ በተለያዩ ቁርጠኛ ማስረጃዎች የተረጋገጡትን የአላህን መገለጫዎች ቀጥተኛ መልእክት ለመቆልመም አላህ አምሳያ እንደሌለው የሚያስገነዝቡ ጥቅል ማስረጃዎችን ማቅረብ ግልፁን ትቶ አሻሚን የማፈላለግ ውጤት ነው! ይህ ደግሞ ልባቸው በጥመት በሽታ የተወረሰ ሰዎች ምልክት ነው። በተቃራኒው የእውቀትና የፅኑ እምነት ባለቤቶች ምልክት ከጌታቸው ዘንድ ለሚመጣ ማንኛውም ማስረጃ እጅ መስጠታቸው ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፦
هُوَ ٱلَّذِيٓ أَنزَلَ عَلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ مِنۡهُ ءَايَٰتٞ مُّحۡكَمَٰتٌ هُنَّ أُمُّ ٱلۡكِتَٰبِ وَأُخَرُ مُتَشَٰبِهَٰتٞۖ فَأَمَّا ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمۡ زَيۡغٞ فَيَتَّبِعُونَ مَا تَشَٰبَهَ مِنۡهُ ٱبۡتِغَآءَ ٱلۡفِتۡنَةِ وَٱبۡتِغَآءَ تَأۡوِيلِهِۦۖ وَمَا يَعۡلَمُ تَأۡوِيلَهُۥٓ إِلَّا ٱللَّهُۗ وَٱلرَّٰسِخُونَ فِي ٱلۡعِلۡمِ يَقُولُونَ ءَامَنَّا بِهِۦ كُلّٞ مِّنۡ عِندِ رَبِّنَاۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّآ أُوْلُواْ ٱلۡأَلۡبَٰبِ [آل عمران: 7]
⇛ «እርሱ ባንተ ላይ መፅሐፉን ያወረደው ነው፤ ከርሱ ፍፁም የሆኑ (ግልፅ) አንቀፆች አሉ፤ እነሱም የመፅሐፉ ‘እናት’ (መሠረትና ዋነኛ መገለጫ) ናቸው፤ ሌሎች (ደግሞ) ”ሙተሻቢህ” (በአንፃሩ አሻሚ ገፅታ ያላቸው) ናቸው፤ እነዚያ በልባቸው ጥመት ያልለ ፈተናን በመፈለግና “ተእዊሉን”( ) በመፈለግ የተመሳሰለውን (አሻሚውን) ይከታተላሉ፤ "ተእዊሉን" ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም፤ በእውቀት ውስጥ የሰረፁትም “ ፤ ” ይላሉ..» [ኣሊ ዒምራን 7]

ተወዳጁ መልእክተኛ (ﷺ) ይህንን አንቀፅ አንብበው እንዲህ ብለዋል፦
إِذَا رَأَيْتُمُ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ، فَأُوْلَائِكَ الَّذِينَ سَمَّى اللهُ؛ فَاحْذَرُوهُمْ
⇛«አነዚያ ከርሱ (ከቁርኣን) የተመሳሰለውን (አሻሚ ሆኖ ያገኙትን) የሚከታተሉትን ካያችሁ አላህ (በአንቀፁ) የጠቀሰው እነሱኑ ነውና ተጠንቀቋቸው!»
[አል-ቡኻሪይ (4547)፣ ሙስሊም (2665) ላይ ከእናታችን ዓኢሻህ እንደተላለፈው።]

አላህ ቀናውን መንገድ ይምራን!



©: በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1391785995651967&id=100044617380985&mibextid=Nif5oz

ሸሪዓዊ ልባስ!
{لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ}
––––––––––––
(ዝርዝር ማስረጃዎችን ለመናድ ጥቅል አንቀፆችን በማቅረብ ፍልስፍናዊ መነሻዎችን ሸሪዓዊ ልባስ የማልበስ ስልት)

🖌 ኢልያስ አሕመድ
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹

በሰለፎች ምልአተ ድምፅ የተኮነነው የጀህሚያው የተዕጢል መስመር ጠንሳሾችንና አቀንቃኞችን በቁርኣንና በሐዲሥ በተደጋጋሚ የፀደቁትን የፈጣሪ ዝርዝር መገለጫዎችን መልእክት ለመቆልመም ያበቃቸው እውነተኛ መነሻ ፍልስፍናዊ እንጂ ሸሪዓዊ አይደለም። (ዝርዝሩን በሌላ ጊዜ እንመለስበት ይሆናል።)
ሆኖም አብዛኛዎቹ ብዙሃኑን ለመሸንገል በየአጋጣሚው የሚያነሷቸው አንዳንድ ጥቅል ጥቅሶች እንዳሉ ይታወቃል! አንድ የቁርኣን አንቀፅን በምሳሌነት እንውሰድ፦
{ لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ }
[سُورَةُ الشُّورَىٰ: ١١]
⇛«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው።» [አሽ-ሹራ 11]

ለምሳሌ፡‐ አላህ በዐርሹ ላይ ከፍ ያለ መሆኑንና ሌሎች መገለጫዎቹን የሚያረጋግጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ማስረጃዎች ይዘት ላለመቀበላቸው፣ በአንፃሩም «አላህ ያለ ቦታ ነው ያለው!» ለተሰኘው መጤ መፈክራቸው ማስረጃ ሲጠየቁ ይህን የማይገናኝ አንቀፅ ይጠቅሳሉ!

