22/12/2021
Part 2
ብርሃኑ ወደነሱ የበለጠ እየቀረበ ሲመጣ ከ4ቱ አንደኛው ባትሪ አንስቶ ብርሃን በሚመስለው መጓጓዣ ላይ ያበራበታል።
ነገር ግን ይህ ሰው ትክክለኛ ውሳኔ አልነበረም የወሰነው!
መጓጓዣው ብርሀኑን የበለጠ አስፍቶ 4ቱንም ወደ ላይ አንሳፎ ይስባቸዋል።
ከዚህ ቅፅበት በኋላ ግን 4ቱም ምን ተከስቶ እንደነበር የሚያስታውሱት ነገር አልነበረም።
ጠዋት ሲነጋም እራሳቸውን ቀኑን ሙሉ ያሳለፉበት ሀይቅ ዳርቻ ጋር ያገኙታል።
ነገር ግን ምሽቱን የት እንዳሳለፉ ትዝም የሚላቸው ነገር የለም። ከመሀከላቸው አንደኛው ግን ድካምና ህመም ቢጤ ይታይበት ነበር።
ፈጠን ብለውም ህክምና ወደሚያገኝበት ሆስፒታል ይወስዱታል። ህክምናውን ከጨረሰ በኋላም በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተነግሯቸው ጉብኝታቸውን አቋርጠው 4ቱም ወደየቤታቸው ይመለሳሉ።
ከተመለሱ ከሳምንታቶች በኋላ ግን እነዚ ጓደኛማቾች ተመሳሳይ ቅዠትን በተደጋጋሚ መመልከት ይጀምራሉ።
ይሄ ቅዠት ሲደጋገምባቸውም ወደ Ufo ኤክስፐርቶች ጋር ያመራሉ።
የተፈጠረውን በሙሉም ለufo ኤክስፐርቶቹ ይነግሯቸዋል።
ወጣቶቹ የዛን ቀን ምሽት እጅግ በሚያስፈሩ ፍጡሮች ታግተው እንደተወሰዱ እና ከመኋላቸው ከአንደኛው ላይ ለምርመራ በሆነ መሳሪያ ከእጁ እነኚ ፍጡራኖች ደም ሲወስዱ በቅዠት መልክ እንደተመለከቱ ተናግረዋል። የUfo ኤክስፐርቶችም ለወጣቶቹ የሰመመን ምርመራ ያረጉላቸው ሲሆን በአስገራሚ ሁኔታ የሶስቱ ውጤት ተመሳሳይ ሆኖ የአንደኛው ተለይቶ አጊንተውታል።
በስተመጨረሻም የጥበብ ተማሪ እንደመሆናቸው የተመለከቱትን እንዲስሉ የተጠየቁ ሲሆን እነሱም በወቅቱ ተመልክተው የነበሩትን በሙሉ በወረቀት ላይ ስለው ለUfo ኤክስፐርቶች አስረክበዋል።
ኤክስፐርቶቹም የተለያዩ ምርመራዎችን ካደረጉ በኋላ እነዚ ወጣቶች ያጋጠማቸው እገታ የእውነት እንደነበር በውጤታቸው አረጋግጠዋል።
የሚያስገርመው ግን ከሳሉት ስዕል ውስጥ አንደኛው ጓደኛቸው አለመኖሩ ነው።
ስዕሉም እንደምከተለዉ ቀርቦዋል
21/12/2021
እ.አ.አ 1976 ላይ 4 በጥበብ ት/ት ቤት ውስጥ የተወዋቁ ጓደኛሞች በእረፍት ጊዜያቸው ለመዝናናት ሜን ወደተባለ ገጠራማ ከተማ ያመራሉ።
በመጀመሪያ ቀን ጉዞቸውም አሪፍ ጊዜን ቦታው ላይ የሚገኙ አንዳንድ ቦታዎችን በመጎብኘት ያሳልፋሉ።
በ2 ኛው ቀን ውሎዋቸው ግን ቀኑን በሰላም ያሳልፉና ምሽት ላይ ያልጠበቁት ነገር ይገጥማቸዋል።
እሱም ምሽት በግምት 4 ሰአት አካባቢ በሰማይ ላይ አንድ የሚያበራ ነገር ለእነሱ በቅርቡ ርቀት ላይ ሆኖ ይመለከታሉ።
ነገር ግን ይህ የሚያበራው ነገር ብዙም አልቆየም ወዲያው ነበር የጠፋው ምንም እንኳን እነዚ ጓደኛማቾች በሁኔታው እጅግ በጣም ግራ ቢጋብም ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ ረስተውት የራሳቸውን ጨዋታ መጫወት ይጀምራሉ።
አይነጋ የለ ጠዋት ሲነጋ ጠብቀውም አሳ ለማጥመድ አቅራቢያ ወደሚገኝ ሀይቅ ያመራሉ።
ሙሉ ቀኑንም ሀይቁ ዳርቻ ላይ ያሳልፉና ሲመሽ ወደ ካምፖቸው ይመለሳሉ።
ጨዋታቸውንም እንደ ትላንቱ ሞቅ ባለ ሁኔታ እየተጫወቱ ሳለ ትላንት ያዩትን ብርሃን በድጋሚ ሰማይ ላይ ይመለከቱታል።
በአሁኑ ግን ብርሃኑ እጅግ በጣም ወደ ነሱ ቀርቦ ነበር።
Part 2 ይቀጥላል.....
18/03/2021
❤️ ኢትዮጵያ እኮ ❤️
1.ሳይንሳዊነቱ ተወዳዳሪ የሌለው የምድሪቱ ቀዳማይ ፊደል ያላት ።
2.ለመጀመሪያ ግዜ ፈረስና አህያን አዳቅሎ በቅሎ የፈጠሩባት ሳይንሳዊ ጠበብቶች ሀገር ።
3.በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ግዜ ከአንድ ወጥ ዲንጋይ ተፈልፍሎ የተሰራ ሕንፃ ቤተክርስቲያን ያላት (ቅ.ላልይበላ) ።
4.በዓለም ላይ ሁሉም አይነት አየር ከውርጭ እስከ ከፍተኛ ሙቀት ያላት ብቸኛ ሀገር ።
5.ለሌላው ዓለም ያበረከተችው ተክሎች
=>ዝግባ
=>ዋንዛ
አራዊቶች
=>ዋልያ
=>የሜዳ አህያ
ከምግብ
=>ጤፍ፣ቡና ያሉ ድንቅ የተፈጥሮ ምርቶች
6.የዲሞክራሲ ስርዓትን ለግሪኮች ያስተማረች ቤተ-ህዝብ፣ቤተ-ምልክና፣ቤተ-ክህነት ሶስቱን የስልጣን ክፍፍል ለዓለም ያበረከተች ።
7.በተፈጥረ ፀረ-ቫይረስ የሆኑትን ቁንዶ በርበሬ፣ሚጥሚጣ ፀረ-ትላትል ኮሶ፣መተሬ፣እንቆቆ በምድሯ አፍርታ የምትገኝ ብቸኛ ሀገር ።
8.የአምላክን ግማደ መስቀል፣ተከርኦተ-ርዕስ በቅርስነት የያዘች ፣ታቦተ ፅዮንን ይዛ በመጠበቅ የኖረች ሀገር ።
9.የቅዱሳን አስደናቂ ቃልኪዳን ያላት ለምሳሌ በአቡነ አሮን ቃልኪዳን ከአናቱ ባዶ ሆኖ ዝናብ የማያስገባው ቤተክርስቲያን ያላት የዝንጆሮዎች አዝመራን አለመብላት ምስጢር ።
10.በቀኝ ገዥዊች ያልተንበረከከች ሀገር ፣ ነጭ ህዝብን በማሸነፍ የጥቁር ህዝብን ሀያልነት ያሳየች ጀግና ሀገር ።
11.የተባበሩት መንግስታትን ለመመስረት በአፍሪካ ብቸኛዋ የመጀመሪያ ሀገር የአፍሪካ አንድነት መስራችና መቀመጫ ሀገር ።
12.እንግዶችን በክብር በመቀበል ፍትህን፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ሀይማኖተኝነትን መመሪያዋ መሆኑን ያስመሰከረች ሀገር ።
13.በእስልምና ሀይማኖት ትልቅ ስፍራ ያላት ሀገር(የመጀመሪያውን አዛን የተናገረው ቢላል..) ።
14.በሌሎች ዓለም ቤተክርስቲያናት ያልተገኙ እንደ ኩፋሌ፣ሄኖክ፣ዮሴፍ ወልደኮርዮስ የብሉያት ኦርጂናል መፃህፍት የሚገኙበት ሀገር ።
15.በዘምናዊ ህክምናቸው ያልደረሱበትን በሽታዎች የሚፈውስ የፀበል ፀጋን የታደለች ሀገር ።
16.የመንፈስ አዛጦን የታደለች:- የስነ ነፍስን ፣የሀብተ መንፈስን(ሥነ-ልቦናን)፣የሥነ-ምግባር ሰናያት(ትዕግስት ፣ትህትና ፣አፍቅሮ ስብዕ፣ ንፅሐ-ህሊና ) የምድሪቱ መልካም ባህላዊ እሴቶች ጉዲፈቻ (ማደጎ ልጅ፣ ነፍስ ልጅ የብዙ ዘመናት ድልብ ባለ መልካም ባለ ቅርስ ይሉኝታ ፈሪሃ-እግዚአብሔር፣ይቅር ባይነት አትህቶ-ርዕስ ) ።
17.የቅዱሳት መፃህፍት የሀይማኖት መርሆዎች በህዝቦቿ መርሆዎች በህዝቦቿ አእምሮ ተፅፈው በተግባር የሚፈፀሙባት ሀገር ባሁኑ ጊዜግን?
