22/04/2026
MARVEL
Grade 7 and 8
EXAM BOOK
2015,2016 AND 2017 (E.C) ESSLCE
ENTRANCE TEST MATERIAL
👉አማርኛ
👉MATHEMATICS 👉SOCIAL STUDIES
👉GENERAL SCIENCE
👉CITIZENSHIP EDUCATION
COMPLETE SOLUTION
07/04/2026
የተወደዳችሁ!
የ"ዥዋዥዌ" ን ዳግም መታተም በማስመልከት ነገ ከዚሁ መፅሐፌ አንድ ታሪክ አጋራለሁ።
ጠፍታባችሁ ከነበር አሁን ጃፋር ጋር በሽ ነች።
🌸🌸🌸
ከደራሲ ህይወት እምሻዉ ገፅ የተገኘ!!
03/04/2026
ነገ ግን ቅዳሜ ነው
💠💠💠💠💠
++++
ወጣት ነው።
ደራሲ ነው።
ሃያ ስምንት ዓመት ሳይሞላው ሶስት መፅሐፍት ያሳተመ ታታሪ፣ በጊዜ መክሊቱን ያገኘ ብርቱ ልጅ ነው።
በተለይ በ' ዛሬ ቅዳሜ አይደለም' መፅሐፉ የተወደደው ናትናኤል ቀረዓለም ነገ ግን ቅዳሜ ስለሆነ በጃፋር የለገሀር መደብር የመጽሐፍ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ያደርጋል።
ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ብትመጡ ከሶስቱም መፅሐፎቹ ጋር በአካል ታገኙታላችሁ።
ለአንጋፋ ደራሲዎቻችን የምንሰጠው ክብር ጀማሪዎቻችንም ያበረታልና ከተመቻችሁ ኑ እና በርታ በሉት።
😘😘😘
ከደራሲ ህይወት እምሻዉ ገፅ የተገኘ
31/03/2026
እነሆ የመገናኛ ቀናችን ተቆርጧል!
የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 26 በአዲሱ እና ዘመናዊው የጃፋር መጻሕፍት መደብር የፊርማ ፕሮግራም ይኖረናል፡፡
በዕለቱ እንድንገናኝ፣ ጥቂት እንድንጨዋወት፣ አብረን ፎቶ እንድንነሳ አጥብቄ እወዳለሁ፡፡
እ ን ዳ ት ቀ ሩ !
ናትናኤል ቀረዓለም
25/03/2026
ሃገረ ትግራይ መፅሐፍ ስለ ኢትዮጵያ የተጻፈ መጽሐፍ ነው።ርእሱን ብቻ አይቶ የትግራይ ጉዳይ ማድረግ ስሕተት የሚሆነው ትግራይ እራሱ ኢትዮጵያ ስለሆነ ነው።
ደራሲው ርእሱን "ሃገረ ትግራይ" ቢለው ጥሩ ነበር የሚሉ አሉ።አልተሳሳቱም።
የመፅሐፉን ሽፋን ካያቹት ስለ ሕገመንግስቱ ክልሎችና አንቀጽ 39 ይመስላል። የመጽሐፉ ሽፋን ስእል ግን 86+ ሃገረ ቤር ቤረሰብ የጣደ እና እያቁላላ ያለ መሆኑን መካድ አይቻልም።
እኔ ደካማ ከሆንኩባቸው የእውቀት መስኮች በግሌ ታሪክ ዋናው ነው።
አገረ ትግራይ ግን ያለፈን የኢትዮጵያን ታሪክ ያጠኑ የተነተኑ ምሑራንን ስራ ብርቅዬው ትግራዋይ ኢትዮጵያዊው ጓደኛዬ ሙሉጌታ አረጋዊ በታሪክ በሕግ በፍልስፍና እና ፖለቲካ መነጽሮች አንጥሮ ወደፊት ለኢትዮጵያውያን የሚያዋጣንን መክሮናል።ከእነዚሕ ኢትዮጵያውያን ውስጥ ደግሞ የትግራይ ወንድሞችና እሕቶች እኩል ሚና አላቸው።የሚሻለንም ያ ነው።
ቁጭ ብለን ለስሜት ሳይሆን በስሌት ለአባቶቻችን ሳይሆን ለልጆቻችን ስንል አደብ ገዝተን ኢትዮጵያን አክመን እንገንባ።አዋጭ ነው።
እያለን ነው።
ሙሌ ማእረ አመሰግንሐለው።
እስቲ አንብቡት።
