ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት

ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት ተንቢሀት - የተለያዩ ኢስላማዊ ትምህርቶች የሚቀርቡበት ፔጅ Important Lessons for muslimah
see also
www.facebook.com/fatawa.lmar2a.lmoslima

📣 የሙሀደራ ግብዣ ለሴቶች🌸 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር የ2018 የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክኒያት በማድረግ የተዘጋጀውን ልዩ ፕሮግራም እንድትታደሙ ተጋብዛችሗል::🗓 ቅዳሜ ሰኔ 20/...
24/06/2026

📣 የሙሀደራ ግብዣ ለሴቶች

🌸 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር የ2018 የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክኒያት በማድረግ የተዘጋጀውን ልዩ ፕሮግራም እንድትታደሙ ተጋብዛችሗል::

🗓 ቅዳሜ ሰኔ 20/2018
ከጠዋቱ 3:00-6:30

🕌 ረያን መስጂድ
ጦር ሃይሎች አካባቢ

⚠️ጥሪውን ለእህቶች በማድረስ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!

____
🕌 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር
📲 t.me/merkezuna

📣 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር  ከ 10 አመት በላይ ላሉ ወንድና ሴት ታዳጊዎችና ወጣቶች የ 2 ወራት የዲን ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ጀምሯል።በ 4 ደረጃ የሚሰጡ ትምህርቶች📔ተጅዊድ📗አቂ...
10/06/2026

📣 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ከ 10 አመት በላይ ላሉ ወንድና ሴት ታዳጊዎችና ወጣቶች የ 2 ወራት የዲን ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ጀምሯል።

በ 4 ደረጃ የሚሰጡ ትምህርቶች

📔ተጅዊድ
📗አቂዳ
📔ሲራ
📕ተርቢያ
📘ፊቅህ

🕰 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቀንና ሰአት
ከሰኞ እስከ ሃሙስ ከ 3:00-6:30

🏫 ትምህርቱ የሚሰጥባቸው ቦታዎች

1⃣ ኮልፌ 18 ማዞሪያ (ለወንዶች)

ለመረጃ - 0912617007

🔸ኮልፌ 18 ማዞሪያ (ለሴቶች)

ከሰኞ እስከ ጁሙአ ለጀማሪና ቁርአን ላላኸተሙ ተማሪዎች ኑራኒያ ነዘር እና መሰረታዊ የዲን ትምህርት ይሰጣል::

ለመረጃ - 0904366666

2⃣ ቤተል (ለሴቶች)

ለመረጃ
0911062499/ 0913840323

3⃣ ፉሪ (ለሴቶች)

ለመረጃ
0926948459 / 0965405072

📆 የምዝገባ ቀን:- ከስኔ 1-19 /2018

📅 ትምህርቱ የሚሰጠው:-
ከሀምሌ 1- ነሀሴ 29/2018

⚠️ ወላጆች ልጆችዎ የዚህ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በጊዜው በማስመዝገብ ሃላፊነትዎን ይወጡ!

⚠️ መልእክቱን ሼር በማድረግ ከምንዳው ይካፈሉ!

____
🕌 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር
📲 t.me/merkezuna

የቲሞችን ማገዝ ታላቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው።  በመጭው የኢድ አል አድሃ / የአረፋ በዓል በባህር ዳርና አካባቢዋ ለሚገኙ የቲሞችና መሳኪኖች በደስታ እንዲውሉ አዳዲስ ልብሶችን ለማልበስ የ...
09/05/2026

የቲሞችን ማገዝ ታላቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው።

በመጭው የኢድ አል አድሃ / የአረፋ በዓል በባህር ዳርና አካባቢዋ ለሚገኙ የቲሞችና መሳኪኖች በደስታ እንዲውሉ አዳዲስ ልብሶችን ለማልበስ የበኩልዎን ድጋፍ ያድርጉ !!

1 የቲም/ ሚስኪን ለማልበስ 2,000 ብር

እርሶ በዒድ ቀን ስንት የቲም/ሚስኪን ለማስደስት አስበዋል?

ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ባህርዳር ቅርንጫፍ

ንግድ ባንክ
1000441566666
ሂጅራ ባንክ
1001318180001
አዋሽ ባንክ
014251151025300

ለበለጠ መረጃ :–
📱 0904947575
📱 0918412322

ዑምራ የሚያሸልመው ውድድር ነገ ይካሄዳልበተከበረዉ የረመዳን ወር ታላቅ የቁርአን ዉድድር ጦርሀይሎች ረያን መስጂድበሁለቱም ፆታዎች በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚገኙ መስጂዶች ሲደረግ የነበረዉ የቁር...
01/03/2026

ዑምራ የሚያሸልመው ውድድር ነገ ይካሄዳል

በተከበረዉ የረመዳን ወር ታላቅ የቁርአን ዉድድር ጦርሀይሎች ረያን መስጂድ

በሁለቱም ፆታዎች በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚገኙ መስጂዶች ሲደረግ የነበረዉ የቁርአን ሂፍዝ ዉድድር በነገዉ እለት ፍፃሜዉን ሲያደርግ በሁለቱም ፆታ በአንደኝነት ለሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች የኡምራ ፓኬጅ ሽልማት ሲበረከትላቸዉ ሁለተኛ ለሚወጡ 50ሺ ሶስተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች ደሞ የ30ሺ ብር ሽልማት ይበረከትላቸዋል

የወንዶቹን ዉድድር በወንድ ዳኞች በረያን መስጂድ ሲያከናዉን የሴቶቹ የፍፃሜ ዉድድር ደሞ በሴት ዳኞች አዲስ አበባ መጅሊስ ጊቢ 5ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘዉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይደረጋል

ሁላቹም ቦታዉ ድረስ መታቹ እንድትታደሙ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን

ሰአት ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ

07/02/2026
حلمكِ بأن تكوني "طالبة في الحرم" أصبح بين يديكِ.. وأنتِ في منزلك! ✨ الحلم الذي لم تعرفه الكثيرات! 🕋يا أخواتي الكريمات، ك...
08/01/2026

