24/03/2022
https://vm.tiktok.com/ZMLujytRr/
መፅሕፍ እናንብብ on TikTok Reply to
መፃሕፍት የጥበብና የአዕምሮ መዝገብ ናቸው፡፡ አዕምሮም የነ
24/03/2022
https://vm.tiktok.com/ZMLujytRr/
መፅሕፍ እናንብብ on TikTok Reply to
24/03/2022
መፅሕፍ እናንብብ on TikTok 10 አስገራሚ የማንበብ ጥቅሞች
tiktok.com/
20/03/2022
ከትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው ወደ አማራ ክልል እየተሰደዱ የሚገኙ ወገኖቻችንን በፍቅር በመቀበል ያላችሁን አካፍላቹ በኢትዮጵያዊነት ባህል እንክብካቤ እያደረጋችሁ የምትገኙ መልካም ኢትዮጵያውያን ሁሉ ብድራችሁን ፈጣሪ ይክፈላቹ።
20/03/2022
የሲሚንቶ ፋብሪካ ባለቤቶች እና ሲሚንቶ ደብቀው ዋጋ በማናር እጃቸው ያለበት አሻጥረኞች የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደሆነ ታውቋል፡፡ ዋና ዋናዎቹ እንዳይሸሹ በደህንነት ራዳር ውስጥ ገብተዋል፡፡
20/03/2022
"እኛ በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለብን ጠንቅቀን የምናውቅና ያቀድነውንም ዕቅድ በፈለግነው ቦታና ሰዓት ያለአንዳች ከልካይ በእርግጠኝነት የምናሳካ ህዝቦች ነን።"
ቭላድሜር ፑቲን በሞስኮ ሉዝሂኒኪ ስታዲየም ለተሰበሰቡ ሩሲያውያን የተናገሩት
15/03/2022
NATO እና ዩክሬን ከሩሲያ ሚሳኤሎች አስበልጠው የሚፈሯቸው የሩሲያ Chechnya ወታደሮች።
🇷🇺🇷🇺🇷🇺🇷🇺🇷🇺🇷🇺
👉አስፈሪው የቼቺንያው መሪ " Ramzan Kadyrov " ዩክሬን ገብቷል። የ Chechnya ወታደሮች እስከ 20,000 የሚደርስ ጦር ሲሆን በአደገኛ ተዋጊነታቸው እና ወደር የለሽ ጀግንነታቸው ይታወቃሉ።
👉" Ramzan Kadyrov " የchechnya republic ስልጣንን ከአባቱ የተረከበ ሲሆን በጋለ ብረት አንቀጥቅጦ የሚገዛ መሆኑ ይነገርለታል። ፑቲን ወደ ስልጣን ሲመጣ በሩሲያ ድጋፍና በጀት እጅግ የፈረጠመ Paramilitary ያቋቋመ ሲሆን በሩሲያ ሶሪያ ጣልቃ ገብነት የዚህ ሰው ጦር አብሮ ሲዋጋ የከረመ ነው። በሶርያ ከተሞች የ ISIS ታጣቂዎች በገቡበት ገብተው ያደኑት እነሱ ናቸው።
👉ወታደሮች በከተማ እና በፎቅ ለፎቅ ሽምቅ ውጊያ ምትክ የማይገኝላቸው ተዋጊዎች ናቸው። ከቀናት በፊት በሩሲያ special ወታደሮች እጅ እንደወደቀ የሚነገርለት የkiev አንቶኖቭ አየር ማረፊያ የያዙትም እነዚህ የchechen ወታደሮች ናቸው።
👉checheniya የሩሲያ ፌደሬሽን አካላት ከሆኑ 85 ግዛቶች አንዷ ናት። በሩሲያ የፌዴራል ስርአት ውስጥ ከሚገኙት 22 ራስ-ገዝ ሪፐሊኮች ውስጥ ትገኛለች። ከ100 በላይ ብሔሮች በሚኖሩበት ሩሲያ ከፍተኛ ራስን በራስ የማስተዳደር አቅም የተሰጣት ራሷን እንደ republic የምታስተዳድር ግዛት ናት። Ramzan Kadyrov ለፑቲን ጥብቅ ታማኝነት አለው። ራሱንም የፑቲን እግረኛ ወታደር ሲል ይገልፃል።
👉የዩክሬን ሰራዊት በ Kiev የከተማ ውጊያ የሚያደርጉ ከሆነ ካለጥርጥር የሚዋጉት ከchechen ወታደሮች ጋር ነው። ዩክሬንን የሚያርበደብደውን ይሄ ነው። የምዕራቡ አለም ጩኸትም ለዚ ነው። "Ramzan Kadyrov" ከወታደሮቹ ጋር ሆኖ በጦር ግንባር እያለ የሚያሳየው ቪዲዮ ከተለቀቀ በኋላ የአለም መገናኛ ብዙሃን እየተቀባበሉት ይገኛል። ከዩክሬኗ ዋና ከተማ ከ Kiev ጫፍ ሆኖ ለዩክሬይን መሪዎች በአስቸኳይ እጃችሁን ስጡ ያለበለዚያ የሚኖራችሁ ጊዜ እጅግ በጣም አጭር ነው ብሏል።