የዚህን የመረጃ አቀራረብ ግድፈትና የአንቀፁን ትክክለኛ መልእክት የሚያጎሉ በአጭሩ እነሆ፡‐

1⃣ ይህንና መሰል ጥቅል የቁርኣን አንቀፆችን ያወረደው ጌታ ሌሎች ባህሪያቱ የተረጋገጡባቸውን ዝርዝር አንቀፆችንም ያወረደው ጌታ ራሱ ስለሆነ የሚጋጩ መልዕክቶች ሊኖሯቸው አይችልም! ስለዚህ በሁሉም ማመን ግዴታ ነው። ይህ የሚቻለው ደግሞ ሁሉንም ባህሪያቱን ከምንም ጋር ሳያመሳስሉ ለርሱ ማንነት በሚገባ መልኩ በማፅደቅ ብቻ ነው።
ይህን የሚያፀናው ደግሞ፡‐

2⃣ ሰለፎች ከዚህኛውና ከመሰል ጥቅል አንቀፆች ለአላህ በማስረጃ የተረጋገጡትን የትኞቹንም ባህሪያት መልእክት በልዩ ዘይቤ መቀየር እንደሚያስፈልግ አልተረዱም፤ ይህንም አልተገበሩም! የሁሉንም ማስረጃዎች መልእክቶች አጣጥመው እምነታቸውን እንዳራመዱ በሚያሳዩ ዘገባዎች መዛግብት ተሞልተዋል። እነርሱ ስለ ቁርኣን መልእክትና ለአላህ ስለሚገባው መገለጫ ከኋለኞች የተሻለ እንደሚገነዘቡ ግልፅ ነው።

3⃣ ስለባህሪያቱ ሁኔታ ሳያነሱ መልዕክታቸውን ለርሱ ብቻ በሚገባ መልኩ ማፅደቅ አላህ ውድቅ ያደረገው ማመሳሰል (تشبيه) ውስጥ እንደማይካተት የታወቀ ነው፤
📌 አል-ኢማም አት-ቲርሚዚይ (279 ዓ.ሂ) እንደሚያስተላልፉት ታላቁ የሙስሊሞች ኢማም (161 – 238 ዓ.ሂ) እንዲህ ብለዋል፦
إِنَّمَا يَكُونُ التَّشْبِيهُ إِذَا قَالَ: يَدٌ كَيَدٍ أَوْ مِثْلُ يَدٍ، أَوْ سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ. فَإِذَا قَالَ: سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ فَهَذَا التَّشْبِيهُ، وَأَمَّا إِذَا قَالَ- كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى-: يَدٌ، وَسَمْعٌ، وَبَصَرٌ، وَلاَ يَقُولُ: كَيْفَ، وَلاَ يَقُولُ: مِثْلُ سَمْعٍ وَلاَ كَسَمْعٍ، فَهَذَا لاَ يَكُونُ تَشْبِيهًا. وَهُوَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى فِي كِتَابهِ: {لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡبَصِيرُ}
«ማመሳሰል የሚሆነው “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት እጅ”፣ “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት መስማት” ሲባል ነው፤…ነገር ግን አላህ እንደተናገረው “እጅ፣ መስማት፣ ማየት” ብሎ “እንዴት” ካላለ፣ “እንዲህ አይነት፣ እንዲያ ያለ መስማት..” ካላለ ማመሳሰል አይሆንም! አላህ ራሱ በመፅሃፉ እንዳለው ‘እንደርሱ ያልለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው’ »
[“ሱነኑ’ት-ቲርሚዚይ”፤ ኪታቡ’ዝ-ዘካህ፤ ከሐዲሥ ቁጥር (662) ቀጥሎ]

4⃣ የስያሜ መገጣጠም የሁኔታና የይዘትን መመሳሰል አያመላክትም! አላህ አዋቂ ከመሆኑ ጋር ከፊል ፍጡራንን አዋቂ ሲል ጠርቷል፤ ሰሚና ተመልካች ከመሆኑም ጋር ሌሎችን በእነዚህ ስያሜዎች ጠርቷል… ሌሎች ለራሱ ያፀደቃቸውን ባህሪያትም ለፍጡራኑ አፅድቋል፤ ምሳሌዎቹ እጅግ ብዙ ናቸው።
እነኚህ የተዕጢል ወገኖቻችን በግርድፉም ቢሆን የሚያፀድቋቸው ጥቂት ባህሪያት ፍጡራንም ሊጠሩባቸው የሚችሉ ናቸው።

ታዲያ አላህ አምሳያ የለውምና እነኚህንም መገለጫዎቹን እናስተባብል? ወይስ የፍጡርን ባህሪ ለማንነቱ በሚገባ ሁኔታ እንደምናፀድቀው የፈጣሪን ባህሪይ ለማንነቱ በሚገባ ልዩ መልኩ አረጋግጠን እንለፍ?
በተጨማሪም፦

5⃣ በአንቀፁ مِثۡل «አምሳያ» ውድቅ መደረጉ የባህሪያቱን ጥቅል ቋንቋዊ መልእክት መጋራትን አይከለክልም። አላህ አምሳያ (مِثۡل) እንደሌለው እንደጠቀሰው ሁሉ ከፍጡራን መካከልም አምሳያ (مِثۡل) እንደሌላቸው በቁርኣን የተወሱ ነገሮች አሉ፤ ሆኖም በስያሜና በጥቅል መልእክት የሚጋሯቸው ፍጡራን መኖራቸው አይካድም። ለምሳሌ፦

إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ ۝ ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ ۝

⇛«ባለ ረጃጅም ምሰሶዎች የሆነችዋ ‘ኢረም’፤ #አምሳያዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ የሆነችዋ» [አል-ፈጅር 8-9]

ሌሎች ባለ ምሰሶ አገሮች መኖራቸው ግልፅ ነው። አገራቱ በዝርዝር ይዘት መለያየታቸው የየትኛውንም አገር አገርነት አይሽርም፤ የአገራቱንም መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት ሊሆን አይችልም!