18.ነውርን በግፍ የምታወግዝ ሰምቶ አደር ያልሆነች ሀገር ።
19.ድሆችን በፀበል በድግስ መልክ የምታበላ ብቸኛ ሀገር ።
20.ሲያስነጥስህ ይማርህ እንቅፋት ሲመታህ እኔን የምትል እናት ሀገር ።
21.አምላክ የሚወዳት በህዝቦቿ ሀጢያት ልክ ሳይሆን በሱ ድንቅ ቸርነት የሚያኖሯት የኛ መኖሪያ የኛ እማማ ኢትዮጵያ ።
ታሪክህን ስትጎረጎረው ልብህ በሀሴት ይሞላል ይሄ ሁሉ ድንቅ ማንነት አሁን የት ሄደ ብለህ ራስህን ስትጠይቅ ደሞ ታዝናለህ!
"በቃ ሀገርህ ይቺ ናት ዝምብለህ ውደዳት "
13/03/2021
🇪🇹 ጥበበ ኢትዮጵያ
በአገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ በአበው ጥበብ የተሰወሩት ጥንታዊ ጥበቦች አሁን ያለውን የአለም የቴክኖሎጂ አቅምና ሀይል መቀልበስ የሚችሉ ናቸው። ይህን ስል ከስሜታዊነት ተነስቸ አይደለም ብዙ ማስረጃወች ስላሉ እንጅ። አለም አሁንም ድረስ የሀገራችን ሉአላዊነት ለመንካት እንዴት እንደሚፈራ የአደባባይ ሚስጥር ነው ይህም ምክንያቱ የህዝቦቿ ጀግንነት፤ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የበላይነት ፤የተደራጀ አስፈሪ ጦርም ሆኖ አይደለም ፡፡
ሃገሪቱ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዋ ደሃ ፤ በፖለቲካ ርዕዮቷም የከሰረች ፤በየ ጊዜው በአሳደገቻቸው ልጆቿ ጡቷን የምትነከስ ምስኪን ሃገር ነች.. ጠላቶቿ ብዙ እያሉ በእየ ደጇፎቿ እያገሱ ታዲያ ግን ለማንም ወራሪ ራሷን አታስደፍርም፤ ለጠላቶቿ ግርማዋ ያስፈራል፤ በሃይል ለመጣ ወራሪ ከሃይሉ በላይ ትሆናለች፤ የነካት ሁሉ ሲፈረስ ሲቃጠል እነ የመን ና ሶርያ እነ ሊቢያ ምስክሮች ናቸው .. ይህ በተላይ ለታሪክ አጥኝወች ሆነ ለብዙወቻችን ሚስጥር ነው....ታዲያ ምንድነው የሃይል ምንጯ? ወዴትስ ነው የጥበቧ መገኛ? ደካማ ሲሏት ጠንክራ የምትገኝ፤ የወደቀች ሲሏት ሃያል ሁና የምትነሳ፤ ጠላቶቿ ብዙ ሳሉ የማትፈረስ ፤መሪወቿ ደካማ ሳሉ የማትጠፋ፤ ጠባቂወቿ ሲሸሹ የማትወርር.. እች እንቁ፣ ክቡር፣ ጽሩይ ፣ሃገር ብሔሯ ወዴት ነው? ዘመን የማይሽረው አልደፈር ባይነቷስ ከየት ነው? በለን/ብላችሁ አበውን ብትጠይቁ ? ልዩ የሆነ የመላእክት ጥበቃ ስላላት ነዉ የሚል መልስ ታገኛላችሁ... ፡፡
አበው ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ እግዚአብሔር ቃሉን ሲሰጥ አይወስድም፤ የተናገረውን ለዘመናት ያጸናል፤ የዘረጋውንም እጂ እስከ ልጂ ልጂ አይጥፍም.. ፤ መሬቷ በውጭ ወራሪ እንዳትመዘበር፤ የኖህ ልጂ ነገደ ካም በምርኮ እንዳይወድቅ፤ ለባርነት እንዳይገዛ፤ የእግዚአብሔር ቃል በዘሮቹ ላይ ጸንቷልና ምስኪኗን ሃገር አይነኬ አስፈሪ አደረጓታል ።
ወደ ቀደመዉ ነገራችን እንግባና
ይህም ከከርሰ ምድር ማእድናት፣
ከስነህዋ ጥበባት፣ ከህክምና ጥበብ፣ ከአስተዳደር ጥበብና ከመከላከያ ጥበብ ጋር የተዛመዱ ናቸው። እነዚህ ጥበባት የተሰወሩት በነስማዝያ ጭፍራ
ከሚመሩት ምእራባውያን ዘረፈና ሴራ ለመታደግ እንደሆነ እናምናለን።
ምእራባውያኑ እነዚህን ጥበባት
ለማግኘት ብሎም ተተኪው ትውልድ እነዚህ የአያቶቹን ጥበባት እንዳይረዳ በርካታ መረጃዎችን በርዘዋል፣ በርካታ ሺህ መፃህፍቶቻችንን ሰርቀዋል አሰርቀዋል፣ በርካታ ቅርሶቻችንንም አቃጥለዋል፣ በተሰራው ዘመን ተሻጋሪ ሴራም ኢትዮጵያዊ ስብእናችንንም ለውጠውት አሁን ላይ እነርሱን ለመሆን እየታተርን እንገኛለን።
ይህ ዘመን አብቅቶ የተሰወሩት የሚገለጡበት ዘመን እንዲመጣ የነስማዝያ ስልጣኔ ተንኮታኩቶ
የአያቶቻችን ጥበብ እንዲያንሰራራ እያንዳንዳችን እራሳችንን በኢትዮጵያዊ ስብእና በማብቃት ቅርሶቹን የሚጠብቅና ለአገር ጥቅም የሚያውላቸው መንገድ
ጠራጊ ትውልድ መገንባት አለብን። ለውጥ የሚጀምረው ከግለሰብ ነውና እራሳችንን በማብቃት ቤተሰባችን እናብቃ። በኢትዮጵያ ስብእና የበቃ
ቤተሰቦችን ማፍራት ከቻልን መንፈሳዊና ማህበረሰባዊ እሴቶችን የተረዳ ንቁ ማህበረሰብ መገንባት ይቻለናል። በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ጠንካራና
ንቁ ማህበረሰብ መፍጠር ከቻልን የጥንቷን ኢትዮጵያ መገንባት እንችላለን። ስለዚህ የትንሳኤውን መንገድ እራሳችንን በጥበብና በምግባር በማብቃት እንጀምር። ያኔ በመላዉ አለም እንዲህ ይባላል "ኢትዮጽያ ተነሳች"....
አሜን ጌታ ሆይ የኢትዮጵያን ትንሳኤዋን አሳየን ፡
11/02/2021
የኢትዮጵያውያን የዘመን ስሌት....