👉ሩሲያ Kiev'ን የከበበች ሲሆን በቀናት ውስጥ በቁጥጥር ስር ታደርጋታለች ተብሎ ይጠበቃል። Kiev'ን ለመቆጣጠርም የቺቺንያ አስፈሪዎቹ ጦረኞች ፊታውራሪ ሆነው እየተፋለሙ ይገኛሉ። 👌
Mihreteab G Desta
05/03/2022
ካራ ማራ ዳግማዊ አድዋ
የሶማሊያ ጦር በምስራቅ በኩል 700 ኪሜ.፣በደቡብ በኩል ደግሞ 300 ኪሜ. የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ ገብቶ ነበር
የሶማሊያ ጦር በምስራቅ በኩል 700 ኪሜ.፣በደቡብ በኩል ደግሞ 300 ኪሜ. የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ ገብቶ ነበር
ከዛሬ 42 ዓመታት በፊት የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጦር ድንበር ጥሶ ወደ ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ገብቶ የነበረውን የሶማሊያን ሰራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት በማስወጣት ካራማራ ተራራ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ማወለብለቡን ታሪክ ያስታውሳል፡፡
የካራማራ ድል ከደርግ ውድቀት በኋላ በመንግስት ደረጃ የማይከበር ድል ቢሆንም የቀድሞ ሰራዊት አባላትና ግለሰቦች በተነሳሽነት እያከበሩት ነው፤ በዓሉም ብሄራዊ በዓል ሆኖ በመንግስት እንዲከበር ይፈልጋሉ፡፡
ሶማሊያ በ1952 ዓ.ም ከጣሊያንና ከእንግሊዝ ቅኝ ገዢዎች ነፃነቷን ባገኘች ማግሥት የሀገሪቱ መሪዎች “ታላቋ ሶማሊያን እንገነባለን” የሚል ህልም ማለም ጀመሩ፡፡ በዚህም ምክንያት በ1953 ዓ.ም የድንበር ላይ ትንኮሳ ጀምረው በ1956 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብድረሺ አሊ ሸርማርኬ እንዲሁም በ1969፣ በ1972 እና በ1973 ዓ.ም ደግሞ ፕሬዝደንት ዚያድ ባሬ (ሜጀር ጀኔራል) የሶማሊያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ እንዲገባና ወረራ እንዲፈፅም ሰራዊታቸውን አዘዙ፡፡
በተለያዩ ጊዜያት ደግሞ ሰርጎ ገቦችን አስታጥቆ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት በማስገባት ፈንጅ በማፈንዳት፣ ድንገተኛና የደፈጣ ጥቃቶችን በመፈፀም እንዲሁም ባለስልጣናትንና ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ በመውሰድ ለኢትዮጵያ ሰላምና ልማት መሰናክል ሆነው መቆየታቸውንም በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደራዊ መሪዎች ይገልጻሉ፡፡
ይሁን እንጂ እነዚህ የሶማሊያ ወረራዎችና ጥቃቶች በኢትዮጵያ አሸናፊነት ቢመለሱም ዘላቂ ሰላም ሊሰፍን አለመቻሉ ይገለጻል፡፡ በተለይ የ1969 ዓ.ም የዚያድ ባሬ ወረራ የኢትዮጵያ ድንበር በምስራቅ በኩል እስከ 700 ኪሎ ሜትር እንዲሁም በደቡብ በኩል ደግሞ እስከ 300 ኪሎ ሜትር በሶማሊያ ሰራዊት እንዲደፈር፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲሞቱና እንዲቆስሉ፣ አካል ጉዳተኛ እንዲሆኑ በአጠቃላይ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በርካታ የሕይወትና የንብረት መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ያደረገ ነበር፡፡