ሌላ ምሳሌ፡‐
وَإِن تَتَوَلَّوۡاْ يَسۡتَبۡدِلۡ قَوۡمًا غَيۡرَكُمۡ ثُمَّ لَا يَكُونُوٓاْ أَمۡثَٰلَكُم [محمد: 38]
⇛ «(በእንቢታ) ብትዞሩ ከናንተ ሌላ ህዝቦችን ይተካል፤ ከዚያም #አምሳያዎቻችሁ አይሆኑም።» [ሙሐመድ 38]

ተኪዎቹም፣ ተተኪዎቹም እጅግ ብዙ ባህሪያትን በጥቅሉ የሚጋሩ ፍጡራን (ሰዎች) ከመሆናቸው ጋር ከፊሎቹ የሌሎቹ አምሳያዎች እንዳልሆኑ በግልፅ ተወስቷል። ሆኖም ይህ ሁሉም ሰዎች የመሆናቸውን እውነታና የሚጋሯቸውን ጥቅል መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት አይሆንም።
ስለዚህ ውድቅ የተደረገው “አምሳያ” (مِثۡل) ወይም “መመሳሰል” ለሁሉም ማንነቱን የሚመጥን ባህሪን እንድናፀድቅ ያደርገናል እንጂ የአንደኛውን ባህሪይ መሰረታዊ መልእክት እንድናዛባ አያስገድደንም።

6⃣ የላይኛው አንቀፅ ሁለት ዋና ዋና መልእክቶችን አዝሏል፦
«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» የሚለው የአንቀፁ የመጀመሪያ ክፍል ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በምንም መልኩ ማመሳሰል ውድቅ መሆኑን የሚያስገነዝብ ሲሆን፤
«እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው» የሚለው መቋጫ ደግሞ መስማትና ማየትን ጨምሮ ለአላህ በመረጃ የተረጋገጡትን ስሞችና ባህሪያት ተቀብሎ ማፅደቅ የግድ መሆኑን ይጠቁማል።

📌 አቡ መንሱር አል‐አስበሃኒይ (በ418 ዓ.ሂ ያለፉ) የአንቀፁን ትክክለኛውን መልእክት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡‐
فـ{لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ} يَنْفِي كلَّ تَشْبِيه وتمثيل، {وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ} يَنْفِي كلَّ تَعْطِيل وَتَأْويل، فَهَذَا مَذْهَب أهل السّنة وَالْجَمَاعَة والأثر
«{እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤} = ሁሉንም የማመሳሰል ደረጃ (ተሽቢህ እና ተምሢል) ውድቅ ያደርጋል። {እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው} = ሁሉንም የባህሪውን መልእክት ያለመቀበልና የመቀየር ስልትን (ተዕጢልና ተእዊል) ውድቅ ያደርጋል! ይህ የሱንና እና የጀማዓህ እንዲሁም የአሠር (የትክክለኛ ትውፊት) ተከታዮች መንገድ ነው።»
[“አል‐ሑጅ‐ጃህ ፊ በያኒ'ል‐መሐጅ‐ጃህ” (1/260)]

ስለሆነም የአንቀፁ መረጃነቱ ለኛ እንጂ ለነርሱ አይደለም! የዚህን አንቀፅ መልእክት ራሱ በትክክል ተግባራዊ አድርገው ቢሆን ወደ እውነተኛው ጎዳና በተመሩ ነበር! ይህን የሚያብራራው ደግሞ የሚቀጥለው ነጥብ ነው፦

7⃣ አንድ ነገር የሚወደሰው በመገለጫዎቹ ምጥቀት እንጂ በባህሪ-አልባነቱ እንዳልሆነ ግልፅ ነው! «እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» ማለቱ ውዳሴ በመሆኑ የመለያ ባህሪያቱን ብዛት እንጂ ተቃራኒውን ሊያመላክት አይችልም! ምክንያቱም ቃሉ የሚያሳየው ባህሪያት እንደሌሉት ቢሆን ኖሮ ባዶነትን የሚጠቁም ይሆን ነበር፤ ባዶነት ደግሞ እንደስያሜው ባዶነትን እንጂ ምሉዕነትን የሚያስጨብጥ አይደለም።

8⃣ እንደነሱ አባባል አላህ እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ በተለያዩ ስልቶች ራሱን የገለፀባቸውን ጉልህ መልዕክቶች መቀበል እንደሌለብን የሚያመላክተን እንዲህ በደፈናው አምሳያ እንደሌለው በመንገር ብቻ ከሆነ ንግግሩ በብዙኃኑ ሙስሊሞች የማይፈታ የቅኔ ቋጠሮ ነው ማለት ነው!! ቃሉ ከእንዲህ ያለ መድበስበስ ፍፁም ለጠራውና ለላቀው ጌታችን ምስጋናና ውዳሴ የተገባ ነው!