حلمكِ بأن تكوني "طالبة في الحرم" أصبح بين يديكِ.. وأنتِ في منزلك! ✨ الحلم الذي لم تعرفه الكثيرات! 🕋
يا أخواتي الكريمات، كثير من البنات يظنّون أن نيل شرف طلب العلم في رحاب الحرم المكي أو النبوي يتطلب السفر أو الإقامة هناك.. لكن المعلومة التي قد تغير حياتكِ ومساركِ العلمي هي أن الحرم الآن يأتي إليكِ أينما كنتِ! 🌍

ما هو موقع "وقار الحرم"؟ 🎓
هو جسرُكِ الإيماني لتصبحي طالبة رسمية، تحضرين الحلقات والدروس العلمية "أونلاين" مباشرة، دون اشتراط الحضور الجسدي في معهد الحرم.

لماذا هذه الفرصة لا تُعوض؟

بالمجان تماماً: العلمُ متاح لكل طالبة حق، بلا أي رسوم.

مرونة تامة: يمكنكِ اختيار المواعيد التي تناسب جدولكِ وحياتكِ اليومية.

شهادة وعلم: تنهلين من دروس كبار العلماء والمحفظات في أطهر بقاع الأرض.

كيف تبدئين الرحلة؟ 📝
التقديم متاح عبر الرابط الرسمي لمنصة "وقار، والرابط في التعليق الأول

💡 ملاحظة هامة جداً: التقديم يفتح رسمياً مع بداية العام الدراسي، لذا كوني مستعدة!

نصيحة من القلب: لا تتركي هذه المعلومة تقف عندكِ، فالدال على الخير كفاعله. احفظي المنشور (Save) وشاركيه مع كل صديقة أو أخت تحلم بالعلم الشرعي لعلّكِ تكونين سبباً في وصلها برحاب الحرم. 🕊️🌿




رابط التسجيل هنا :
https://reg.qm.edu.sa/Minton/Account/NewRegistration

ሸሪዓዊ ልባስ!🖌 ኢልያስ አሕመድ {لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ}–––––––––––– (ዝርዝር ማስረጃዎችን ለመናድ ጥቅል አንቀፆችን በማቅረብ ፍልስፍናዊ መነሻዎችን ሸሪዓዊ ልባስ...
19/11/2025

ሸሪዓዊ ልባስ!
🖌 ኢልያስ አሕመድ
{لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ}
––––––––––––
(ዝርዝር ማስረጃዎችን ለመናድ ጥቅል አንቀፆችን በማቅረብ ፍልስፍናዊ መነሻዎችን ሸሪዓዊ ልባስ የማልበስ ስልት)

🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹

በሰለፎች ምልአተ ድምፅ የተኮነነው የጀህሚያው የተዕጢል መስመር ጠንሳሾችንና አቀንቃኞችን በቁርኣንና በሐዲሥ በተደጋጋሚ የፀደቁትን የፈጣሪ ዝርዝር መገለጫዎችን መልእክት ለመቆልመም ያበቃቸው እውነተኛ መነሻ ፍልስፍናዊ እንጂ ሸሪዓዊ አይደለም። (ዝርዝሩን በሌላ ጊዜ እንመለስበት ይሆናል።)
ሆኖም አብዛኛዎቹ ብዙሃኑን ለመሸንገል በየአጋጣሚው የሚያነሷቸው አንዳንድ ጥቅል ጥቅሶች እንዳሉ ይታወቃል! አንድ የቁርኣን አንቀፅን በምሳሌነት እንውሰድ፦
{ لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ }
[سُورَةُ الشُّورَىٰ: ١١]
⇛«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው።» [አሽ-ሹራ 11]

ለምሳሌ፡‐ አላህ በዐርሹ በላይ ከፍ ያለ መሆኑን የሚያረጋግጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ማስረጃዎች ይዘት ላለመቀበላቸው፣ በአንፃሩም «አላህ ያለ ቦታ ነው ያለው!» ለተሰኘው መጤ መፈክራቸው ማስረጃ ሲጠየቁ ይህን የማይገናኝ አንቀፅ ይጠቅሳሉ!

የዚህን የመረጃ አቀራረብ ግድፈትና የአንቀፁን ትክክለኛ መልእክት የሚያጎሉ በአጭሩ እነሆ፡‐

1⃣ ይህንና መሰል ጥቅል የቁርኣን አንቀፆችን ያወረደው ጌታ ሌሎች ባህሪያቱ የተረጋገጡባቸውን ዝርዝር አንቀፆችንም ያወረደው ጌታ ራሱ ስለሆነ የሚጋጩ መልዕክቶች ሊኖሯቸው አይችልም! ስለዚህ በሁሉም ማመን ግዴታ ነው። ይህ የሚቻለው ደግሞ ሁሉንም ባህሪያቱን ከምንም ጋር ሳያመሳስሉ ለርሱ ማንነት በሚገባ መልኩ በማፅደቅ ብቻ ነው።
ይህን የሚያፀናው ደግሞ፡‐

2⃣ ሰለፎች ከዚህኛውና ከመሰል ጥቅል አንቀፆች ለአላህ በማስረጃ የተረጋገጡትን የትኞቹንም ባህሪያት መልእክት በልዩ ዘይቤ መቀየር እንደሚያስፈልግ አልተረዱም፤ ይህንም አልተገበሩም! የሁሉንም ማስረጃዎች መልእክቶች አጣጥመው እምነታቸውን እንዳራመዱ በሚያሳዩ ዘገባዎች መዛግብት ተሞልተዋል። እነርሱ ስለ ቁርኣን መልእክትና ለአላህ ስለሚገባው መገለጫ ከኋለኞች የተሻለ እንደሚገነዘቡ ግልፅ ነው።