ኢትዮጵያ በወቅቱ በብዙ የውስጥ ችግሮች (የመሐል አገር የሥልጣን ሽኩቻ፣ የነጻነት ጠያቂዎች በሃገር ቤት፣ የተለመደው ድህነትና ረሀብ …) ተወጥራ ስለነበር የዚያድ ባሬ ወረራ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባት ነበር ይላሉ የታሪክ ጸሐፊያን፡፡
ሶማሊያ ኢትዮጵያን ለመውረር ሰፊ የሰው ኃይል፣ የትጥቅ፣ የስንቅ፣ የሥነ ልቦና ዝግጅት ስታደርግ ቆይታለች፤ኢትዮጵያ ግን በውስጣዊ ችግሮች ከመወጠሯም ባሻገር በወቅቱ የነበራት የሰራዊት ቁጥርና ጥራትእንዲሁም የትጥቅ አቅርቦት እጅግ የተመናመነ እንደነበርም ነው የሚገለጸው፡፡
300ሺ የሚሆን ሕዝባዊ ሰራዊት በአጭር ጊዜ ሰልጥኖ ለውጊያ የተሰለፈ ሲሆን ፤የኩባና የደቡብ የመን መንግሥታት ጦራቸውን ይዘው ከኢትዮጵያ ጎን መሰለፋቸውም ይታወሳል፡፡ ሶቭየት ኅብረት በጀኔራል ፔትሮቭ የሚመሩ ወታደራዊ አማካሪዎቿን ለኢትዮጵያ ረዳት አድርጋ ወደ ኢትዮጵያ መላኳንም መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከኢትዮጵያ በኩል ተሰልፈው ህይወታቸውን ላጡ ኩባውያ ወታደሮች በአዲስ አባበ መታሰቢያ ተሰርቶላቸዋል፡፡
የሶማሊያን ሰራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት የማባረሩ ዘመቻ በሐምሌ ወር 1969 ዓ.ም ተጀመረ፡፡ ኢትዮጵያውያን በምድርና በአየር አስደናቂ ገድል ስለመፈጸማቸው የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ተናግረዋል፡፡
05/03/2022
#አድዋ
የአድዋ ጦርነት በየካቲት ፳፫ ቀን ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. በኢትዮጵያና ኢጣሊያ መካከል የተካሄደ ውጊያ ሲሆን የአንደኛው የኢትዮጵያና ጣሊያን ጦርነት ክፍል ነው። በ ኢትዮጵያ አሸናፊነት የጣልያን የቀኝ ግዛት ማስፋፋት ተኮላሸ።
ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ እንቀላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤
***
ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ
መድፍ አገላባጭ ብቻለብቻ፤
***
የአድዋ ሥላሴን ጠላት አረከሰው
ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሰው፤
የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው፡፡ የመላው ዓለም ተፈጥሮአዊ ግብር እና ሰብአዊ ክብር የታደሠው፤ በእውነትና በፍትህ ህልውናና ምልዓት ላይ የተሰካ ትልቅ ጥርስ የተነቀለው … በአድዋ የታላቅ ህዝቦች ታላቅ ድል ነው፡፡
ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ስንሄድ 1066 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታላቁ ጦርነት የተደረገበትና ታላቁ ድል የተገኘበት ሥፍራ አድዋ ከተማና የከተማው ግድም ገመገሞች ይገኛሉ፡፡ በኢትዮጵያውያን አቡሻኽር (Julian calendar) የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም፤ ወይም በአውሮጳውያን የዘመን አቆጣጠር (Gregorian Calendar) February (የካቲት) መጨረሻ እና March (መጋቢት) መጀመሪያ ላይ 1896. ለጦርነቱ መነሻ የሆነው ውል የተፈፀመው በዚሁ ዘመን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 468 ኪሎ ሜትር ርቀት ግድም ከውጫሌ ከተማ ግርጌ ከአምባሰል ተራራ ሥር ወሎ ውስጥ ንጉሥ ይስማ እየተባለ በሚጠራ ሥፍራ ነው፡፡