ጠቢባን የሆኑ አባቶቻችን የዘመን ስሌትን በሚገባ ተንትነው ዘመናዊቷ አለም ከምትጠቀምበት አቆጣጠር ረቀቅ ባለ መልኩ እስከ ሳድሲት ማለትም 0.00000185 ሰከንድ ድረስ አስለተዋል።
መሬት በፀሐይ ላይ በምታደርገው ኡደት ን ተረድተው የጊዜ መለኪያ እና መቁጠሪያ አስቀመጠውልናል ....
1ኛ ሳድሲት ይህ ቁጥር 0.00000185 ሰከንድ ነው።
2ኛ ኀምሲት ይህ ቁጥር 0.00011 ሰከንድ ነው።
3ኛ ራብዒት ይህ ደግሞ 0.0067 ሰከንድ ነው።
4ኛ ሣልሲት ይህ ደግሞ 0.4 ሰከንድ ነው።
5ኛ ካልዒት ይህ ደግሞ 24 ሰከንድ ነው
6ኛ ኬክሮስ ይህ ደግሞ 24 ደቂቃ ነው።
60 ኬክሮስ=1 ዕለት ወይም 24 ሰዓት ነው። ይህ ደግሞ 1 ሰዓት 2.5 ኬክሮስ ነው ማለት ነው።
ጨረቃ በቀን ከፀሐይ 1 ኬክሮስ ከ 52 ካልዒት ከ 31 ሣልሲት በአነሰ ነው።
በቀን 1 ኬክሮስ በ30 ቀን 30 ኬክሮስ ይሆናል።
በ2 ወር 60 ኬክሮስ ይሆናል። 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 እለት ስለሆነ።በ2 ወር 1 እለት በ12 ወር 6 እለት
ታበራለች ማለት ነው።
በ12 ወር ወይም በአንድ አመት 5 ቀንና 15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት ይሆናል።...... የቀረችው 52 ካልዒትን ልቀይረው.... 52 ካልዒት×30 ቀን×12 ወር=18720 ካልዒት በአመት ይገኛል።
ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንለውጠው 312 ኬክሮስ ይመጣል።በመቀጠል 30 ሣልሲት×30
ቀን×12 ወር 10800 ሣልሲት ይመጣል ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንቀይረው 3 ኬክሮስ ይሆናል።
ይህ ማለት የ 52 ካልዒትየ 30+(1) ሳልሲት ጠቅላላ ስንደምረው ... 312+3=315 ኬክሮስ ይሆናል።
ይህንን ወደ እለት ስንቀይረው 5 ቀን ከ15 ኬክሮስ ይሆናል።....
ይህች 5 ቀን ተሰብስባ ጷግሜን ናት.....።
የተረፈችው 15 ኬክሮስ ለ4 አመታት ስትጠራቀም... በ4 ዓመት 4×15=60 ኬክሮስ ወይም አንድ እለት ይሆናል። በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 የምትሆን በዚህ ምክንያት ነው።.....
ከላይ የ 30 ዋን ሳልሲት ሰርቸ አንዷን አላሰላሆትም....አንዷ ሣልሲት በ600 ዓመት 1 ቀን ትሆናለች።ይኽውም 1 ሣልሲት×30 ቀን×12 ወር×600 ዓመት 216000 ሣልሲት ይገኛል ይህንን ወደ
ኬክሮስ ስንቀይረው 60 ኬክሮስ ይሆናል።60 ኬክሮስ ደግሞ አንድ ቀን ወይም እለት ነው። ስለዚህም በ600 ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 7 ትሆናለች ማለት ነው።...
ወይም በቀላል መንገድ ላሳያችሁ...
አንድ ቀን =365 እለት ከ 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት /
ወይም 365 ቀን ከ 6 ስዓት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ነው...36o ቀን + 5 ቀን ጳጉሜ .. ይሆንና 6 ስአት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ትተርፍለች... የተሰባሰበችው 6 ስአት በ አራተኛው አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ስትሆን ጳጉሜ 6 ትሆናለች። ትራፊ 2ደቂቃ ከ 24 ሰከንዷ ትሰበሰባለች ይህ ማለት በ 600 አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ትሞላለች።
ይህ በ 600 ኛው አመት ጳጉሜን 7 ያደርጋታል ማለት ነው.....
አበቅቴ እና መጥቅእ
አበቅቴ ማለት ተረፈ ዘመን ማለት ነው።ይህም ማለት ጨረቃ ከፀሐይ ባነሰ የምታበራበት የጊዜ መጠን ነው።ፀሐይ በዓመት 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት
ታበራለች።ጨረቃ ደግሞ 11 ቀን አንሳ 354 ቀን ታበራለች።በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት አበቅቴ ይባላል።
ስለዝህ በባቶች በተገለጠላቸው መጠን 11 ጥንተ አበቅቴ ይባላል።
መጥቅዕ ማለት ትረጉሙ ደወል ሲሆን አጽዋማትን እና በዓላትን የሚያስገኝ ነው ከዚህ ላይ ተንተረሰን በዚህ ቀን ይህ ጾሜ በዚህ ዕለት ይህ በዓል ለማለት ያስችላል...።
መጥቅዕ እና አበቅቴ ተደምረው 30 መሆን ስላለባቸው መጥቅዕ 30-11=19 ይሆናል።
ስለዚህ በመጀመሪያው ዓመት 11 አበቅቴ ከሆነ በሁለተኛው አመት 22 ይሆናል በሦስተኛው 33 ይሆናል።ከ30 በላይ ሲሆን በ30 አካፍለን ቀሪውን እየያዝን አበቅቴን እናወጣለን ስለዚህ 3 ይሆናል።ከዚያ በአራተኛው 3+ 11=14 እያለ ይሄዳል።አበቅቴና መጥቅእ ሁለቱ ተደምረው 30 ስለሚሆኑ አንዱ ከተገኘ ሌላኛውን ከ30 በመቀነስ እናገኘዋለን።
አለም ከተፈጠረች ጠቅላላ ዕድሜ 5500+2013=7513 አመት....ስለዚህ በሚቀጥለው ዓመት ዘመኑ ዘመነ ማን ነው የሚለውን ለማወቅ ስንፈልግ ዓመተ ዓለሙን ለ4 አካፍለን
ቀሪው 1 ከሆነ ዘመነ ማቴዎስ ፤ቀሪው 2 ከሆነ ዘመነ ማርቆስ ፤ቀሪው 3 ከሆነ ዘመነ ሉቃስ ያለ ቀሪ ከተካፈለ ዘመነ ዮሐንስ ነው።
የዓመቱ መስከረም 1 ቀን መቼ መቼ ትውላለች?
መስከረም አንድ ቀን መቼ እንደምትውል ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከመጠነ ራብዒት ጋራ ደምረን በእለታቱ መጠን በ7 አካፍለን
ቀሪው 1 ከሆነ ማክሰኞ ፤ቀሪው 2 ከሆነ ረቡእ፤ቀሪው 3 ከሆነ ሐሙስ፤ቀሪው 4 ከሆነ አርብ፤ቀሪው 5 ከሆነ ቅዳሜ፤ቀሪው 6 ከሆነ እሑድ፤ ያለ ቀሪ ከተካፈለ ሰኞ ይውላል።
ስለዚህ አሁን ቀጣይ መስከረም 1 መቼ ይውላል የሚለውን ለማወቅ።
(7513+1878)÷7=1341 ቀሪ 4 ይሆናል።
ቀሪው 4 ከሆነ አርብ ይውላል።ስለዚህ መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም አርብ ይውላል ማለት ነው።
መስከረም 1 በዋለበት ሚያዝያ 1 ይውላል
ጥቅምት 1 በዋለበት ግንቦት 1 ይውላል
ህዳር 1 በዋለበት ሰኔ 1 ይውላል
ታሕሣሥ 1 በዋለበት ሐምሌ 1 ይውላል
ጥር 1 በዋለበት ነሐሴ 1 ይውላል።
ይህም ማለት ለምሳሌ መስከረም 1 ቀን አርብ ከዋለ ሚያዝያ 1 ቀንም አርብ ይውላል ማለት ነው።ታህሣሥ 19 ሰኞ ከዋለ ሐምሌ 19ም ሰኞ ይውላል ማለት ነው።..