3⃣ ስለባህሪያቱ ሁኔታ ሳያነሱ መልዕክታቸውን ለርሱ ብቻ በሚገባ መልኩ ማፅደቅ አላህ ውድቅ ያደረገው ማመሳሰል (تشبيه) ውስጥ እንደማይካተት የታወቀ ነው፤
📌 አል-ኢማም አት-ቲርሚዚይ (279 ዓ.ሂ) እንደሚያስተላልፉት ታላቁ የሙስሊሞች ኢማም (161 – 238 ዓ.ሂ) እንዲህ ብለዋል፦
إِنَّمَا يَكُونُ التَّشْبِيهُ إِذَا قَالَ: يَدٌ كَيَدٍ أَوْ مِثْلُ يَدٍ، أَوْ سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ. فَإِذَا قَالَ: سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ فَهَذَا التَّشْبِيهُ، وَأَمَّا إِذَا قَالَ- كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى-: يَدٌ، وَسَمْعٌ، وَبَصَرٌ، وَلاَ يَقُولُ: كَيْفَ، وَلاَ يَقُولُ: مِثْلُ سَمْعٍ وَلاَ كَسَمْعٍ، فَهَذَا لاَ يَكُونُ تَشْبِيهًا. وَهُوَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى فِي كِتَابهِ: {لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡبَصِيرُ}
«ማመሳሰል የሚሆነው “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት እጅ”፣ “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት መስማት” ሲባል ነው፤…ነገር ግን አላህ እንደተናገረው “እጅ፣ መስማት፣ ማየት” ብሎ “እንዴት” ካላለ፣ “እንዲህ አይነት፣ እንዲያ ያለ መስማት..” ካላለ ማመሳሰል አይሆንም! አላህ ራሱ በመፅሃፉ እንዳለው ‘እንደርሱ ያልለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው’ »
[“ሱነኑ’ት-ቲርሚዚይ”፤ ኪታቡ’ዝ-ዘካህ፤ ከሐዲሥ ቁጥር (662) ቀጥሎ]

4⃣ የስያሜ መገጣጠም የሁኔታና የይዘትን መመሳሰል አያመላክትም! አላህ አዋቂ ከመሆኑ ጋር ከፊል ፍጡራንን አዋቂ ሲል ጠርቷል፤ ሰሚና ተመልካች ከመሆኑም ጋር ሌሎችን በእነዚህ ስያሜዎች ጠርቷል… ሌሎች ለራሱ ያፀደቃቸውን ባህሪያትም ለፍጡራኑ አፅድቋል፤ ምሳሌዎቹ እጅግ ብዙ ናቸው።
እነኚህ የተዕጢል ወገኖቻችን በግርድፉም ቢሆን የሚያፀድቋቸው ጥቂት ባህሪያት ፍጡራንም ሊጠሩባቸው የሚችሉ ናቸው።

ታዲያ አላህ አምሳያ የለውምና እነኚህንም መገለጫዎቹን እናስተባብል? ወይስ የፍጡርን ባህሪ ለማንነቱ በሚገባ ሁኔታ እንደምናፀድቀው የፈጣሪን ባህሪይ ለማንነቱ በሚገባ ልዩ መልኩ አረጋግጠን እንለፍ?
በተጨማሪም፦

5⃣ በአንቀፁ مِثۡل «አምሳያ» ውድቅ መደረጉ የባህሪያቱን ጥቅል ቋንቋዊ መልእክት መጋራትን አይከለክልም። አላህ አምሳያ (مِثۡل) እንደሌለው እንደጠቀሰው ሁሉ ከፍጡራን መካከልም አምሳያ (مِثۡل) እንደሌላቸው በቁርኣን የተወሱ ነገሮች አሉ፤ ሆኖም በስያሜና በጥቅል መልእክት የሚጋሯቸው ፍጡራን መኖራቸው አይካድም። ለምሳሌ፦

إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ ۝ ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ ۝

⇛«ባለ ረጃጅም ምሰሶዎች የሆነችዋ ‘ኢረም’፤ #አምሳያዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ የሆነችዋ» [አል-ፈጅር 8-9]

ሌሎች ባለ ምሰሶ አገሮች መኖራቸው ግልፅ ነው። አገራቱ በዝርዝር ይዘት መለያየታቸው የየትኛውንም አገር አገርነት አይሽርም፤ የአገራቱንም መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት ሊሆን አይችልም!

ሌላ ምሳሌ፡‐
وَإِن تَتَوَلَّوۡاْ يَسۡتَبۡدِلۡ قَوۡمًا غَيۡرَكُمۡ ثُمَّ لَا يَكُونُوٓاْ أَمۡثَٰلَكُم [محمد: 38]
⇛ «(በእንቢታ) ብትዞሩ ከናንተ ሌላ ህዝቦችን ይተካል፤ ከዚያም #አምሳያዎቻችሁ አይሆኑም።» [ሙሐመድ 38]

ተኪዎቹም፣ ተተኪዎቹም እጅግ ብዙ ባህሪያትን በጥቅሉ የሚጋሩ ፍጡራን (ሰዎች) ከመሆናቸው ጋር ከፊሎቹ የሌሎቹ አምሳያዎች እንዳልሆኑ በግልፅ ተወስቷል። ሆኖም ይህ ሁሉም ሰዎች የመሆናቸውን እውነታና የሚጋሯቸውን ጥቅል መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት አይሆንም።
ስለዚህ ውድቅ የተደረገው “አምሳያ” (مِثۡل) ወይም “መመሳሰል” ለሁሉም ማንነቱን የሚመጥን ባህሪን እንድናፀድቅ ያደርገናል እንጂ የአንደኛውን ባህሪይ መሰረታዊ መልእክት እንድናዛባ አያስገድደንም።

6⃣ የላይኛው አንቀፅ ሁለት ዋና ዋና መልእክቶችን አዝሏል፦
«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» የሚለው የአንቀፁ የመጀመሪያ ክፍል ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በምንም መልኩ ማመሳሰል ውድቅ መሆኑን የሚያስገነዝብ ሲሆን፤
«እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው» የሚለው መቋጫ ደግሞ መስማትና ማየትን ጨምሮ ለአላህ በመረጃ የተረጋገጡትን ስሞችና ባህሪያት ተቀብሎ ማፅደቅ የግድ መሆኑን ይጠቁማል።