ሸልዶ ተራራ ወይም (ሶሎዳ ተራራ)፤ ማርያም ሸዊቶ፤ አዲ ተቡን፤ ረቢ አርእየኒ (እግዚሃር አሳየኝ)… በመሠኘት የሚታወቁት እነዚህ ገመገሞችና ተራራማ ሥፍራዎች ዋነኞቹ የጦር ግንባሮች ናቸው፡፡ በመቶ ሺህ የሚሠላ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ከአንድ ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የአውሮጳ ቅኝ ገዢ ወራሪዎችን ድባቅ ከመታና ረግጦ ካስወጣ በኋላ ከምሽቱ አራት ሰዓት ግድም (የካቲት 23 ቀን) እንዳማርያም ላይ ተሰባስቦ በአንድ እግሩ ቆሞ ቀኙን (ድሉን) ለሰጠው አምላክ ምሥጋና አቅርቧል፡፡ አባት ሆይ፤ ንቀውን የመጡ የአገራችንን ድንበርና ልዕልና የደፈሩ የአውሮጳ ኮሎኒያሊስት ወራሪዎችን እንድናሸንፍ (ድል እንድናደርግ) ስለረዳኸን እናመሰግንሃለን ...
ሃያ ዘጠኝ ሺህ ፈረሰኞችን ጨምሮ ከመቶ ሺህ እስከ መቶ ሃያ ሺህ የሚገመት አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር በባዶ እግሩ የተጓዘ የኢትዮጵያ የገበሬ ሠራዊት በወታደራዊ አካዳሚ የሠለጠነውን የአውሮጳ ወራሪ ጦር የካቲት 23 ማለዳ አሥራ አንድ ሰዓት ግድም ገጥሞ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ማሸነፉን አረጋግጧል ይለናል የታሪክ ተመራማሪው ጆርጅ በርክሌይ የአድዋ ጦርነትና ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ በተሰኘና ዳኘው ኃይለሥላሴ ወደ አማርኛ በተረጐሙት መጽሐፉ ላይ፡፡ የኢትዮጵያ ገበሬ ሠራዊት ፈረሱ ላይ ሆኖ የጋሻውን እምብርት መሬት ላይ እያጠቀሰ ጐራዴውን አየር ውስጥ እየቀዘፈ ባበደ መንፈስ (በተቆጣና በቆረጠ መንፈሥ) በጀግንነት ተዋግቷል፡፡
ጦርነቱ በተጀመረ ከአምስት ሰዓት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ሃምሣ ስድስቱም የኢጣሊያ መድፎች ሙሉ ለሙሉ ተማርከዋል፤ የቅኝ ገዢውን ወራሪ ሠራዊት ከመሩት ጀኔራሎች ጄኔራል አልቤርቶኒ ሲማረክ የሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ ከጥቂት አጃቢዎቹና በሽንፈት ከተበታተኑ የኢጣሊያ ወታደሮች ጋር ሸሽቷል፡፡
05/03/2022
የአሜሪካ የኮንግረስ አባላት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ ኤችአር 6600 የተባለ ረቂቅ ሕግ አስተዋውቀዋል።
ይህ በኒው ጀርሲው የኮንግረስ አባል ቶም ማሊኖወስኪ ለአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተዋወቀው ረቂቅ ሕግ ተፈጻሚ የሚሆን ከሆነ "በኢትዮጵያ ላይ የሚያርፈው ጠንካራ የአሜሪካ ክንድ" ይሆናል ተብሎለታል።
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥት አጥብቀው የተቃወሙት ይህ ረቂቅ ሕግ በፕሬዝደንት ባይደን የሚጸድቅ ከሆነ አሜሪካ በደኅንነት፣ በፋይናንስ/በኢንቨስትመንት እና በኢሚግሬሽን ጉዳዮች ላይ አዲስ ማዕቀብ ትጥላለች።
የዚህ ረቂቅ ሕግ ይዘት ምንድን ነው?