አጽዋማትና በአላትን ዕለት ለማውጣት የምንጠቀምበት መባጃ ሐመር ይባላል ይህንን ለመቀመር የምናገኘው መጥቅዕ+መጥቅዕ የዋለበት የእለት ተውሳክ አድርገን ማገኝነት ይቻላል።
07/02/2021
አዳም ዘ -ኢትዮጵያ
የአዳም አባት መሬት ነው ከአፈር ተፈጥሯልና።
አዳም የተፈጠረው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።የተፈጠረበት አፈር "ስውሩ አፈር" ይባላል።አዳም በምድር ላይ የኖረው 930 ዓመት ነው።አዳም የሚለው ቃል አደመ፥ አማረ፣ተዋበ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ነው፡፡ስለዚህ የመጀመሪያው ፍጡር አዳም የስሙ ስያሜ የመጣው ከግእዝ ነው።
# አዳም የተፈጠረው ከአራት ባህርያተ ሥጋ ማለትም፦ከነፋስ፣ከእሳት ፣ከውሀ፣ከመሬት
እንዲሁም ከሶስቱ ባህርያተ ነፍስ ማለትም ከልብ ፣ከቃል፣ከእስትፋስ ሲሆን የተፈጠረበት ቀን እለተ አርብ 3 ሰዓት ላይ ነው።ሲፈጠር የ30 አመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጠረ።
# አዳም የት ተፈጠረ ለሚለው በመጽሐፈ ሄኖክ ላይ
“ኤልዳ” በሚባል ቦታ ተፈጠረ ይላል። ኤልዳ ደግሞ
ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው። ምክንያቱም አስሌዳውያን
ወይም ኤልዳውያን የሚባሉ አሁንም ድረስ ጎጃም ውስጥ አሉ። ሄኖክ በመጽሐፉ ኤልዳ ነው የተፈጠረው ይላል ኤልዳ ከግዮን አትርቅም።
# ግዮን ደግሞ የኤደን ገነት የሚያጠጣ ወንዝ ነው። አዳም ኤልዳ ከሚገኝ አፈር ተፈጥሮ በ40ኛ ቀኑ የግዮን ወንዝ ወደሚያጠጣት የኤደን ገነት አስገባው።አዳም ለሰባት አመታት የኖረው የአዴንን ገነት በሚያጠጠው ግዮን (አባይ) ዙሪያ ነው።በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ከቁጥር 13 ግዮን የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል።የሚያበራ ዕንቁና የሚያብረቀርቅ ዕንቁም ይገኝበታል።የግዮን ምንጭ ደግሞ ጎጃም ሰከላ ውስጥ ነው።
#*በሳይንሳዊ ምርምር እንደተረጋገጠው በጎጃም በስተምዕራብ ፋዞግሊ የሚባል የወርቅ ማውጫ ቦታ ነበረ።ንጉሥ ድግናዣን በጎጃም በስተምዕራብ የሚገኘውን ፋዞግሊ የተሰኘውን የወርቅ ማምረቻ ለመቆጣጠርመቶ ሺህ የሚያህል ሠራዊት ይዞ በበጌምድር በኩል ሲዘምት በአሸዋ ተውጦ ቀረ።
# ፋዞግሊ የወርቅ ማውጫን ዐፄ ካሌብ በአገዎች ያስጠብቀው ነበር።በደቡብ እየገነነ የመጣው የዳሞት መንግሥትም ይህንን የወርቅ ማውጫና የወርቅ ጎዳና ለመቆጣጠር ወደ ሰሜን ተጉዞ ነበረ።የዛግዌ መሥራች መራ ተክለ ሃይማኖትም በዚህ የወርቅ ጎዳና ጥበቃ ላይ ከተሠማሩት ኃያላን የጦር አዛዦች መካከል አንዱ ነበረ።ከላይ በጠቀስነው መረጃ አግባብ በግዮን ዙሪያ የሚያበራውና የሚያብረቀርቀው ዕንቁ ከታዋቂው የወርቅ ማውጫ ብዙም አይርቅም።
# አዳም በምድር ላይ የኖረው 930 ዓመት ነው። የተቀበረው ኮሬብ በሚባል ቦታ ነው።ኮሬብ የሚባል ቦታም በአምሓራ ሳይንት ይገኛል።ክሬብ የዮቶር ርስት ነው።ሙሴ በግ የሚጠብቅበት የነበረ ተራራ ነው።
*አራራት ተራራ የሚገኘው ጎጃም ዘጌ ነው
*የኖኅ ሚስት መቃብር የሚገኘው ጭልጋ አይከል ነው።
*የኖኅ መቃብር የሚገኘው ጎንደር ፋሲለደስ ግንብ ከተገነባበት ቦታ ላይ ነው።
*ግማደ መስቀሉ የሚገኘዎ ቤተ አምሓራ ግሼን ማርያም ነው።
*የቃልኪዳን ታቦቱ የሚገኘው አኩስም ነው።
*ቅዱስ ኡራኤል የክርስቶስን ደም የረጨበት ቅድስ ጽዋ ተሰውሮ የሚገኘው መንዝ-እመጓ ቆጵሮስ ተራራ ላይ ነው።
*በዚህ ጉዳይ ጥንታዊ ሰነዶች፣የተለያዩ መረጃዎች አሉኝ። አሠናድቸ በረድፍ በረድፍ የምጽፈው ይሆናል።እንዲያውም ከሺህ ዓመታት በፊት በግእዝ ቋንቋ የተጻፈ ጥንታዊ ሰነድ በአንድ አርሶአደር ጎጃም ውስጥ በአንድ ዋሻ ተገኝቷል።የጊዜና የገንዘብ ጉዳይ ሆኖ ነው እንጂ ይፋ ለማድረግ አስበናል።ቀርቦ ከሚያግዘን ይልቅ ዘርፎን ለመሄድ የሚያስበው ብዙ ስለሆነ በምስጢር ተይዟል።ይኼ ክቡር ጥንታዊ ሰነድ አነጋገሪ መሆኑ አይቀርም።ያልተገለጡትን ይገልጣቸዋል ብለን እናስባለን።የተሰወሩ ቦታዎችን፣ታሪኮችን፣ማዕድ
ኖችን፣ፒራሚዶችን፣ቤተ መንግሥቶችን፣ቤተ መቅደሶችን ይጠቁማል ብለን እናስባለን።እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይሆናል።
06/02/2021
የቃልኪዳን_ምድር ኢትዮጵያ
ዘር ሲጣል አንድ ነው ሲነሳግን ብዙ ነው ወርቅ በእሳት እዲፈተን ።
የዘብሩ መነኩሴ አባ ኤኔታ አክሊሉ ከ 50ሺ ሊቃውንት በላይ ያፈሩ ለጵጵስና ማእረግ ደርሰው እቢ አሻፈረኝ ያሉ የ130 አመት እድሜ ባለፀጋ ለቅድስና ማእረግ የደረሱ አሁን ስላለው መግስት እዲ ብለዋል።
"ጥሩ ስሜት አይሰማኝም ስለ እርሱ የተነገረ ትንቢት የለም እኔ የማውቀው የኢትዮጵያን_ትንስኤ_ሳላይ_አልሞትም"
ዝምተኛው መንኩሴ አባ ላቀ(ዘጊሸን ደብረ ከርቤ) ኢትዮጵያን ትንሳኤ አዲህ ይገልፁታል።
መይሳው ካሳን የኢትዮጵያን የመጀመሪያው ጵጳስ አቡነ ሰላማ በመቅደላ ሲያነግሱት ማን ብዬ ልሹምክ ሲሉት
መይሳው ካሳም ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ብለው ስምሹሙኝ አላቸው አቡነ ሰላማም ዳግማዊ አፄ ታዎድሮስ ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ ብለው ሾሙት።
አፄ ቴዎድሮስን ዳግማዊ ያሉበት ምክንያት ነበራቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ከዳግማዊ ቴዎድሮስ በፊት የነገሰ ቀዳማዊ_ቴዎድሮስ የሚባል የሚባል አልነበረም ታድያ አፂ ቴዎድሮስ ለምን ዳግማዊ አሉ ቢባል የኢትዮጵያን_ትንስኤ_የሚያበስረው አንድም አድርጎ የሚገዛት ቀዳማዊ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉስ ወደ ፊት እደሚነሳ የኢትዮጵያን ትንሳኤ የሚናገረው ፍካሬ_እየሱስ የሚባለውን መፀሀፍ አንብቦ ስለተረዳ ነው።