📌 አቡ መንሱር አል‐አስበሃኒይ (በ418 ዓ.ሂ ያለፉ) የአንቀፁን ትክክለኛውን መልእክት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡‐
فـ{لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ} يَنْفِي كلَّ تَشْبِيه وتمثيل، {وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ} يَنْفِي كلَّ تَعْطِيل وَتَأْويل، فَهَذَا مَذْهَب أهل السّنة وَالْجَمَاعَة والأثر
«{እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤} = ሁሉንም የማመሳሰል ደረጃ (ተሽቢህ እና ተምሢል) ውድቅ ያደርጋል። {እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው} = ሁሉንም የባህሪውን መልእክት ያለመቀበልና የመቀየር ስልትን (ተዕጢልና ተእዊል) ውድቅ ያደርጋል! ይህ የሱንና እና የጀማዓህ እንዲሁም የአሠር (የትክክለኛ ትውፊት) ተከታዮች መንገድ ነው።»
[“አል‐ሑጅ‐ጃህ ፊ በያኒል‐መሐጅጀህ” (1/260)]

ስለሆነም የአንቀፁ መረጃነቱ ለኛ እንጂ ለነርሱ አይደለም! የዚህን አንቀፅ መልእክት ራሱ በትክክል ተግባራዊ አድርገው ቢሆን ወደ እውነተኛው ጎዳና በተመሩ ነበር! ይህን የሚያብራራው ደግሞ የሚቀጥለው ነጥብ ነው፦

7⃣ አንድ ነገር የሚወደሰው በመገለጫዎቹ ምጥቀት እንጂ በባህሪ-አልባነቱ እንዳልሆነ ግልፅ ነው! «እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» ማለቱ ውዳሴ በመሆኑ የመለያ ባህሪያቱን ብዛት እንጂ ተቃራኒውን ሊያመላክት አይችልም! ምክንያቱም ቃሉ የሚያሳየው ባህሪያት እንደሌሉት ቢሆን ኖሮ ባዶነትን የሚጠቁም ይሆን ነበር፤ ባዶነት ደግሞ እንደስያሜው ባዶነትን እንጂ ምሉዕነትን የሚያስጨብጥ አይደለም።

8⃣ እንደነሱ አባባል አላህ እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ በተለያዩ ስልቶች ራሱን የገለፀባቸውን ጉልህ መልዕክቶች መቀበል እንደሌለብን የሚያመላክተን እንዲህ በደፈናው አምሳያ እንደሌለው በመንገር ብቻ ከሆነ ንግግሩ በብዙኃኑ ሙስሊሞች የማይፈታ የቅኔ ቋጠሮ ነው ማለት ነው!! ቃሉ ከእንዲህ ያለ መድበስበስ ፍፁም ለጠራውና ለላቀው ጌታችን ምስጋናና ውዳሴ የተገባ ነው!
ለመሆኑ! የላይኛውን ጥቅል አንቀፅ እንደ መረጃ አጣቅሶ አላህ ራሱን በተደጋጋሚ የገለፀበትን እዝነት፣ ቁጣ፣ መውደድ፣ መጥላት፣ መናገር፣ በዐርሹ ላይ መሆን፣ ፊት፣ እጅ.. እና ሌሎች በጣም ብዙ መገለጫዎችን በአንድ ስንዝር መደምሰስ እኮ አላህ በምድር ላይ ያለውን ነገር ሁሉ ለኛ እንደፈጠረልን የተናገረበትን ጥቅል አንቀፅ (አል‐በቀራህ 29) ተመርኩዞ እንደ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥ፣ የአሳማ ስጋን መብላት.. ያሉ ግልፅ ሸሪዓዊ ክልከላዎችን ከማስተባበል የከፋ ነው። ምክንያቱም አላህ ስለራሱ የገለፀባቸው አንቀፆች ስለ ሐላልና ሐራም ህግጋት ከገለፀባቸው ይበልጥ የጐሉና የበዙ ናቸውና!
……………………

በጥቅሉ በተለያዩ ቁርጠኛ ማስረጃዎች የተረጋገጡትን የአላህን መገለጫዎች ቀጥተኛ መልእክት ለመቆልመም አላህ አምሳያ እንደሌለው የሚያስገነዝቡ ጥቅል ማስረጃዎችን ማቅረብ ግልፁን ትቶ አሻሚን የማፈላለግ ውጤት ነው! ይህ ደግሞ ልባቸው በጥመት በሽታ የተወረሰ ሰዎች ምልክት ነው። በተቃራኒው የእውቀትና የፅኑ እምነት ባለቤቶች ምልክት ከጌታቸው ዘንድ ለሚመጣ ማንኛውም ማስረጃ እጅ መስጠታቸው ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፦
هُوَ ٱلَّذِيٓ أَنزَلَ عَلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ مِنۡهُ ءَايَٰتٞ مُّحۡكَمَٰتٌ هُنَّ أُمُّ ٱلۡكِتَٰبِ وَأُخَرُ مُتَشَٰبِهَٰتٞۖ فَأَمَّا ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمۡ زَيۡغٞ فَيَتَّبِعُونَ مَا تَشَٰبَهَ مِنۡهُ ٱبۡتِغَآءَ ٱلۡفِتۡنَةِ وَٱبۡتِغَآءَ تَأۡوِيلِهِۦۖ وَمَا يَعۡلَمُ تَأۡوِيلَهُۥٓ إِلَّا ٱللَّهُۗ وَٱلرَّٰسِخُونَ فِي ٱلۡعِلۡمِ يَقُولُونَ ءَامَنَّا بِهِۦ كُلّٞ مِّنۡ عِندِ رَبِّنَاۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّآ أُوْلُواْ ٱلۡأَلۡبَٰبِ [آل عمران: 7]
⇛ «እርሱ ባንተ ላይ መፅሐፉን ያወረደው ነው፤ ከርሱ ፍፁም የሆኑ (ግልፅ) አንቀፆች አሉ፤ እነሱም የመፅሐፉ ‘እናት’ (መሠረትና ዋነኛ መገለጫ) ናቸው፤ ሌሎች (ደግሞ) ”ሙተሻቢህ” (በአንፃሩ አሻሚ ገፅታ ያላቸው) ናቸው፤ እነዚያ በልባቸው ጥመት ያልለ ፈተናን በመፈለግና “ተእዊሉን”( ) በመፈለግ የተመሳሰለውን (አሻሚውን) ይከታተላሉ፤ "ተእዊሉን" ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም፤ በእውቀት ውስጥ የሰረፁትም “ ፤ ” ይላሉ..» [ኣሊ ዒምራን 7]

