Werabe University Museyd and Abdulselam counselors

Werabe University Museyd and Abdulselam counselors

Share

Abdu Passport

03/04/2026

ፓስፖርት ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ወደ እኛ ይደውሉ! 📞
​የፓስፖርት ወረፋ ለማስያዝ ከቤትዎ መውጣት አያስፈልግዎትም እኛ ሁሉንም ሂደቶች እናመቻቻለን!
​🔹 አዲስ ለማውጣት (መታወቂያ፣ የልደት ካርድ፣ ስልክ)
🔹 ለማደስ (የቆየው ፓስፖርት ኮፒ፣ ፎቶ፣ ስልክ ቁጥር)
🔹 ለጠፋ (መታወቂያ፣ ፎቶ፣ የፖሊስ ማስረጃ)
🔹 ስም እና እድሜ ለማስተካከል (አስፈላጊ ማስረጃዎች እና ፎቶ
​ጥራት ያለው እና ፈጣን አገልግሎት ከእኛ ዘንድ ያገኛሉ!
​📲 አሁኑኑ ይደውሉ

25/11/2025

ማስታወቂያ

ለ2014 እና 2015 ባች የተከታታይ መርሃ ግብር ት/ት የ1ኛ ዲግሪ ተማሪዎች በሙሉ

የ1ኛ ዲግሪ ተማሪዎች (2014 ባች ተማሪዎች ለ5ኛ ዓመት 1ኛ ሴሚስተር እና የ2015 ባች ተማሪዎች ለ4ኛ ዓመት 1ኛ ሴሚስተር) ምዝገባ የሚካሄደው ህዳር 22-23/2018 ዓ/ም መሆኑን አውቃቹ የሚመለከተው የስራ ክፍል በሚያሳውቀው የክፍያ መጠን መሰረት በዩኒቨርሲቲው የንግድ ባንክ አካውንት (1000246381357) ገቢ በማድረግና በዩኒቨርስቲው የፋይናንስ ቢሮ በአካል በመቅረብ የገቢ ደረሰኝ በስማቹ በማስቆረጥ ምዝገባ እንድትፈፅሙ እያሳሰብን በተጠቀሰው የምዝገባ ቀናት ምዝገባ ያልፈፀመ ተማሪ ህዳር 24/2018 ብቻ በቅጣት የምንመዘግብ ይሆናል፡፡

ማሳሰብያ፡

➢ በተጠቀሰው ቀን መመዝገብ የማትችሉ (በNG ወይም ተያያዥ ውጤት ምክንያት) ተገቢው ውሳኔ በመያዝ ታኅሣሥ 06/2018 ምዝገባ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

> የምዝገባ ወረቀት (Registration and Id renewal approval form) በሬጅስትራር ጽ/ቤት በተመደበላቹ መስኮት መውሰድ ይኖርባቸዋለ፡፡

25/11/2025

ማስታወቂያ

በ2018 ትም/ት ዘመን በሪሚድያል ፕሮግራም ወደ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ

በ2018 ትምህርት ዘመን ከትምህርት ሚኒስቴር ወደ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በሪሚድያል ፕሮግራም (Remedial) የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ታህሳስ 02 እና 03/2018 መሆኑን እያሳወቅን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ

ከ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ጀምሮ ያሉ የትምህርት ማስረጃዎች ኦርጅናልና አንድ የማይመለስ ኮፒ፤

ሁለት 3በ4 ጉርድ ፎቶ፤

ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣የትራስ ልብስ ፣ የስፖርት ትጥቅ፣የብሄራዊ መታወቂያ ካርድና የግብር ከፋይነት ቁጥር መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ማሳሰቢያ፡-
👉ሁሉም ተማሪዎች ከ21/03/2018-01/04/2018 registrar.wru.edu.et የሚለውን ማስፈንጠሪያ የተጠየቁ መረጃዎችን እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ fans

Photos from Werabe University Museyd and Abdulselam counselors's post 19/11/2025

Worabe University is giving Induction training for new teachers.

November 19, 2025 Werabe University is giving a training for new teachers.

Muhaba Nuredin, the director of the academic program of the university, said that the training will enable teachers to use their teaching methodology, knowledge, skills and competence to lead the teaching sector with knowledge and empower students with better teaching skills.