እናስተውል! የላይኛውን ጥቅል አንቀፅ እንደ መረጃ አጣቅሶ አላህ ራሱን በተደጋጋሚ የገለፀበትን እዝነት፣ ቁጣ፣ መውደድ፣ መጥላት፣ መናገር፣ በዐርሹ ላይ መሆን፣ ፊት፣ እጅ.. እና ሌሎች በጣም ብዙ መገለጫዎችን በአንድ ስንዝር መደምሰስ እኮ አላህ በምድር ላይ ያለውን ነገር ሁሉ ለኛ እንደፈጠረልን የተናገረበትን ጥቅል አንቀፅ (አል‐በቀራህ 29) ተመርኩዞ እንደ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥ፣ የአሳማ ስጋን መብላት.. ያሉ ግልፅ ሸሪዓዊ ክልከላዎችን ከማስተባበል የከፋ ነው። ምክንያቱም አላህ ስለራሱ የገለፀባቸው አንቀፆች ስለ ሐላልና ሐራም ህግጋት ከገለፀባቸው ይበልጥ የጐሉና የበዙ ናቸውና!
……………………

በጥቅሉ በተለያዩ ቁርጠኛ ማስረጃዎች የተረጋገጡትን የአላህን መገለጫዎች ቀጥተኛ መልእክት ለመቆልመም አላህ አምሳያ እንደሌለው የሚያስገነዝቡ ጥቅል ማስረጃዎችን ማቅረብ ግልፁን ትቶ አሻሚን የማፈላለግ ውጤት ነው! ይህ ደግሞ ልባቸው በጥመት በሽታ የተወረሰ ሰዎች ምልክት ነው። በተቃራኒው የእውቀትና የፅኑ እምነት ባለቤቶች ምልክት ከጌታቸው ዘንድ ለሚመጣ ማንኛውም ማስረጃ እጅ መስጠታቸው ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፦
هُوَ ٱلَّذِيٓ أَنزَلَ عَلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ مِنۡهُ ءَايَٰتٞ مُّحۡكَمَٰتٌ هُنَّ أُمُّ ٱلۡكِتَٰبِ وَأُخَرُ مُتَشَٰبِهَٰتٞۖ فَأَمَّا ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمۡ زَيۡغٞ فَيَتَّبِعُونَ مَا تَشَٰبَهَ مِنۡهُ ٱبۡتِغَآءَ ٱلۡفِتۡنَةِ وَٱبۡتِغَآءَ تَأۡوِيلِهِۦۖ وَمَا يَعۡلَمُ تَأۡوِيلَهُۥٓ إِلَّا ٱللَّهُۗ وَٱلرَّٰسِخُونَ فِي ٱلۡعِلۡمِ يَقُولُونَ ءَامَنَّا بِهِۦ كُلّٞ مِّنۡ عِندِ رَبِّنَاۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّآ أُوْلُواْ ٱلۡأَلۡبَٰبِ [آل عمران: 7]
⇛ «እርሱ ባንተ ላይ መፅሐፉን ያወረደው ነው፤ ከርሱ ፍፁም የሆኑ (ግልፅ) አንቀፆች አሉ፤ እነሱም የመፅሐፉ ‘እናት’ (መሠረትና ዋነኛ መገለጫ) ናቸው፤ ሌሎች (ደግሞ) ”ሙተሻቢህ” (በአንፃሩ አሻሚ ገፅታ ያላቸው) ናቸው፤ እነዚያ በልባቸው ጥመት ያልለ ፈተናን በመፈለግና “ተእዊሉን”( ) በመፈለግ የተመሳሰለውን (አሻሚውን) ይከታተላሉ፤ "ተእዊሉን" ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም፤ በእውቀት ውስጥ የሰረፁትም “ ፤ ” ይላሉ..» [ኣሊ ዒምራን 7]

ተወዳጁ መልእክተኛ (ﷺ) ይህንን አንቀፅ አንብበው እንዲህ ብለዋል፦
إِذَا رَأَيْتُمُ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ، فَأُوْلَائِكَ الَّذِينَ سَمَّى اللهُ؛ فَاحْذَرُوهُمْ
⇛«አነዚያ ከርሱ (ከቁርኣን) የተመሳሰለውን (አሻሚ ሆኖ ያገኙትን) የሚከታተሉትን ካያችሁ አላህ (በአንቀፁ) የጠቀሰው እነሱኑ ነውና ተጠንቀቋቸው!»
[አል-ቡኻሪይ (4547)፣ ሙስሊም (2665) ላይ ከእናታችን ዓኢሻህ እንደተላለፈው።]

አላህ ቀናውን መንገድ ይምራን!

06/11/2025
30/10/2025

🔖 ሒጃብን ከመልበስ ምን ከለከለሽ ?