ተወዳጁ መልእክተኛ (ﷺ) ይህንን አንቀፅ አንብበው እንዲህ ብለዋል፦
إِذَا رَأَيْتُمُ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ، فَأُوْلَائِكَ الَّذِينَ سَمَّى اللهُ؛ فَاحْذَرُوهُمْ
⇛«አነዚያ ከርሱ (ከቁርኣን) የተመሳሰለውን (አሻሚ ሆኖ ያገኙትን) የሚከታተሉትን ካያችሁ አላህ (በአንቀፁ) የጠቀሰው እነሱኑ ነውና ተጠንቀቋቸው!»
[አል-ቡኻሪይ (4547)፣ ሙስሊም (2665) ላይ ከእናታችን ዓኢሻህ እንደተላለፈው።]

አላህ ቀናውን መንገድ ይምራን!



©: በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1391785995651967&id=100044617380985&mibextid=Nif5oz

ሸሪዓዊ ልባስ!
{لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ}
––––––––––––
(ዝርዝር ማስረጃዎችን ለመናድ ጥቅል አንቀፆችን በማቅረብ ፍልስፍናዊ መነሻዎችን ሸሪዓዊ ልባስ የማልበስ ስልት)

🖌 ኢልያስ አሕመድ
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹

በሰለፎች ምልአተ ድምፅ የተኮነነው የጀህሚያው የተዕጢል መስመር ጠንሳሾችንና አቀንቃኞችን በቁርኣንና በሐዲሥ በተደጋጋሚ የፀደቁትን የፈጣሪ ዝርዝር መገለጫዎችን መልእክት ለመቆልመም ያበቃቸው እውነተኛ መነሻ ፍልስፍናዊ እንጂ ሸሪዓዊ አይደለም። (ዝርዝሩን በሌላ ጊዜ እንመለስበት ይሆናል።)
ሆኖም አብዛኛዎቹ ብዙሃኑን ለመሸንገል በየአጋጣሚው የሚያነሷቸው አንዳንድ ጥቅል ጥቅሶች እንዳሉ ይታወቃል! አንድ የቁርኣን አንቀፅን በምሳሌነት እንውሰድ፦
{ لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ }
[سُورَةُ الشُّورَىٰ: ١١]
⇛«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው።» [አሽ-ሹራ 11]

ለምሳሌ፡‐ አላህ በዐርሹ ላይ ከፍ ያለ መሆኑንና ሌሎች መገለጫዎቹን የሚያረጋግጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ማስረጃዎች ይዘት ላለመቀበላቸው፣ በአንፃሩም «አላህ ያለ ቦታ ነው ያለው!» ለተሰኘው መጤ መፈክራቸው ማስረጃ ሲጠየቁ ይህን የማይገናኝ አንቀፅ ይጠቅሳሉ! አላህ እጅ እንዳለው የሚያረጋግጡ ግልፅ ማስረጃዎችን ላለመቀበል የሚያቀርቡትም ማመካኛ ይህን አንቀፅ ነው። እንደመቆጣት፣ መደሰት፣ መውደድ፣ መጥላት… ያሉ ዝርዝር መገለጫዎችን መልእክት ለመቆልመም ዘወትር የሚገቡበት መሸሸጊያም ይኸው ጥቅል አንቀፅ ነው!

የዚህን የመረጃ አቀራረብ ግድፈትና የአንቀፁን ትክክለኛ መልእክት የሚያጎሉ በአጭሩ እነሆ፡‐

1⃣ ይህንና መሰል ጥቅል የቁርኣን አንቀፆችን ያወረደው ጌታ ሌሎች ባህሪያቱ የተረጋገጡባቸውን ዝርዝር አንቀፆችንም ያወረደው ጌታ ራሱ ስለሆነ የሚጋጩ መልዕክቶች ሊኖሯቸው አይችልም! ስለዚህ በሁሉም ማመን ግዴታ ነው። ይህም አላህ እንደገለፀው የአዋቂዎች መንገድ ነው፡‐
{ وَٱلرَّٰسِخُونَ فِي ٱلۡعِلۡمِ يَقُولُونَ ءَامَنَّا بِهِۦ كُلّٞ مِّنۡ عِندِ رَبِّنَاۗ }
«በእውቀት ውስጥ የሰረፁትም “ ፤ ” ይላሉ..» [ኣሊ ዒምራን 7]

ይህ ተግባራዊ የሚደረገው ደግሞ ሁሉንም ባህሪያቱን ከምንም ጋር ሳያመሳስሉ ለርሱ ማንነት በሚገባ መልኩ በማፅደቅ ብቻ ነው።
ይህን የሚያፀናው ደግሞ፡‐

2⃣ ሰለፎች ከዚህኛውና ከመሰል ጥቅል አንቀፆች ለአላህ በማስረጃ የተረጋገጡትን የትኞቹንም ባህሪያት መልእክት በልዩ ዘይቤ መቀየር እንደሚያስፈልግ አልተረዱም፤ ይህንም አልተገበሩም! የሁሉንም ማስረጃዎች መልእክቶች አጣጥመው እምነታቸውን እንዳራመዱ በሚያሳዩ ዘገባዎች መዛግብት ተሞልተዋል። እነርሱ ስለ ቁርኣን መልእክትና ለአላህ ስለሚገባው መገለጫ ከኋለኞች የተሻለ እንደሚገነዘቡ ግልፅ ነው።