In addition, they have stated that it has a great contribution to ensure the quality of education as there is an experience exchange between teachers.

Sultan Hulchafo, Dean of the University Education and Ethics School, has given an explanation on the purpose and importance of the training.

The training will be held for the next three days including today.

Knowledge for wisdom.
Worabe University

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለአዳዲስ መምህራን ላለፉት ሶስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የሙያ ትውውቅ (Induction) ስልጠና ተጠናቀቀ

ሕዳር 10፣ 2018 (ወራዩ /ህ /አ/ አ/ ግ) ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለአዳዲስ መምህራን ላለፉት ሶስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የሙያ ትውውቅ (Induction) ስልጠና ተጠናቋል።

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተወካይና የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ መ/ር ከድር ሽፋ አዳዲስ መምህራን ያገኙት የሙያ ትውውቅ (Induction) ስልጠና ዕውቀት ውጤታማ የመማር ማስተማር ስራ እንዲሰሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።

ሰልጣኝ መምህራን ግንዛቤያቸውን አዳብረው በሚያስተምሩት የትምህርት ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ስልጠናው አዳዲስ መምህራን የማስተማር ስነ-ዘዴያቸውን እንዲያጎለብቱ እና ጥራት ያለው የመማር ማስተማር ስራ እንዲተገብሩ እንደሚረዳቸው ተገልጿል።

ለሰልጣኝ መምህራን የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ዕውቀት ለልህቀት
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ

18/10/2025

#ማስታወቂያ

በ2018 ትምህርት ዘመን ከትምህርት ሚኒስቴር ወደ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ እና በ2017 ትምህርት ዘመን በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሪሜድያል ኘሮግራም ተከታትላቹ ማለፊያ ነጥብ ያስመዘገባቹ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት የምዝገባ ቀናት ጥቅምት 20 እና 21/2018 መሆኑን እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
1) ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ
ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ ፣ የስፖርት ትጥቅ፣የብሄራዊ መታወቂያ ካርድና የግብር ከፋይነት ቁጥር መያዝ ይኖርባቸዋል።
2) በተጨማሪም በ2018 ትምህርት ዘመን ከትምህርት ሚኒስቴር ወደ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች ከ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰርተፊኬት ጀምሮ ያሉ የትምህርት ማስረጃዎች ኦሪጅናልና አንድ የማይመለስ ኮፒ መያዝ ይኖርባቸዋል።
3) ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ይሁን ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
4) በ2018 የትምህርት ዘመን አዲስ ወደ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በሪሜድያል ኘሮግራም የምትመደቡ ተማሪዎች ጥሪ ወደ ፊት የሚገለጽ መሆኑን እናሳውቃለን።

ዕውቀት ለልህቀት
https://www.facebook.com/wru.edu.et

16/01/2025
11/01/2025

ማስታወቂያ

በሪሚዲያል ፕሮግራም ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባቹ ተማሪዎች በሙሉ

በ2017 ትምህርት ዘመን ከት/ት ሚኒስቴር በሪሚዲያል ፕሮግራም ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባቹ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ጥር 21-22/2017 መሆኑን እያሳወቅን ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ:-

☞ ከ8ኛ-12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት ማስረጃዎችን ኦርጅናልና አንድ የማይመለስ ኮፒ

☞ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ካርድ፤

- 3 በ 4 የሆነ 4 ጉርድ ፎቶ

☞ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ልብስ፣ የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይኖርባቸዋል

ማሳሰቢያ

➢ ከላይ ከተገለጹት ቀናት ቀድሞም ይሁን ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

Photos from Werabe University Museyd and Abdulselam counselors's post 21/10/2024

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከስር በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ እንድትወዳደሩ የተጋበዛችሁ ሲሆን የመመዝገቢያ ጊዜ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ከቀን 11/2/2017 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስር የስራ ቀናት ይሆናል፡፡ አመልካቾች ሙሉ የህይወት ታሪካቸውን (CV) እና ሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ዋናውንና የማይመለስ ኮፒ በመያዝ በዩኒቨርሲቲው ሰው ሀብት አስተዳዳርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 03 መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

Photos from Werabe University Museyd and Abdulselam counselors's post 10/10/2024

የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልፀ!

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

14/09/2024

ማስታወቂያ

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Silte
Addis Ababa