ይህን ንጉስ አፄ ቴዎድሮስ ይመኘው ስለነበር ስሙን አፄ ቴዎድሮስ ካስባለ ቡሀላ መጠሪያውን ዳግማዊ አስባለው። አፄ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ ለመግዛት የተነሳው ይህን ፍካሬ እየሱስ መሰረት አድርጎ ነው።
ይህንን ሚስጥራዊ መፀሀፍ የተረዱት እግሊዞች አፄ ቴዎድሮስን ለማጥፋት ተነስተዋል የኢትዮጵያ መግስት ከአፄው ሹሩባ በላይ በጅምስ ብሩዝ የተዘርርፈው በንግስቲቱ እጅ ያለውን ፍካሬ እየሱስ የብራና መፀሀፍ ጭምር መጠየቅ አለበት።
ይህ ሚስጥራዊ መፀሀፍ ሁለት ቦታ ብቻ ይገኛል አንደኛው በእግልዝ ሲሆን ሁለተኛው በኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል።
ይህን_መፀሀፍ_ያነበቡ_አባ_ላቀ_እዲ_ይላሉ
ኢትዮጵያ አህዛብ ይገዛታል የኢትዮጵያ ድንኰኖች ይቀጠቀጣሉ ከመከራዋም ቡሀላ ከምሥራቅ የሚነሳው ህፃን ቴዎድሮስ የሚባል ነጭ ጭራ በእጁ የሚይዝ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ድንበር ላይ ይቆማል ኢትዮጵያንም አንድ አድርጎ ይገዛል ኤርትራም በድሮው በኢትዮጵያ ትጠቃለላለች። ይህ ህፃን ቴዎድሮስ የተባለው የአለምን ቴክኖሎጂ ሶፍትዌሩን ያጠፋዋል የአሜሪካም ሀያልነት ያከትማል በምትኩም ኢትዮጵያ አያል ሀገር ትሆናለች አንድ ሀይማኖት አንዲትም ብሔር የሌላት አዲት ሀገር አዲት ባንዲራ ያላት ትሆናለች።
ቀዳማዊ አፄ ቴዎድሮስ ተብሎ በቤዛዊት ማርያም (ባህርዳር ላይ) ንግስናውን ይቀበላል።
ይህ ባለምጡክ አዕምሮ ንጉስ ባንድ ገዳም ተሰውሮ እደሚኖር አባቶች በስፋት ይናገራሉ።
አለም_ኢትዮጵያ_መግባት_ጭንቅ_ይሆንባታል አለም ሁሉ የሚመኛት የእግዜብሄር ሀገር የክርስትያን ደሴት የሰላም ቤት የፍቅር የበረከት ሀገር ትሆናለች።
እናም በስተመጨረሻ አባ ላቀ - ይህን ቀን ታዩአት ዘንድ የመከራዋ ጊዜ ያጥርላት ዘንድ ስለ አንዲት ሀገራቹ አልቅሱ ለምኑም።
አዲስ ብርሀን ለማየት የግድ መጨለሙ አይቀርም።
የአድነት ማገሩ ኢትዮጵያዊነት ማሰሪያው የሀገር ፍቅር አድነቱ አንተ የሞትክላት ሀገር የተመኘትም የኢትዮጵያ ትንሳኤ አስኪመጣ ሹሩባክ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ህያው ምስክር ሆኖ ይቀመጣል።
ከአባቶቻችን የሰማነውን አካፈልናቹ።
#ሼር ይደረግ ለወገን
29/01/2021
[የውጪ ሀገር ተመራማሪዎችን ትኩረት የሳበው አስደናቂዎች ድብቆች የኢትዮጵያ ማዕድናት
♥ በባሕር ማዶ በነበርኩ ጊዜ በአንድ ታላቅ ሚዚየም ውስጥ ከአንድ የውጪ ተመራማሪ ጋር በድንገት ተገናኘን፤ ይኽ የባሕር ማዶ ሰው ግእዝን በሚገባ የሚችል በመኾኑ እጅግ ተደንቄ ጨዋታችንን በዚኽ በግእዝ ቋንቋ አደረግነው፤ የጻፍኳቸውን ከግእዝ ቋንቋም የተረጐምኳቸውን ወደ 19 የሚጠጉ መጻሕፍቶቼ ስነግረው ብዙ የግእዝ ብራና መጻሕፍት በእጁ እንዳሉ ነግሮች ጥቂቶቹን ሊያሳየኝ ግን ሊሰጠኝ እንደማይችል ነግሮኝ በሌላ ቀን ቀጥሮ አሳየኝ፡፡
♥ በእጁ ከያዛቸው በርካቶች ጥንታውያት የኢትዮጵያ መጻሕፍት ውስጥ ጥናት የሚያደርግበትን ደማቅና ውብ የኾነችውን መጽሐፍ አውጥቶ አሳየኝ፤ ይኽችም መጽሐፍ የቀደምት ኢትዮጵያውያንን የማዕድን ዕውቀት የሕንፃ አሠራር ጥበባቸውን የያዘች ነበረች፡፡ እነዚኽ ድብቅ የኢትዮጵያ ማዕድናት በእጁ ከገባ ዓለምን በእጅጉ ሊያስደምሙ ጉድ ሊያሰኙ የሚችሉ ሕንፃዎችን ሊያስገነባ እንደሚችልና ለዚኽም ፍለጋ በሳተላይት ምስል የታገዘ ቊፋሮ ማድረግ እርሱና የጥናት ቡድኑ እንደሚፈልግ ነግሮኝ ተለያየን፡፡
♥ ይኽንን ከተመለከትኩ በኋላ ከሺሕ ዓመት በፊት የተሠሩ የቀደምት ኢትዮጵያውያን የሕንፃ ጥበብ በአግራሞት ማሰብ ጀመርኩ፡፡ እጅግ የተራቀቁ የሕንፃ ግንባታ መሣሪያዎች ከመሠራታቸው አስቀድመው ደንጊያ ፈልፍለው ሕንፃዎችን የሚገነቡ ነበሩ፤ በኢትዮጵያውያን ጠበብት የታነጹ ዓለምን ያስደነቁ በአክሱም የተሠሩ ሐውልቶች፤ ከአንድ ወጥ ዐለት በላሊበላ የተሠሩ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፤ በጐንደር ያለው የፋሲልና የነገሥታቱ አብያተ መንግሥትና እና ሌሎችም ከመሬት ተቆፍረው ያልወጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ከተሞች ይገኙበታል፡፡
♥ ኢትዮጵያ በማዕድናት የከበረች ሀገር ስለመኾኗ ኢዮብ ከ4000 ዓመት በፊት “ስለ ዛጐልና ስለ አልማዝ አይነገርም የጥበብ ዋጋ ከቀይ ዕንቍ ይልቅ ይበልጣል የኢትዮጵያ ቶጳዝዮን አይተካከላትም በጥሩም ወርቅ አትገመትም” (ኢዮ 28:18-19) ይላል፡፡
ስለኢትዮጵያ ንግሥት ስለ ማክዳም ስጦታ “ለንጉሡም መቶ ሀያ መክሊት ወርቅ እጅግም ብዙ ሽቱ የከበረም ዕንቍ ሰጠችው የሳባ ንግሥት ለንጉሡ ለሰሎሞን እንደ ሰጠችው ያለ የሽቱ ብዛት ከዚያ ወዲያ አልመጣም ነበር” ይላል (1ኛ ነገ 10፡10)
♥ በዚኽ ላይ ጥልቅ ጥናት ካጠኑት ተመራማሪዎች ውስጥ ሄሬንና ማውሪሴ ይገኙበታል፡፡ ሄሬን፡- “that the ancestors of these Ethiopians had long lived in cities and had erected magnificent temples and edifices” (የእነዚኽ የኢትዮጵያውያን ትውልዶች ዘሮች ከተማን ከትመው ይኖሩ የነበሩና ዕጹብ ድንቅ አስገራሚ መቅደሶችንና ሕንፃዎችን የገነቡ ናቸው) ይላል፡፡
♥ ተመራማሪው ማውሪሴና ዶክተር ዱራሱላም በምርምራቸው፡- ‘The ancient Ethiopians were the architectural giants of the past… ’ (ቀደምት ኢትዮጵያውን ጥንቱኑ በሕንፃ ጥበብ ታላቅ ዝና የነበራቸው ነበሩ … ድንቅ ሕንፃ ከዐለት የሚያቆሙ፤ ተራራ በስተው መተላለፊያ የሚሠሩ፤ ሰው ሠራሽ ሐይቅ ያዘጋጁ የነበሩና ዐልፎ ተርፎ ግብጽ ድረስ ኼደው ፒራሚዶችን የገነቡ ሕዝቦች እንደነበሩ በስፋት ጽፈዋል፡፡
♥ ካስነበበኝ ውስጥ በእጅጉ የገረመኝ አንድ የኢትዮጵያ መዓድን በግእዝ “በረቅ” ይባላል፤ በዕብራይስጥ ቋንቋ ባራቅ፤ በሱርስት ደግሞ ብራቅ ይባላል፤ የቀጥታ ትርጕሙ የመብረቅ ብልጭታ፤ መፍለቅ፤ ማንጸብረቅ ማለት ሲኾን፡፡ ይኽ ማዕድን እንደ መብረቅ ብልጭታ የመሰለ ብጫ ቀለም ያለው ነበር፤ ይኽን ማዕድ