Mulugeta Aregawi Kefe Hailu Get Toughe Zer Getahun Heramo Ja Liberty Wosenseged Gebrekidan Bineyam Firdawok Hawlet Ahmed
ከዶ/ር ኤርሲዶ ገፅ የተገኘ
22/03/2026
“ቀይ ባሕር ሲቀላ” መጽሐፍን ያነበባችሁ፣ ልታነቡ ያሰባችሁ፤ ማግሰኞ፣ መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም. 11፡00 ሰዐት ላይ ለገሀር፤ አቢሲኒያ ባንክ ዋናው ቅርንጫፍ ሕንፃ ሥር የሚገኘው ጫካ ቡና ብቅ በሉና ከባለታሪኩ ዶክተር ፍርድአወቀ ማሞ ጋር ቡና እየጠጣን ስለ መጽሐፉ እና የካቲት ወር 1982 ዓ.ም. ምጽዋ ከተማ ምን ትመስል እንደነበር እንጨዋወት። መጽሐፉ ውስጥ አግኝተን የወደድናቸውን፣ ያሳዘኑንን፣ ያስለቀሱንን፣ ያስገረሙንን፣ … ብዙ ብዙ ያሳሰቡንን፤ በወቅቱ ከባለታሪኩ ጋር አብረው ያንን የጭንቅ ጊዜ ያሳለፉ ሰዎችን እያነሳን፤ መጨረሻቸውን እየጠየቅን አብረን እናመሻሽ!
ከዘላለም ምፅላል ፋንቱ ገፅ የተገኘ
15/03/2026
ምናሴ (ማስረሻ) "እግዚአብሔር መከራዬን ሁሉ አስረሳኝ" ሲል ዮሴፍ ለወንድ ልጁ ያወጣው ስም ነበረ:: "ጸሎተ ምናሴ" በተሰኘው የንስሐ ጸሎቱ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቀው የይሁዳ ንጉሥ ምናሴ ታሪክ ደግሞ በግል ሕይወታችን ላይ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እንዲሁም በሀገራችን ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች ወለል አድርጎ የሚያሳይና በጸጸት ባሕር አስጥሞ ለኀዘናችን ማስረሻ የሚሆን ታሪክ የነበረው ሰው ነው::
"ጾምና ምጽዋት" ፤ "ጸሎት ለመንፈሳዊ ሕይወት" ፤ "ፍካሬ ሞት ወሕይወት" የመሳሰሉ በሳል መጻሕፍትን ያበረከቱልን መምህር ቃኘው ወልዴ አሁን ደግሞ "ምናሴ" የተሰኘ የእኩለ ጾም አበርክቶ አምጥተውልናል::
መምህር ቃኘው ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪክ የአበውን የሥነ ጽሑፍ ዘዴ ተጠቅመው የራሱን ታሪክ በአንደበቱ በማናገር በልቦለዳዊ ግለ ታሪክ (fictional autobiography) መልክ ውብ መጽሐፍ አበርክተዋል:: ሃይማኖት ቀመስ ልቦለዳዊ የትረካ አጻጻፍን ለሚቶሎጂያዊ ቅዠቶችና ያልተረጋገጡ አወዛጋቢ ታሪኮችን ለመፍጠር ከመዋል ይልቅ እንዲህ ለሀገራዊ ለግላዊና ለመንፈሳዊ ቁስሎች መድኃኒት መሆን የሚችል የአጻጻፍ ስልት እንደሆነ የሚያሳይ ድንቅ ሥራ ነው:: መጽሐፉ የአንድን ንጉሥ ድቀትና የእግዚአብሔርን ምሕረት ብዛት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና ለንስሐ የሚጠራ በምናሴ አገላለጽ "ቸርነቱን እየለመንን በልባችን ጉልበት እንድንሰግድ" የሚጣራ መጽሐፍ ነው::
ከዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ ገፅ የተወሰደ….