3⃣ ስለባህሪያቱ ሁኔታ ሳያነሱ መልዕክታቸውን ለርሱ ብቻ በሚገባ መልኩ ማፅደቅ አላህ ውድቅ ያደረገው ማመሳሰል (تشبيه) ውስጥ እንደማይካተት የታወቀ ነው፤
📌 አል-ኢማም አት-ቲርሚዚይ (279 ዓ.ሂ) እንደሚያስተላልፉት ታላቁ የሙስሊሞች ኢማም (161 – 238 ዓ.ሂ) እንዲህ ብለዋል፦
إِنَّمَا يَكُونُ التَّشْبِيهُ إِذَا قَالَ: يَدٌ كَيَدٍ أَوْ مِثْلُ يَدٍ، أَوْ سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ. فَإِذَا قَالَ: سَمْعٌ كَسَمْعٍ أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ فَهَذَا التَّشْبِيهُ، وَأَمَّا إِذَا قَالَ- كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى-: يَدٌ، وَسَمْعٌ، وَبَصَرٌ، وَلاَ يَقُولُ: كَيْفَ، وَلاَ يَقُولُ: مِثْلُ سَمْعٍ وَلاَ كَسَمْعٍ، فَهَذَا لاَ يَكُونُ تَشْبِيهًا. وَهُوَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى فِي كِتَابهِ: {لَيۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَيۡءٞۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡبَصِيرُ}
«ማመሳሰል የሚሆነው “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት እጅ”፣ “እንዲህ ያልለ ወይም እንዲህ አይነት መስማት” ሲባል ነው፤…ነገር ግን አላህ እንደተናገረው “እጅ፣ መስማት፣ ማየት” ብሎ “እንዴት” ካላለ፣ “እንዲህ አይነት፣ እንዲያ ያለ መስማት..” ካላለ ማመሳሰል አይሆንም! አላህ ራሱ በመፅሃፉ እንዳለው ‘እንደርሱ ያልለ (አምሳያ) ምንም የለም፤ እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው’ »
[“ሱነኑ’ት-ቲርሚዚይ”፤ ኪታቡ’ዝ-ዘካህ፤ ከሐዲሥ ቁጥር (662) ቀጥሎ]

4⃣ የስያሜ መገጣጠም የሁኔታና የይዘትን መመሳሰል አያመላክትም! አላህ አዋቂ ከመሆኑ ጋር ከፊል ፍጡራንን አዋቂ ሲል ጠርቷል፤ ሰሚና ተመልካች ከመሆኑም ጋር ሌሎችን በእነዚህ ስያሜዎች ጠርቷል… ሌሎች ለራሱ ያፀደቃቸውን ባህሪያትም ለፍጡራኑ አፅድቋል፤ ምሳሌዎቹ እጅግ ብዙ ናቸው።
እነኚህ የተዕጢል ወገኖቻችን በግርድፉም ቢሆን የሚያፀድቋቸው ጥቂት ባህሪያት ፍጡራንም ሊጠሩባቸው የሚችሉ ናቸው።

ታዲያ አላህ አምሳያ የለውምና እነኚህንም መገለጫዎቹን እናስተባብል? ወይስ የፍጡርን ባህሪ ለማንነቱ በሚገባ ሁኔታ እንደምናፀድቀው የፈጣሪን ባህሪይ ለማንነቱ በሚገባ ልዩ መልኩ አረጋግጠን እንለፍ?
በተጨማሪም፦

5⃣ በአንቀፁ مِثۡل «አምሳያ» ውድቅ መደረጉ የባህሪያቱን ጥቅል ቋንቋዊ መልእክት መጋራትን አይከለክልም። አላህ አምሳያ (مِثۡل) እንደሌለው እንደጠቀሰው ሁሉ ከፍጡራን መካከልም አምሳያ (مِثۡل) እንደሌላቸው በቁርኣን የተወሱ ነገሮች አሉ፤ ሆኖም በስያሜና በጥቅል መልእክት የሚጋሯቸው ፍጡራን መኖራቸው አይካድም። ለምሳሌ፦

إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ ۝ ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ ۝

⇛«ባለ ረጃጅም ምሰሶዎች የሆነችዋ ‘ኢረም’፤ #አምሳያዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ የሆነችዋ» [አል-ፈጅር 8-9]

ሌሎች ባለ ምሰሶ አገሮች መኖራቸው ግልፅ ነው። አገራቱ በዝርዝር ይዘት መለያየታቸው የየትኛውንም አገር አገርነት አይሽርም፤ የአገራቱንም መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት ሊሆን አይችልም!

ሌላ ምሳሌ፡‐
وَإِن تَتَوَلَّوۡاْ يَسۡتَبۡدِلۡ قَوۡمًا غَيۡرَكُمۡ ثُمَّ لَا يَكُونُوٓاْ أَمۡثَٰلَكُم [محمد: 38]
⇛ «(በእንቢታ) ብትዞሩ ከናንተ ሌላ ህዝቦችን ይተካል፤ ከዚያም #አምሳያዎቻችሁ አይሆኑም።» [ሙሐመድ 38]

ተኪዎቹም፣ ተተኪዎቹም እጅግ ብዙ ባህሪያትን በጥቅሉ የሚጋሩ ፍጡራን (ሰዎች) ከመሆናቸው ጋር ከፊሎቹ የሌሎቹ አምሳያዎች እንዳልሆኑ በግልፅ ተወስቷል። ሆኖም ይህ ሁሉም ሰዎች የመሆናቸውን እውነታና የሚጋሯቸውን ጥቅል መገለጫዎች ለማስተባበል ምክንያት አይሆንም።
ስለዚህ ውድቅ የተደረገው “አምሳያ” (مِثۡل) ወይም “መመሳሰል” ለሁሉም ማንነቱን የሚመጥን ባህሪን እንድናፀድቅ ያደርገናል እንጂ የአንደኛውን ባህሪይ መሰረታዊ መልእክት እንድናዛባ አያስገድደንም።