13/01/2021
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
#ቶኔቶር
ቶኔቶር በመባል ምትታወቅ ሀገር ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ናት። ቶኔቶር ማለት የአምላክ ሀገር ማለት ነዉ። ይህን ስያሜ የሰጣት የጥንት ግብጻዊያን ናቸዉ። የሰጡበትም በሁለት አበይት ዋና ምክንያት ነዉ። አንደኛው ለግብጽ ስልጣኔ ለመኖር ዋስትና የስትንፋሳቸዉ አካል የሆነዉ ናይል በቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ስለሚገኝ።
ሁለተኛዉ ለአማልክቶቻቸዉ የሚሆን ገጸ በረከት ዕጣን፣ የከበረ ሽቶና የከበረ መዓድን የሚያገኙት ከኢትዮጵያ ድንግል ምድር ሰለሆነ ቶኔቶር እንዲላት አስገዷቸዋል። እዉነትም ቶኔቶር የአምላክ ሀገር የአምላክ ሀገር ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ሁሉ በጇ ሁሉ በደጇ ነዉ። ምንም ነገር አልፏት አያዉቅም። የገነት መዐዛም ቢሆን።
#የመጀመሪያወቹ ዜማዎች የግእዝ በቅዱሰ ያሬድ አማካኝነት የተበረከተባት ቅድሰት ሃገር
#አራት ወራት የሚፈራረቁባት ቅድሰት ሃገር አበባዎች ወቅቱን ጠብቀው የሚያብቡባት ቅድሰት ሃገር ኢትዮጵያ
#እናንተ እሰራኤላውያን እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያውያን አደላቹሁምን በመባል በአምላክ የተመሰከረላት ሃገር
#የካህኑ መልከጸዲቅ ሃገር የዮቶር ሃገር
#የአባይ መነሻ የግዮን መፍለቂያ የገነት በር
#የኦሪት እና ሃዲሰ ኪዳን ቀዳሚ ሃገር ኢትዮጵያ
ላሰታ ላሊበላ ሂዱ ከአንድ ድንጋይ ሰር የተፈለፈሉ 11ውቅር 90ድግሪ ቀጥብለው የቆሙ ታምራዊ የሚመሰሉ መቅደሶችን
በየትኛውም አለም የሌሉት ቅዱሳን ፀበሎች በብዛት የሚፈልቁባት የታመመ ሁሉ የሚፈወሰባት ዘወትር ቅዳሴ ዜማ ሰአታታ ለአምላኳ የሚቀርብባት
እውነትም የአምላክ ሃገር ቶ.ኔ.ቶ.ር
Like 👍👍 share በማረግ ለወዳጅ ጓደኛ ያጋሩ
06/01/2021
ሊቃውንትን አነጋግሯል፤ የዓለም አቀፍ ተመራማሪዎችን ትኩረት ስቧል፤
ወንጌላዊው ማቴዎስ አመጣጣቸውንና ስጦታቸውን ተናገረ እንጂ ሀገራቸውንና
ስማቸውን አልጻፈም፨
ለማንኛውም ነቢያት ስለነዚኽ ነገሥታት ሀገር በትንቢት ምን ተናገሩ?
የሚለው ለሁሉም መልስ ይሆናል።
ከነቢያት ዳዊትና ኢሳይያስ የሰብአ ሰገል አመጣጥ ተገልጾላቸው ትንቢት
ሲናገሩ፤ ይልቁኑ ኢሳይያስ ሀገራቸው የሳባ ምድር ኢትዮጵያ እንደኾነና ኹሉም
ከዚኽ እንደሚኼዱ፦
"የግመሎች ብዛት፥ የምድያምና የጌፌር ግመሎች፥ ይሸፍኑሻል፤ ሁሉ ከሳባ
ይመጣሉ፥ ወርቅንና ዕጣንን ያመጣሉ የእግዚአብሔርንም ምስጋና
ያወራሉ" (ትንቢተ ኢሳይያስ 60: 6) አለ፨
ዳዊትም በመዝሙሩ ላይ ለአምላክ ልደት ስጦታ እንደሚመጣ ጠላት
ሰይጣን ጠላት ሄሮድስ እንደሚያፍሩ ኢትዮጵያውያን በፊቱ እንደሚሰግዱ፦
"በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፥ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ። የተርሴስና
የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብና የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን
ያቀርባሉ ነገሥታትም ሁሉ ይሰግዱለታል" (መዝ 71 (72):9-10) ይላል። ይህም
የትንቢት ቃል ሲፈጸም፦
“ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፥ ወድቀውም
ሰገዱለት፥ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም
አቀረቡለት።” (ማቴዎስ 2፥11) ይለናል።
በተጨማሪም ዳዊት "ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር ነገሥተ
ምድር ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር" ( ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር
ትዘረጋለች (ታደርሳለች)፤ የምድር ነገሥታት እግዘአብሔርን አመስግኑት"
በማለት ትንቢት ተናግሮላታል፨
ታላላቅ ሊቃውንት እንደገለጹት የግእዝ ቋንቋችን እንደሚያስረዳን "በጽሐ"
የሚለው የግእዝ ቃል ቀጥታ የዐማርኛ ትርጉሙ (ደረሰ) ማለት ሲኾን ታበጽሕ
ማለት ደግሞ (ታደርሳለች) ማለት ነው፨ "ሰፍሐ" ማለት ግን (ዘረጋ) ማለት
ነውና ትሰፍሕ ቢል ትዘረጋለች ባልን ነበር፤ መዘርጋት ማንም ሊዘረጋ ይችላል፤
ዘርግቶም ሊቀበልም ላይቀበልም ይችላል፤ ይኽቺ ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር
ኢትዮጵያ ግን "ታበጽሕ" (ታደርሳለች) ተብላ ተነግሮላታልና አምላኳ ሲወለድ
ሥጦታን በማቅረብ በእውነት አድርሳለች ነገሥታቱም አመስግነዋልና ይኽም
ከአምላኳ ለርሷ ብቻ የተሰጠና የተነገረላት ነው (መዝ 67:11)፨
ሥጦታም መስጠት ጥንቱኑ በብሉይ ኪዳን በነ ንግሥት ሳባ የጀመረችው
እንጂ ለሀገሪቱ እንግዳ አይደለም "ለንጉሡም መቶ ሀያ መክሊት ወርቅ እጅግም
ብዙ ሽቱ የከበረም ዕንቍ ሰጠችው፤ የሳባ ንግሥት ለንጉሡ ለሰሎሞን እንደ
ሰጠችው ያለ የሽቱ ብዛት ከዚያ ወዲያ አልመጣም ነበር" እንዲል (መጽሐፈ
ነገሥት ቀዳማዊ 10: 10)፨
ከምንኖርባት ፕላኔት መሬት ላይ ካሉ የዓለም ሀገራት በብቸኝነት ጌታችን
የተወለደበትን ወር ለክርስቶስ አምላኳ የሰጠች ብቸኛ ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት፤
ይኸውም ጌታ የተወለደበትን ወር "ታኅሣሥ" ብላለች በቋንቋዋ በግእዝ፤
ይኸውም በግእዝ ቋንቋ "ኀሠሠ" ማለት ፈለገ ማለት ሲኾን ታኅሣሥ ማለት
"ወርኀ ተኀሥሦ" (የማሰስ ወር፣ የፍለጋ ወር) ማለት ሲኾን፤ ሊቃውንት ይኽነን
ያሉበት ምክንያት ሦስቱ ነገሥታት "የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?
ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና" እያሉ አስሰው ፈልገውት
ስላገኙት ይኽ ሥያሜን ቀደምት አባቶቻችን ሰጥተዋል (ማቴ 2: 1-2)፨
ከዓለም ዐቀፍ ተመራማሪዎች ውስጥ ዊልያም ሊዮ ሀንስበሪና
ኢሀርፐር ጆንሰን Africa's Golden Historical facts እና በሌሎች በጥልቅ
ጥናታዊ ሥራቸው ላይ የሰብአ ሰገል መነሻ ሀገር ኢትዮጵያ እንደነበረች
"Casapar king of Ethiopia, Melchior King of Ethiopia, and
Balthazar king of Saba ... he brought the gift of frankincense ...
which was for a thousands years the capital city of African
Christian Kingdom" የሚልና ሌላም ገራሚ ጥናትን እናነባለን፨
https://books.google.com.et/books?id=NuEDAAA
AMBAJ&pg=PA86&lpg=PA86&dq=
በአውሮፓ የዜና መዋዕል ጥናትና ምርምር የያዘው የሰብዐ ሰገል
ትውልድ የነበረውን ካህኑ ዮሐንስ (Prester John) የሚሉት ታሪካዊ መሪን
ለማግኘት በዓለም ዙሪያ ባደረጉት ሰፊ ዐሰሳ ሥርወ መንግሥቱ ሕንድ ሳይኾን
ኢትዮጵያ እንደነበር ገልጠው ጽፈዋል (Thornton, Joe (2012). A Cultural
History of the Atlantic World, 1250-1820. Cambridge University
Press. pp. 16–17). https://www.blackpast.org/global-african-h
istory/prester-john/
ሰብአ ሰገል የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሲሆኑ ታላቁ ተመራማሪ ጆን ጃክሰን
"ethiopian and the origin of civilization" በሚለው ድንቅ መጽሐፉ ገጽ
28 ላይ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የሥነ ጠፈር ጥናት የተጀመረባት ጋላክሲን
ከነፕቶሎሚ አስቀድማ መሰየም የቻለች ሀገርና ለሌሎች ሀገር ጥናቱን
እንዳስተላለፈች በስፋት ገልጾታል፤ እነዚኽም ነገሥታት የሥነ ጠፈር (የኅዋ)
መርማሪዎች ከነበሩ ምንጩ እዚኽ መኾኑ ያስረዳል፨
ሌሎች ተመራማሪዎች በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሣው ቤዴን ጨምሮ
ሜልኩ (ሜልኪዮር) የሚባለው የፐርሺያ ንጉሥ እንደነበር ወርቅን በጌታ ፊት
እንዳቀረበና ከሰብአ ሰገል አረጋዊው ርሱ እንደኾነ ጠቅሷል፨
ማንቱሲማር (ጋስፖር) ደግሞ ንጉሠ ሕንድ ሲኾን በጌታችን ፊት ዕጣንን
ያቀረበው ርሱ መኾኑን ይጠቅሳሉ፨
በዲዳስፋ (ባልዛር) ደግሞ ጥቁሩው ንጉሠ ኢትዮጵያ እንደኾነ ሲገልጹ
መልኩም ጥቁር እንደነበር በመመስከር ከርቤን በአምላኩ በክርስቶስ ፊት
እንዳቀረበ ጽፈዋል፨ ዛሬ ድረስ ምዕራባውያን በሚሠሩት የልደት የፊልም
ተውኔትና ሠዓሊዎቻቸው በሚሥሏቸው የሰብአ ሰገል ሥዕሎች ላይ
ኢትዮጵያዊውን አንዱን ጥቁር ያደርጉታል። https://www.washingtonpo
st.com/archive/lifestyle/style/1989/12/10/the-legend-of-the-
three-kings/c58d1b2c-4615-47a9-be76-7ca057b7ed37/
መተርጉማን ደግሞ ወርቅ ያመጣውን ከነገደ ሴም፣ ዕጣን ያመጣውን
ከነገደ ካም፣ ከርቤ ያመጣውን ከነገደ ያፌት ያደርጉታል። በኹሉም ብንመረምር
የኢትዮጵያ የክርስትና ታሪክ በሀገሪቱ የሚጀምረው በ34 ዓ.ም. ሳይኾን ልክ
ጌታችን ሲወለድ በ 1 ዓመተ ምሕረት መሆኑ ነው፨
ዛሬ ድረስ በምድራችን የሚኖሩ ሀገራት ኹሉ በዲዮናስዮስ ኤክስጊዩስ
በተፈጠረው ስሕተት ክርስቶስ የተወለደበትን ዘመን በመሳሳት 7 ዓመት
ጨምረው ተሳስስተዋል፤ ይኽነን ስሕተታቸውን የሮማ ካቶሊክ መሪ የነበሩት ፓፕ
ቤኔዲክት በጻፉት መጽሐፍ ያመኑ ሲኾን፤ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ
ሳትጨምር ሳትቀንስ ልደተ ክርስቶስን በትክክል የምታከብር ብቸኛ የዓለማችን
ሀገር ናት (http://www.telegraph.co.uk/news/worldnews/the-
pope/9693576/Jesus-was-born-years-earlier-than-thought-clai
ms-Pope.html )፨
[ደስ በሚያሰኘው በጌታችን ልደት በዓል ዋዜማ ስለ ሰብአ ሰገል
በጥቂቱ በኢትዮጵያዊው ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ተጻፈ]
Error 404 (Not Found)!!1
16/11/2020
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ምስጢረ ጣና
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ጣና ባህላዊ ታሪካዊ፣ጂኦሎጂካዊና ሥነ ውበታዊ እሴት ባለፈ ከባድ ምስጢር አለ።እጅግ በጣም ከባድ ምስጢር። በጣና ሐይቅ ዙሪያ ከሚገኙት አብያ ክርስቲያናት ደኖች እና የአበባ ዝሪያዎች ያለምንም ጥርጥር የእውቀት ማነስ እንጅ መድሀኒት ናቸው።
እነዚህ አብያተ ክርስቲያኖች ከባድ ምስጢር አለ በእጅ የያዙት ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል ሆኖብን እንጅ ገዳማቱን ለማወቅ በመጨረሻም ለማጥፋት የምስጢር ማህበረሰቡ በPedro Paez፣Jeronimo Lobo፣Alfonsi Mendes፣ ፖርቱጋላዊው ሚሲዮናዊ ማኖኤሊ ደ አልሜዳ፣ ጀምስ ብሩስ አማካኝነት ሲመረመር ቆይቷል። 'The hidden of treasure Ethiopia' በሚለው መጽሐፍ ውስጥ ጣናን ከነቅርሶቹ እንደሰለሉ ገልጾ ዋና ዓላማቸው "አዲሱ የኢሉሚናቲና 666 የአገዛዝ እቅድ ሊከሽፍ የሚችለው ጣና ደሴቶች በሚገኝ ጥበብ ነው" ብለው እንደሚያምኑ መጽሐፉ አስቀምጦታል።
በጣና ደሴቶች ዙሪያ ያለው የተደበቀው ምስጢር ምንድነው? አባቶቻችን ያካተተ ሰፊ ጥናት ይጠይቃል።
1.ከኤዶም እየወጣ ገነትን ከሚያጠጡ ወንዞች መካከል ሁለተኛው ግዮን ነው። ግዮን ወይንም አባይ የኢትዮጵያን ምድር (7) ጊዜ ይከብባል።የሚያበራ እና የሚያብረቀርቅ ዕንቁም ይገኝበታል። (ዘፍ 2፥13)
2.አዳም የተፈጠረው የግዮን ወንዝ ከሚወጣበት ኤዶም ነው።
3.ኖህ ከማየ አይኅ የጥፋት ውኃ ልጆቹ፣ ሚስቱና የልጆቹ ሚስቶች የዳኑት በመርከብ ነው። በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት በአቡነ ሒሩት አምላክ የተመሰረተው የዳጋ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን የተሠራው በኖኅ መርከብ ቅርፅ ነው።
