24/04/2026
ትናንት በእግሩ፣ ዛሬ በብሩ የሀገርን ገጽታ ግንባታ በትከሻው የተሸከመው ኃይለኛው ኃይሌ
ብዙ ጊዜ ሺአለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ እንደርእስ አድርጎ መጻፍ እፈልግና ግን ያቅተኛል። እንጃ ቃላትን ይዘላል።
ለእኔ "ኢትዮጵያውያን ዓለምን ረስተው፣ ዓለምም እነሱን ረስቶ ለሺህ ዓመታት ኖሩ(ተኙ)" ያለውን የታዋቂው እንግሊዛዊ የታሪክ ተመራማሪ ኤድዋርድ ጊበን(Edward Gibbon) አባባል/መርገም ከቀየሩ አንዱና ዋናው አድርጌ ነው የምቆጥረው።
የሩጫው ድል አንድ ነገር ነው፤ በየተረሱ አካባቢዎች እየሄደ በብሩ የሚሠራቸው ሪዞርቶች ለእኔ ውድ የኦሎምፒክ ሜዳሊያዎች ናቸው።
ከዚያ ደግሞ የሆቴል አገለግሎት ልሕቀትን የት እንዳደረሰው ኹለት ቀን በአንዱ ሆቴሉ ቆይቶ መውጣት በቂ ነው። የአያት ቤት እንጂ የሆቴል አገልግሎት ለማለት ይከብዳል።
ደ/ብርሃንን ከአጼ ዘርዓያእቆብ ቀጥለህ #አበራህላት!
(ታችኛውንና መካከለኛ ገቢ ደግሞ እንዲያማክል ቢደረግ)
*****
Disclaimer
የጊበን አባባል ላይ በተቃውሞ ጎራ የሚተቹና አውሮፓዊ ማግለል ነው የሚሉ አሉ።
ዘመነ መሣፍንት የተባለውን በድፕሎማሲ መነጠልና በውስጥ ቁርቁስ በተለይ ከአውሮፓውያን አንጻር የተነገረ መሆኑን ልብ ይሏል። በኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍም የጨለማ ዘመን/Dark age" የሚባለው ከ7ኛው -16ኛው መ.ክ.ዘ ያለውን ጊዜ ነው። በአንጻሩ ኢትዮጵያውያን በዚኽ የማይስማሙ አሉ። ኢትዮጵያ በባህል፣ በሥነጽሑፍና በኪነጥበብና በሃይማኖታዊ(ክርስትናውም እስልምናውም) በኩል ያበበችበት ጊዜ ነውና። እነ ቅዱስ ላሊበላ በኪነሕንጻ፣ እነአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሥነጽሑፍና ሌሎችም ባህል ወግ ሃይማኖታዊ እሴችና ባህሎች ያበቡበት ጊዜ ነው። ብቻውን ብዙ ጥራዝ ያለው መጽሐፍ ስለሚወጣው ወደመጽሐፍት ግቡ። ለጊዜው አምሮት ማስታገሻ ቅንጭብ ንባብ እነኾ።
https://www.ethiopianreview.com/index/329