ዛሬ አብዛኛው ሙስሊም እህቶቻችን በሒጃብ ጉዳይ ፍጹም መዘናጋታቸው ጎልቶ ይታያል ለዚህም በተደጋጋሚ እንደምክንያት የሚያቀርቧቸው 10 ነጥቦችን ሸሪዓው የሚሰጣቸውን ምላሾችን በማስመልከት የቀረበ ትምህርት።

🎙 በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

Share link
https://t.me/nesihastudio/2251

የነሲሓ ኢስላማዊ ስቱዲዮ ሙሐደራዎችና ቂርዓቶች የሚቀርቡበት ቻናል
👇🏼👇🏼👇🏼
https://t.me/nesihastudio

19/10/2025

አሊምም ይሁን ተራ ሰው ሲሞት መቀበር ያለበት በሙስሊሞች መቃብር ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ሶሐቦችና ሰለፎች ሁሉ የነበሩበት ተጨባጭ ነው።

عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله ﷺ قال
«لا تجعلوا بيوتكم مقابر....» رواه مسلم، 1/539

ሙስሊም ከአቡሁሑረይራ በተዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ (ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ... ) በማለት የተናገሩትን በማስመልከት አልሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር «ሐዲሱ በግልፅ የሚያመላክተው፤ በማንኛውም መልኩ በቤት ውስጥ መቅበር እንደተከለከለ ነው» ብለዋል። [ፈትሁልባሪ 1/130]

ይህ ግንዛቤ የአል ሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር ብቻ አልነበረም። የኢስላም አዒማዎች በዚሁ መልኩ ከልክለዋል።
አል ኢማም ማሊክ እንዲህ ብለዋል፤
لا يُدفن أحد في بيته ولا في بستانه إلا لضرورة
ብለዋል። [አልሙደወነቱል ኩብራ 1/155]

ለሽርክ መስፋፋት ምክንያት እንዳይሆን ወይም ሙስሊም ካልሆኑ ሰዎች ጋር ላለመመሳሰል እና መሰል ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው።
በተለይ ደግሞ በማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ክብር የሚቸረው ሰው ሲሆን ክልከላው ይጎላል። ምክንያቱም በተውሒድ ላይ የሚደቀነው አደጋ የከፋ ስለሚሆንና ብዙ መዘዞችን ስለሚያስከትል ነው። ወደ ጥፋት የሚያዳርሱ መንገዶችን መዝጋት (ሰድ`ዱ ዘራኢዕ) ታላቅ መርሆ መሆኑ አያጠያይቅም።

አል ኢማሙ አሽ`ሻጢቢይ እንዲህ ብለዋል፤

16/10/2025

📣 ታላቅ የምስራች 📢

🎁 ነፃ የትምህርት ዕድል - ከኢብኑ መስዑድ ኡስላሚክ ሴንተር ወሎ ቅርንጫፍ 🎁

ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የቲምና አቅመደካሞችን በአዳሪ የቁርአን ሒፍዝ ፕሮግራም አወዳድሮ በመቀበል በነፃ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
__
🕌 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ወሎ ቅንርጫፍ፣ ደሴ
☘️ https://t.me/merkezunadessie

14/08/2025

እውን ሙዚቃና ዘፈን በኢስላም አልተከለከለምን?

✍🏻 ሙሀመድ ሀሰን ማሜ (ጥር 2003)
┄┄┉┉✽‌»‌‌🌼»‌‌✽‌┉┉┄┄

አንደሚታወቀው ኢስላም ሰፊና ጥልቅ አስተምህሮቶች፤ ረቂቅና ጥልቅ መመሪያዎችና ድንጋጌዎች አሉት፡፡ ሁሉንም የህይወት ዘርፎች ዳሷል። ሳያስተምረን ያለፈው የህይወት ጉዳይ የለም። በተለያየ መልክና ዘዴ እያንዳንዱን የህይወት ክፍል በመዳሰስም ወደር የሌለው ሃይማኖት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንንም እውነታ የማንኛውም አማኝ ልቦናና ህሊና ያውቀዋል፡፡

ሆኖም በኢስላም ድንጋጌ እና መመሪያ ላይ በየጊዜው እና በየወቅቱ የተለያዩ ብዥታዎችና ውዥንብሮችን የሚፈጥሩ ሰዎች አልጠፉም፣ ነበሩም፣ አሉም፣ ይኖራሉም፡፡ በየጊዜው ብቅ ጥልቅ ከሚሉ በርካታ ውዥንብሮች መካከል የሙዚቃን ብይን የተመለከተው ይጠቀሳል። የራሳቸውን ግንዛቤ ለማስተላለፍ ሲፈልጉ፤ ኢስላም ስለዘፈንም ይሁን ስለሙዚቃ ክልክልነት የተናገረው ነገር የለም፡፡ ክልክል ለመሆኑ የቀረቡ መረጃዎችንም የወደቁና ተቀባይነት የሌላቸው እንደሆኑ፤ ሲጠኑ በሁለት እግር መቆም የማይችሉ እንደሆኑ አድርገው በማቅረብ የሚነዙት ብዥታ ተራ አሉባልታ እንደሆነ በእዚህ መልዕክቴ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡ በተለይም ሰሞኑን አቶ ሀሰን ታጁ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ የጣዕም ልኬት የሙዚቃ ዝግጅት ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ይህ አይነቱን አመለካከት በስፋት ስላብራራ አጠር ያለ ምላሽ አዘጋጅቻለው። አላህ ስራችንን ሁሉ በኢኽላስ የተፈፀመ እንዲያደርገውነ እለምነዋለሁ። እግዛንም ከእርሱ ብቻ እጠይቃለሁ፡፡

ዘፈንና ሙዚቃ በኢስላም የተከለከለ መሆኑን በተለያዩ ኢስላማዊ መረጃዎች ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
1ኛ- ከቁርአን 2ኛ- ከሐዲስ
3ኛ- ከሰሃቦች 4ኛ- ከታቢዒዮች
5ኛ- ከአራቱ መዝሃቦች 6ኛ - ከኢጅማዑ አሰለፍ