6⃣ የላይኛው አንቀፅ ሁለት ዋና ዋና መልእክቶችን አዝሏል፦
«እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» የሚለው የአንቀፁ የመጀመሪያ ክፍል ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በምንም መልኩ ማመሳሰል ውድቅ መሆኑን የሚያስገነዝብ ሲሆን፤
«እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው» የሚለው መቋጫ ደግሞ መስማትና ማየትን ጨምሮ ለአላህ በመረጃ የተረጋገጡትን ስሞችና ባህሪያት ተቀብሎ ማፅደቅ የግድ መሆኑን ይጠቁማል።

📌 አቡ መንሱር አል‐አስበሃኒይ (በ418 ዓ.ሂ ያለፉ) የአንቀፁን ትክክለኛውን መልእክት ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፡‐
فـ{لَیۡسَ كَمِثۡلِهِۦ شَیۡءࣱۖ} يَنْفِي كلَّ تَشْبِيه وتمثيل، {وَهُوَ ٱلسَّمِیعُ ٱلۡبَصِیرُ} يَنْفِي كلَّ تَعْطِيل وَتَأْويل، فَهَذَا مَذْهَب أهل السّنة وَالْجَمَاعَة والأثر
«{እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም፤} = ሁሉንም የማመሳሰል ደረጃ (ተሽቢህ እና ተምሢል) ውድቅ ያደርጋል። {እርሱም ሰሚውና ተመልካቹ ነው} = ሁሉንም የባህሪውን መልእክት ያለመቀበልና የመቀየር ስልትን (ተዕጢልና ተእዊል) ውድቅ ያደርጋል! ይህ የሱንና እና የጀማዓህ እንዲሁም የአሠር (የትክክለኛ ትውፊት) ተከታዮች መንገድ ነው።»
[“አል‐ሑጅ‐ጃህ ፊ በያኒ'ል‐መሐጅ‐ጃህ” (1/260)]

ስለሆነም የአንቀፁ መረጃነቱ ለኛ እንጂ ለነርሱ አይደለም! የዚህን አንቀፅ መልእክት ራሱ በትክክል ተግባራዊ አድርገው ቢሆን ወደ እውነተኛው ጎዳና በተመሩ ነበር! ይህን የሚያብራራው ደግሞ የሚቀጥለው ነጥብ ነው፦

7⃣ አንድ ነገር የሚወደሰው በመገለጫዎቹ ምጥቀት እንጂ በባህሪ-አልባነቱ እንዳልሆነ ግልፅ ነው! «እንደርሱ ያለ (አምሳያ) ምንም የለም» ማለቱ ውዳሴ በመሆኑ የመለያ ባህሪያቱን ብዛት እንጂ ተቃራኒውን ሊያመላክት አይችልም! ምክንያቱም ቃሉ የሚያሳየው ባህሪያት እንደሌሉት ቢሆን ኖሮ ባዶነትን የሚጠቁም ይሆን ነበር፤ ባዶነት ደግሞ እንደስያሜው ባዶነትን እንጂ ምሉዕነትን የሚያስጨብጥ አይደለም።

8⃣ እንደነሱ አባባል አላህ እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ በተለያዩ ስልቶች ራሱን የገለፀባቸውን ጉልህ መልዕክቶች መቀበል እንደሌለብን የሚያመላክተን እንዲህ በደፈናው አምሳያ እንደሌለው በመንገር ብቻ ከሆነ ንግግሩ በብዙኃኑ ሙስሊሞች የማይፈታ የቅኔ ቋጠሮ ነው ማለት ነው!! ቃሉ ከእንዲህ ያለ መድበስበስ ፍፁም ለጠራውና ለላቀው ጌታችን ምስጋናና ውዳሴ የተገባ ነው!

እናስተውል! የላይኛውን ጥቅል አንቀፅ እንደ መረጃ አጣቅሶ አላህ ራሱን በተደጋጋሚ የገለፀበትን እዝነት፣ ቁጣ፣ መውደድ፣ መጥላት፣ መናገር፣ በዐርሹ ላይ መሆን፣ ፊት፣ እጅ.. እና ሌሎች በጣም ብዙ መገለጫዎችን በአንድ ስንዝር መደምሰስ እኮ አላህ በምድር ላይ ያለውን ነገር ሁሉ ለኛ እንደፈጠረልን የተናገረበትን ጥቅል አንቀፅ (አል‐በቀራህ 29) ተመርኩዞ እንደ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥ፣ የአሳማ ስጋን መብላት.. ያሉ ግልፅ ሸሪዓዊ ክልከላዎችን ከማስተባበል የከፋ ነው። ምክንያቱም አላህ ስለራሱ የገለፀባቸው አንቀፆች ስለ ሐላልና ሐራም ህግጋት ከገለፀባቸው ይበልጥ የጐሉና የበዙ ናቸውና!
……………………