ይህ ረቂቅ ሕግ ለአሜሪካ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 'የኢትዮጵያ የመረጋጋት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ሕግ' (Ethiopia Stabilization, Peace, and Democracy Act) በሚል ስያሜ ቀርቧል።
ረቂቅ ሕጉን ለምክር ቤቱ ያስተዋወቁት የኮንግረስ አባላት ሕጉ ተፈጻሚ ቢሆን በኢትዮጵያ መረጋጋት፣ ሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ጥረቶችን ለመደገፍ ያስችላል ይላሉ።
ይህ ረቂቅ ሕግ ጥር 27 2014 ዓ.ም. ለውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ፣ ለሕግ ጉዳዮች ኮሚቴ፣ ለፋይናንስ አገልግሎቶች እና ለመከላከያ አገልግሎቶች ተመርቷል።
የቪዛ እና የንብረት እግድ
ይህ ረቂቅ ሕግ በኢትዮጵያ መረጋጋት እና የዲሞክራሲ ሥርዓት እንዳይኖር ምክንያት ናቸው በተባሉ ግለሰቦች ላይ ተጠያቂነትን ለማምጣት ፕሬዝደንት ባይደን ማዕቀብ እንዲጥሉባቸው የሚጠይቅ ነው።
ግለሰቦች ላይ የሚያነጣጥሩት ማዕቀቦች የንብረት እግድ እና የቪዛ ማዕቀቦችን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም፦
በትግራዩ ጦርነትም ሆነ በአገሪቱ ባሉ ሌሎች ግጭቶች ዙሪያ የተኩስ አቁም ወይም ድርድር እንዳይደረግ እንቅፋት የሆነ ወይም ስምምነት እንዳይደረስ ጥረት ያደረገ፤
የትግራዩ ግጭትም ወይም ሌሎች በአገሪቱ ያሉ ግጭቶች እንዲስፋፉ ምክንያት የሆነ ወይም የተባበረ፤
የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸመ፣ የጦር ወንጀል፣ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት እና ሌሎች በደሎችን የፈጸመ፤
የሰብዓዊ እርዳታ እንዳይደርስ እንቅፋት የሆነ እና በሰብዓዊ እርዳታ ሥራ ላይ የተሰማሩ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ሕብረት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ የሰብዓዊ ድርጅት ሠራተኞች ላይ ጥቃት የሰነዘረ፣ ለመሰንዘር ያቀደ፣ የመራ፤
በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት የተሳተፈ ወይም በፋይናንስ የደገፈ፤
ንብረቱ እንዳይንቀሳቀስ በፕሬዝደንት ባይደን ይወሰናል። ከንብረት እግዱ በተጨማሪ ከላይ የተጠቀሱትን ወንጀሎች ፈጽመዋል የሚባሉ ግለሰቦች የጉዞ እገዳ ይጠብቃቸዋል።
ክልከላዎቹን ተላልፈው የሚገኙ ሰዎች ቀድሞ በነበራቸው ቪዛ አሜሪካ መግባት አይችሉም፤ አዲስ ቪዛ አመልክተው ማግኘት አይችሉም እንዲሁም ይዘው የሚገኙት ቪዛ ይሰረዛል።
እግዱ በላይ በተጠቀሱት ግለሰቦች ላይ ተፈጻሚ ለማድረግ የአሜሪካ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ከተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት፣ ከሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን (ኔቶ) አባል አገራት ጋር፣ ከአውሮፓ እና ከአፍሪካ ሕብረት እንዲሁም ከሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ይተባበራሉ ይላል ረቂቅ ሕጉ።
የደኅንነት እና ፀጥታ ድጋፍ ላይ የሚጣለው ገደብ
ይህ ረቂቅ ሕግ በፕሬዝደንቱ ከጸደቀበት ዕለት አንስቶ አሜሪካ ለኢትዮጵያ እና ለኤርትራ የምታደርገው የደኅንነት እና የፀጥታ ድጋፍ እንዲቋረጥ ይጠይቃል።
ይህ የአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ መልሶ የሚቀጥለው አሜሪካ ያስቀመጠቻቸው ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸው በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ በኩል ተረጋግጦ ለሚመለከተው የኮንግረስ ኮሚቴ ከቀረበበ