1ኛ- ከቁርአን
በሱረቱል ሉቅማን ቁጥር 6
وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْتَرِي لَهْوَ الْحَدِيثِ لِيُضِلَّ عَن سَبِيلِ اللَّهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ وَيَتَّخِذَهَا هُزُوًا ۚ أُولَٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ مُّهِينٌ [٣١:٦]

“ከሰዎች ያለ እውቀት ሆኖ ከአላህ መንገድ ሊያሳስትና ማላገጫ አድርጎ ሊይዛት አታላይ ወሬን (ለህወል ሀዲስ) የሚገዛ አለ፤ እነዚያ እነሱ አዋራጅ ቅጣት አላቸው፡፡”

በእዚህ አንቀፅ ውስጥ “ለህወል ሀዲስ” (አታላይ ወሬ) ተብሎ የተሰየመውና ቅጣቱም አወራጅ ተብሎ የተዛተበት ምን ይሆን? መልሱን ከሰሃቦች ማግኘት ይቻላል፡፡

ሀ. አብድላህ አብኑ መስዑድ

(ስለቁርአን ጥልቅ እውቀት ባላቸው ስመጥር ሰሃባ አንዱ ነው፡፡) ስለ “ለህወል ሀዲስ” (አታላይ ወሬ) ሲጠየቅ ሶስት ጊዜ በመማል “ዘፈን ነው ዘፈን ነው ዘፈን ነው” በማለት መመለሱን ኢብኑ አቡ ሸይባ፣ ኢብኑ ጀሪር፣ አልሃኪም፣ አልበይሀቂ እና ኢብልጀውዚ ዘግበውታል፡፡

ለ. አብደላህ ኢብኑ ዐባስ

(የዑማው አዋቂና በቁርአን ማብራሪያ ላቅ ያለ እውቀት ያለውና ረሱልም “አላህ ሆይ ሃይማኖቱን አስገንዝበው የቁርአንንም ማብራሪያ አሳውቀው፡፡” ብለው ዱዓእ ያደረጉለት ስመ ጥር ሰሃባ ነው፡፡) ስለ (ለህወል ሀዲስ) “ዘፈንና መሰሎቹ ናቸው” ማለቱን ኢብኑ አቡ ሸይባ፣ (ቡኻሪ፣ ኢብኑ ጀሪር፣ አልበይሀቂ፣ እና ኢብኑ ጀውዚ ዘግበውታል፡፡)

ሐ. አብደላህ ኢብኑ ዑመር (የመዲና ሙፍቲና የፊቂህ ምሁር ) ለሕወል ሀዲስን በማስመልከት “እርሱም ዘፈን ነው” በማለት አብራርቶታል፡፡

መ. ጃቢር ኢብኑ አብደላህ (ከኢብኑ ዑመር ቀጥሎ የመዲና ሰዎች ፊቂህ እንዲሁም ሙፍቲ የነበረው) “ዘፈንና ማድመጡ ነው” ማለቱን ኢብኑ ጀሪር ዘግበዋል፡፡

ታዲያ ከእነዚህ ታላላቅና ስመጥር ሰሃቦች ይህን አንቀፅ በተመለከተ (ዘፈን) መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የሰሃቦች ማብራሪያ ማስረጃ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንም ማብራሪያ የተቃረነ አንድም ሰሃባ የለም፡፡

ሰሃቦችም እንዲህ ብለው እንደተረጐሙት ሁሉ ታቢዒዮችም በተመሳሳይ መልኩ አብራርተውታል፡፡ እንደሚከተለውም ዝርዝራቸውን እጠቅሳለሁ፡፡

1.ሙጃሂድ ኢብኑ ጃቢር
2. ዒክሪማህ
3. መክሁል
4.ኢብራሂም አል ነኸዒ
5. ዐጣእ
6.ሰዒድ ኢብኑ ጁበይ
7.አል ሐሰን አል በስሪ
8.ቀታዳህ ኢብኑ ደዓማ
9.መይሙን ኢብኑ ሚህራን
1ዐ. ሀቢብ ኢብኑ አቢሳቢት
11. ዐምር ኢብኑ ሹዓይብ
12. አብዱልመሊክ ኢብኑ ጁረይጅ
13. ሰኢድ ኢብኑልሙሰይብ ናቸዉ፡፡

ሱረቱ ነጅም ቁጥር 59 – 61
أَفَمِنْ هَٰذَا الْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ [٥٣:٥٩]وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ [٥٣:٦٠]وَأَنتُمْ سَامِدُونَ [٥٣:٦١]

“በዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?! ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን? እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡”

ይህንም አንቀፅ በማስመልከት ዘንጊዎች ተብሎ የተተረጐመው ቃል በአረብኛው “ሳሚዱን” የሚለው ቃል ሲሆን ትርጉሙን በተመለከተ የየመን ቋንቋ እንደሆ በመጥቀስ “ዘፈን” እንደሆነ አብደላህ ኢብኑ ዐባስ ፣ ሙጃሂድ፣ ዒክሪማና አደሃክ ተናግረዋል፡፡
ሱረቱል ኢስራእ ቁጥር 64

وَاسْتَفْزِزْ مَنِ اسْتَطَعْتَ مِنْهُم بِصَوْتِكَ وَأَجْلِبْ عَلَيْهِم بِخَيْلِكَ وَرَجِلِكَ وَشَارِكْهُمْ فِي الْأَمْوَالِ وَالْأَوْلَادِ