በጥቅሉ በተለያዩ ቁርጠኛ ማስረጃዎች የተረጋገጡትን የአላህን መገለጫዎች ቀጥተኛ መልእክት ለመቆልመም አላህ አምሳያ እንደሌለው የሚያስገነዝቡ ጥቅል ማስረጃዎችን ማቅረብ ግልፁን ትቶ አሻሚን የማፈላለግ ውጤት ነው! ይህ ደግሞ ልባቸው በጥመት በሽታ የተወረሰ ሰዎች ምልክት ነው። በተቃራኒው የእውቀትና የፅኑ እምነት ባለቤቶች ምልክት ከጌታቸው ዘንድ ለሚመጣ ማንኛውም ማስረጃ እጅ መስጠታቸው ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፦
هُوَ ٱلَّذِيٓ أَنزَلَ عَلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ مِنۡهُ ءَايَٰتٞ مُّحۡكَمَٰتٌ هُنَّ أُمُّ ٱلۡكِتَٰبِ وَأُخَرُ مُتَشَٰبِهَٰتٞۖ فَأَمَّا ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمۡ زَيۡغٞ فَيَتَّبِعُونَ مَا تَشَٰبَهَ مِنۡهُ ٱبۡتِغَآءَ ٱلۡفِتۡنَةِ وَٱبۡتِغَآءَ تَأۡوِيلِهِۦۖ وَمَا يَعۡلَمُ تَأۡوِيلَهُۥٓ إِلَّا ٱللَّهُۗ وَٱلرَّٰسِخُونَ فِي ٱلۡعِلۡمِ يَقُولُونَ ءَامَنَّا بِهِۦ كُلّٞ مِّنۡ عِندِ رَبِّنَاۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّآ أُوْلُواْ ٱلۡأَلۡبَٰبِ [آل عمران: 7]
⇛ «እርሱ ባንተ ላይ መፅሐፉን ያወረደው ነው፤ ከርሱ ፍፁም የሆኑ (ግልፅ) አንቀፆች አሉ፤ እነሱም የመፅሐፉ ‘እናት’ (መሠረትና ዋነኛ መገለጫ) ናቸው፤ ሌሎች (ደግሞ) ”ሙተሻቢህ” (በአንፃሩ አሻሚ ገፅታ ያላቸው) ናቸው፤ እነዚያ በልባቸው ጥመት ያልለ ፈተናን በመፈለግና “ተእዊሉን” (ገሀዳዊ ሁኔታውን) በመፈለግ የተመሳሰለውን (አሻሚውን) ይከታተላሉ፤ "ተእዊሉን" ከአላህ በቀር ማንም አያውቅም፤ በእውቀት ውስጥ የሰረፁትም “ ፤ ” ይላሉ..» [ኣሊ ዒምራን 7]

ተወዳጁ መልእክተኛ (ﷺ) ይህንን አንቀፅ አንብበው እንዲህ ብለዋል፦
إِذَا رَأَيْتُمُ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ، فَأُوْلَائِكَ الَّذِينَ سَمَّى اللهُ؛ فَاحْذَرُوهُمْ
⇛«አነዚያ ከርሱ (ከቁርኣን) የተመሳሰለውን (አሻሚ ሆኖ ያገኙትን) የሚከታተሉትን ካያችሁ አላህ (በአንቀፁ) የጠቀሰው እነሱኑ ነውና ተጠንቀቋቸው!»
[አል-ቡኻሪይ (4547)፣ ሙስሊም (2665) ላይ ከእናታችን ዓኢሻህ እንደተላለፈው።]

አላህ ቀናውን መንገድ ይምራን!

🔖 ሒጃብን ከመልበስ ምን ከለከለሽ ?ዛሬ አብዛኛው ሙስሊም እህቶቻችን በሒጃብ ጉዳይ ፍጹም መዘናጋታቸው ጎልቶ ይታያል ለዚህም በተደጋጋሚ እንደምክንያት የሚያቀርቧቸው 10 ነጥቦችን ሸሪዓው የሚ...
30/10/2025

🔖 ሒጃብን ከመልበስ ምን ከለከለሽ ?

ዛሬ አብዛኛው ሙስሊም እህቶቻችን በሒጃብ ጉዳይ ፍጹም መዘናጋታቸው ጎልቶ ይታያል ለዚህም በተደጋጋሚ እንደምክንያት የሚያቀርቧቸው 10 ነጥቦችን ሸሪዓው የሚሰጣቸውን ምላሾችን በማስመልከት የቀረበ ትምህርት።

🎙 በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

Share link
https://t.me/nesihastudio/2251

የነሲሓ ኢስላማዊ ስቱዲዮ ሙሐደራዎችና ቂርዓቶች የሚቀርቡበት ቻናል
👇🏼👇🏼👇🏼
https://t.me/nesihastudio

አሊምም ይሁን ተራ ሰው ሲሞት መቀበር ያለበት በሙስሊሞች መቃብር ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ሶሐቦችና ሰለፎች ሁሉ የነበሩበት ተጨባጭ ነው።  عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول ...
19/10/2025

አሊምም ይሁን ተራ ሰው ሲሞት መቀበር ያለበት በሙስሊሞች መቃብር ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ሶሐቦችና ሰለፎች ሁሉ የነበሩበት ተጨባጭ ነው።

عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله ﷺ قال
«لا تجعلوا بيوتكم مقابر....» رواه مسلم، 1/539

ሙስሊም ከአቡሁሑረይራ በተዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ (ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ... ) በማለት የተናገሩትን በማስመልከት አልሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር «ሐዲሱ በግልፅ የሚያመላክተው፤ በማንኛውም መልኩ በቤት ውስጥ መቅበር እንደተከለከለ ነው» ብለዋል። [ፈትሁልባሪ 1/130]

ይህ ግንዛቤ የአል ሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር ብቻ አልነበረም። የኢስላም አዒማዎች በዚሁ መልኩ ከልክለዋል።
አል ኢማም ማሊክ እንዲህ ብለዋል፤
لا يُدفن أحد في بيته ولا في بستانه إلا لضرورة
ብለዋል። [አልሙደወነቱል ኩብራ 1/155]

ለሽርክ መስፋፋት ምክንያት እንዳይሆን ወይም ሙስሊም ካልሆኑ ሰዎች ጋር ላለመመሳሰል እና መሰል ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው።
በተለይ ደግሞ በማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ክብር የሚቸረው ሰው ሲሆን ክልከላው ይጎላል። ምክንያቱም በተውሒድ ላይ የሚደቀነው አደጋ የከፋ ስለሚሆንና ብዙ መዘዞችን ስለሚያስከትል ነው። ወደ ጥፋት የሚያዳርሱ መንገዶችን መዝጋት (ሰድ`ዱ ዘራኢዕ) ታላቅ መርሆ መሆኑ አያጠያይቅም።

አል ኢማሙ አሽ`ሻጢቢይ እንዲህ ብለዋል፤

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to ተንቢሃት Tenbihat - ኢስላማዊ ህግጋት እና ተግሳፃት:

Shortcuts

Share