4.የኖኅ መርከብ ማየ አይኅ መጉደል ሲጀምር በ7ኛ ወር ከወሩም በ27ኛው ቀን በአራራት ተራሮች ላይ ተቀመጠች።አራራት ተራራ ደግሞ የሚገኘው ከዚሁ ጣና ነው።
5.ከክርስቶስ ልደት በፊት በጣና ቂርቆስ የኦሪት መስዋዕት ይቀርብ ነበረ፥ ዛሬም አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ከአናቱ ላይ እንደ ሙቀጫ የተቦረቦረው ድንጋይና የኦሪት የብረት መስዋዕት ማቃጠያ በሥፍራው ይገኛሉ።
6.ጣና ቂርቆስ ገዳም ለሙሴ የተሰጠው የቃል ኪዳን ታቦቱ ፅላተ ሙሴ ለ800 ዓመት የተቀመጠችበት ቦታ ነው።
7.አስገራሚ ነገር የኦሪት መስዋዕት እና ታቦተ ጽዮን ምስጢር ለሚገባው ሰው ከእነዚህ ቀጥሎ ድግሞ ድንግል ማርያም ልጇን ይዛ ወደ ምድረ ግብጽ በተሰደደችበት ወቅት ለ3 ወራት ከ10 ቀን በዚሁ ገዳም ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ቆይተዋል። ድንግል ማርያም በገዳሙ የነበራትን ቆይታ አጠናቃ ስትመለስ “ፀአና በደመና” በደመና ጫናት የተባለው በጊዜ ብዛት ለአሁኑ የሐይቁ መጠሪያ ስም “ጣና” መሠረት ሆኖታል።
8.ቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያውን የዜማ መጽሐፉን የፃፈውና ብዙ ተግባራትን ለመከወን የመረጠው ጣና ቂርቆስን ነው፡፡መጽሐፍ ሲጽፍ ለጥቁርና ቀይ ቀለማት መበጥበጫነት ይጠቀምባቸው የነበሩ ከድንጋይ ተቦርቡረው የተሠሩ ጉድጓዶች፣የቅዱስ ያሬድ ድጓና ካባ
በገዳሙ ይገኛሉ።
እነኚህ ፊትለፊት ሁሉም ሰው የሚያያቸው የተገለጡ የጣና በረከቶች ናቸው ነገር ግን በምስጢር ተይዘው ተደብቀው ያሉ ብዙ የብራና መፃህፍት፣ በሃይቅ ውስጥ ያሉ ወደ አራቱ አቅጣጫ የሚሄደ መንገዶች፣ የደሴቶቹና የዋሻዎቹ ሚስጥሮች.... #ዴርቶጋዳን የፃፉት ሰዎች በአንድ እውነት ላይ ተመስርተው ፅፈውታል። ሁሉም በግዜያቸው እንደሚገለጡም አምናለው።
Share በማረግ ለወዳጅ ዘመድ ያጋሩ
24/09/2020
ስለ ዶክተር ኢንጂነር ቅጣው
የዶክተር ቅጣው እጅጉ አጭር የሕይወት
ታሪክ...
ዶክተር ቅጣው እጅጉ የካቲት 16 ቀን 1940
(እ.ኢ.አ) ከአባታቸው ከአቶ እጅጉ ሃይሌ እና
ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ በላይነህ በከፋ
ጠቅላይ ግዛት በቦንጋ ከተማ ተወለዱ። የአንደኛና
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቦንጋ፣ በዋከና በጅማ
ከተማ ካጠናቀቁ በኃላበባህር ዳር በሚገኘው ፖሊ
ቴክኒክ ኮሌጅየከፍተኛ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
ዶክተር ቅጣው ወደ ጃፓን አገር
በመሄድ በኦሳካዪኒቨርስቲ
በቋንቋና የጃፓን
ኢኮኖሚ፣በሄሮሺማ ዩንቨርስቲ
የኢንደስትሪ እናየአውቶሞቲቭ
ኢንጂነሪንግ አጥንተው
ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
በኋላም አሜሪካን
ሀገር ስኮላር ሺፕ አግኝተው በቢዝነስ
አድሚንስትሬሽን ማስትሬታቸውን በመጨረሻም
ለትምህርት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት በኤሮ-ስፔስ
ምህንድስና ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል።
ዶክተር ቅጣው በናሳ (NASA) በሲስተም
መሃንዲስነትና በጠፈር ሳይንቲስትነት የሰሩ
ሲሆን ከሌሎች መሃንዲሶችና ሳይንትስቶች ጋር
በመተባበር ለእኛ አለም (Planet Earth) እና
ለተቀሩት ፕላኔቶች የምርምር ሳይንስ (Planetary
Science Research and Exploration)
የሚረዱ የጠፈር መንኮራኩሮችና ሮኬቶች
ፈጥረዋል። ዶክተር ቅጣው በዚህ ከፈጣሪ በተቸሩት
ታላቅ ችሎታና እውቅት ለዚህች ለምንኖርባት ዓለምና
ሕዝብ ታላቅ አስተዋፅዎ አበርክትዋል። ከነዚህም
ጥቂቱን ለመጥቀስ ለናሳ(NASA) ሁለት የኤሮ-
ስፔስ መወርወሪያ ሜካኒዝም ለቦይንግ ኩባንያ
ሲሙሌተር (Flight Dynamic Simulator) እና
አድቫንስድ
ወይንም ኔክስት ጀነሬሽን (Advance or Next
Generation) በመባል የሚታወቁትን
ግሎባል ፖዚሽን ሳተላይት ሲስተም(Global
Positioning Satellite System)
ከፈለሰፉት ውስጥ አንደኛው ሰው እሳቸው ነበሩ
ዶክተር ቅጣው Trans Tech International
በመባል የሚታወቀውን ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ
ድርጅት በመመስረት የተለያዩ ሀገሮች የቴክኖሎጂ
አቅማቸውን እንዲያሳድጉ በአማካሪነት አገልገለዋል።
በተጨማሪም ለሀገራቸው በነበራቸው ታላቅ ፍቅር
‘የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ግንባር’ የተባለውን
ድርጅት በመመስረት ገንዘባቸውንና ጉልበታቸውን
ሳይቆጥቡ ለኢትዮጵያ ሰላም ፣ ብልፅግናና አንድነት
ትልቅ መስዋዕትነት የከፈሉ የትግል ሰው ነበሩ።
በእውነትም ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለም አንድ ትልቅ
ሰው አጣች ቢባል ማጋነን አይሆንም።
ዶክተር ቅጣው ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ስቴላ እጅጉ ጋር
በመልካምና በደስታ ጋብቻ ተጣምረው ይኖሩ ነበር።
ዶክተር ቅጣው፣ ቢንያም ያሬድ እና አቢጋኤል የተባሉ
የሁለት ወንዶችና የአንድ ሴት አባት ነበሩ።
ዶክተር ቅጣው እጅጉ ወደ ኦስትን ቴክሳስ
ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ መጥተው ድንገት
በደርሰባቸው ሕመም ምክንያት በታማኝነትና
በመሰጠት ሲያገለገሉትና ዘወትር ሊያዩት
ወደሚናፍቁት ጌታቸው እየሱስ ክርስቶስ በጃንዋሪ
12 ቀን 2006 በ58 አመታቸው ተሰብስበዋል።
ዶክተር ቅጣው እጅጉ በመልካም ባህሪያቸው
የተወደዱ፣ በትህትናቸው የተመሰገኑ፣ በስራቸው
የተደነቁ፣ በራዕያቸው ብዙ ተከታዮችን ያፈሩ፣
የብዙዎቻችን ተስፋና አርዓያ እንዲሁም የሀገር ኩራት
የሆኑ ታላቅ ሰው ነበሩ። ዶክተር
ቅጣውባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን አፍቃሪ፣ ዘመድ
ወዳጅ አክባሪ እና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን ፈሪ
ነበሩ።