“ከእነሱ ያቻልከውንም ሰው በድምፅህ አታል በእነሱም ላይ በፈረሶኞችህም ለልብ በገንዘቦቻቸውም፣ በልጆቻቸውም ተጋራቸው፡፡”

ሙጃሂድ ኢብኑ ጃብር (የአብደላህ ኢብኑ ዓባስ ታላቅ ተማሪ) የኢብሊስ ድምፅ ምንነት ሲገልፁ እንዲህ ነበር ያሉት፡፡ “እርሱም ጊና (ዘፈን)፣ ሙዚቃ መሳሪያ፣ ላግጣና ከንቱ ነገር ነው፡፡”

አድሃክም የዘፋኝ (የሙዚቃ መሳሪያ) ድምፅ ነው” ብለዋል

ኢብኑል ቀይምም እንዲህ በማለት ስለዘፈን ሁኔታ ይገልፃሉ :- “ዘፈን ከታላላቅ የሰይጣን ድምፃችና ነፍስን የሚያስበረግግበት፣ የሚረብሽበት እና ሰላም የሚነሰት ለመሆኑ አያጠራጥርም የቁርአን ወደሚረጋጋበት፣ ሰላም የሚያገኝበትና ወደጌታዋ እንድትመለስ የሚያደርገውን ተቃራኒ ነው፡፡”

👉 ቀሪውን ክፍል በሚከተለው ሊንክ ያንብቡ
https://nesiha.com/%e1%8a%a5%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%88%99%e1%8b%9a%e1%89%83%e1%8a%93-%e1%8b%98%e1%8d%88%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%88%b5%e1%88%8b%e1%88%9d-%e1%8a%a0%e1%88%8d%e1%89%b0%e1%8a%a8%e1%88%88%e1%8a%a8/

┄┄┉┉✽‌»‌‌🌼»‌‌✽‌┉┉┄┄

© ተንቢሀት

12/08/2025

የአልረሕማንን ባሮች እወቋቸው

የሱረቱል ፉርቃን መደምደሚያ አንቀፆች ምርጥ ቲላዋ

(ሱረቱል ፉርቃን 63–77) በሸይኽ መንሱር አዛህራኒ

{وَعِبَادُ الرَّحْمَٰنِ الَّذِينَ يَمْشُونَ عَلَى الْأَرْضِ هَوْنًا وَإِذَا خَاطَبَهُمُ الْجَاهِلُونَ قَالُوا سَلَامًا (63)

የአልረሕማን ባሮች፤

እነዚያ በምድር ላይ በዝግታ የሚኼዱ፣ ባለጌዎች በክፉ ባነጋገሩዋቸውም ጊዜ መልካምን የሚመልሱ ናቸው።

وَالَّذِينَ يَبِيتُونَ لِرَبِّهِمْ سُجَّدًا وَقِيَامًا (64)

እነዚያም፦ ለጌታቸው በግንባራቸው ተደፊዎችና ቋሚዎች ኾነው የሚያድሩት ናቸው።

وَالَّذِينَ يَقُولُونَ رَبَّنَا اصْرِفْ عَنَّا عَذَابَ جَهَنَّمَ ۖ إِنَّ عَذَابَهَا كَانَ غَرَامًا (65)

እነዚያም፦ ጌታችን ሆይ! የገሀነምን ቅጣት ከኛ ላይ መልስልን፤ ቅጣቷ የማያልቅ ነውና፤ የሚሉት ናቸው።

إِنَّهَا سَاءَتْ مُسْتَقَرًّا وَمُقَامًا (66)

እርሷ ለመርጊያና ለመኖሪያነት የከፋች ናት! (ይላሉ)።

وَالَّذِينَ إِذَا أَنفَقُوا لَمْ يُسْرِفُوا وَلَمْ يَقْتُرُوا وَكَانَ بَيْنَ ذَٰلِكَ قَوَامًا (67)

እነዚያም፤በለገሱ ጊዜ የማያባክኑት፣ በስስት የማይቆጥቡትም ሲሆኑ፤ በዚህ መካከል (ልግስናቸው) ሚዛናዊ ነው።

وَالَّذِينَ لَا يَدْعُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ وَلَا يَقْتُلُونَ النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ وَلَا يَزْنُونَ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ يَلْقَ أَثَامًا (68)

እነዚያም፣ ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማያመልኩት፤ ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ የማይገድሉት፤ የማያመነዝሩትም ናቸው፤ ይህንንም የሚሠራ ሰው ቅጣትን ያገኛል።

يُضَاعَفْ لَهُ الْعَذَابُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَيَخْلُدْ فِيهِ مُهَانًا (69)

በትንሣኤ ቀን ቅጣቱ በርሱ ላይ ይደራረባል፤ በርሱም ውስጥ የተዋረደ ሆኖ ይኖራል።

إِلَّا مَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ عَمَلًا صَالِحًا فَأُولَٰئِكَ يُبَدِّلُ اللَّهُ سَيِّئَاتِهِمْ حَسَنَاتٍ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا (70)

ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፤

እነዚያን አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፤ አላህም እጅግ መሐሪ አዛኝ ነው።

وَمَن تَابَ وَعَمِلَ صَالِحًا فَإِنَّهُ يَتُوبُ إِلَى اللَّهِ مَتَابًا (71)

ተጸጽቶ የተመለሰ አና መልካምንም የሠራ፤ እርሱ ትክክለኛን መመለስ ወደ አላህ ይመለሳል።

وَالَّذِينَ لَا يَشْهَدُونَ الزُّورَ وَإِذَا مَرُّوا بِاللَّغْوِ مَرُّوا كِرَامًا (72)

እነዚያም፣ እብለትን የማይመሰክሩ፤ ውድቅ ቃልም (በሚገሩ ሰዎች አጠገብ) ባለፉ ጊዜ፤ ክብራቸውን በመጠበቅ የሚያልፉት ናቸው።

وَالَّذِينَ إِذَا ذُكِّرُوا بِآيَاتِ رَبِّهِمْ لَمْ يَخِرُّوا عَلَيْهَا صُمًّا وَعُمْيَانًا (73)

እነዚያም፣ በጌታቸው አንቀጾች በተገሠጹ ጊዜ፣ (ሀቅን የተረዱ ተቀባዮች ሆነው እንጂ) ደንቆሮዎችና ዕውሮች የሆኑ ያህል (በክህደት) በርሷ ላይ የማይደፉት ናቸው።

وَالَّذِينَ يَقُولُونَ رَبَّنَا هَبْ لَنَا مِنْ أَزْوَاجِنَا وَذُرِّيَّاتِنَا قُرَّةَ أَعْيُنٍ وَاجْعَلْنَا لِلْمُتَّقِينَ إِمَامًا (74)

እነዚያም ጌታችን ሆይ! ከሚስቶቻችንና ከዘሮቻችን ለዓይኖች መርጊያን ለኛ ስጠን፤ አላህን ለሚፈሩት መሪ አድርገን፤ የሚሉት ናቸው።

أُولَٰئِكَ يُجْزَوْنَ الْغُرْفَةَ بِمَا صَبَرُوا وَيُلَقَّوْنَ فِيهَا تَحِيَّةً وَسَلَامًا (75)

እነዚያ በመታገሣቸው የገነትን ሠገነቶች ይመነዳሉ፤ በርሷም ውስጥ ውዳሴንና ሰላምታን ይስሰጣሉ።

خَالِدِينَ فِيهَا ۚ حَسُنَتْ مُسْتَقَرًّا وَمُقَامًا (76)

በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ይሆናሉ፤ መርጊያና መኖሪያነቷ አማረች፡፡ (76)

قُلْ مَا يَعْبَأُ بِكُمْ رَبِّي لَوْلَا دُعَاؤُكُمْ ۖ فَقَدْ كَذَّبْتُمْ فَسَوْفَ يَكُونُ لِزَامًا (77)}

ጸሎታችሁ ባልነበረ ኖሮ፤ ጌታዬ እናንተን ከምንም አይቆጥራችሁም ነበር፤ « (ከሀዲያን ሆይ!) በእርግጥም አስተባበላችሁ፤ ወደ ፊትም (ቅጣቱ) የሚይዛችሁ ይኾናል» በላቸው።

-------------////---------------

አላህ ሆይ!

እኔ ዘንድ ኢማንን የተወደደ አድርገው፤

በልቤ ውስጥም ስፍራ ስጥው፤

እውነተኛ አማኝም አድርገኝ!!

አሚን!!

©www.facebook.com/Tenbihat

25/06/2025

⚘️ የሙሐደራ ግብዣ ለሴቶች

🗓 እሁድ ሰኔ 22/ 2017

🕒 ጠዋት ከ3:00-6:30

🕌 18 ማዞሪያ አካባቢ

ለበለጠ መረጃ 0904366666

ኢብን መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር
https://t.me/darulhadis18

24/06/2025

🧊 አዲስ የኪታብ ደርስ 🧊

💠 شرح الأدب عنوان السعادة للشيخ صالح سندي

📘አል አደቡ ዑንዋኑስ-ሰዓደህ

ክ/1

📝 ዝግጅት ፡- ሸይኽ ሳሊሕ ሲንዲ

🔊 ማብራሪያ:-ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም

የዕለተ ማክሰኞ 28/12/1446 ዓ.ሂ
የአደብና ስነ-ሥርዓት ትምህርት

የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ
🔸🔹🔸🔹🔸🔹

🔎 https://is.gd/adab_1

🔸🔹🔸🔹🔸🔹

📘 የኪታቡን ፒ.ዲ.ኤፍ ለማግኘት

⬇ ⬇ ⬇ ⬇

🔎 https://is.gd/adab_kitab

🔹 🔸 🔹 🔸 🔹 🔸

💥 በተጨማሪም የተለያዩ ፔጆቻችንን ለመቀላቀልና ዌብሳይታችንን ለማግኘት ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ

🌐 https://zadalmead.com/

✔️ https://telegram.me/ahmedadem

✔️https://facebook.com/yenegew

✔️https://youtube.com/-Mead

✔️ https://x.com/zadul__mead

✔️https://instagram.com/zadulmead

📚"ዒልም ማለት አላህን መፍራት ነው!"
አል-ኢማሙ ማሊክ

26/03/2025

የአንድ ሰው ዘካተል ፊጥር 230 ብር

ንግድ ባንክ
1000441566666

ሂጅራ ባንክ
1001318180001

አዋሽ ባንክ
014251151025300

ነሲሓ በጎ አድራጎት ባ/ ዳር ቅርንጫፍ

ስልክ ቁጥር: – 0904947575/0911268602

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Address

Addis Ababa