28/05/2026
📢 ፦ በአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም የመምህራን ዝውውር የት ደረሰ?
ለእረጅም ጊዜ ተቋርጦ የነበረውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአማራ ክልል የዞን ዞን እና የክልል-ክልል መምህራን ዝውውር ሥራ በአሁኑ ወቅት በይፋ ተጀምሮ በሂደት ላይ ይገኛል።
ብዙ መምህራን "ውጤቱ ተለቋል ወይ?" በማለት እየጠየቁ ቢሆንም፣ በክልሉ ትምህርት ቢሮ ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አጠቃላይ ውጤቱ ለተጠቃሚዎች የሚደርሰው በሚቀጥሉት ቀናት ይሆናል።
📅 የወቅቱ የዝውውር አፈጻጸም የጊዜ ሰሌዳ፦
🔹 እስከ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም፦ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የዞን ዞን እና የክልል-ክልል ዝውውር ውጤትን ለዞን መምህራን ልማት ቡድን ያሳውቃል።
🔹 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም፦ የዞን መምህራን ልማት ቡድን መረጃውን አጠቃሎ ለየወረዳዎቹ ያስተላልፋል።
🔹 እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፦ የወረዳ መምህራን ልማት ቡድኖች ውጤቱን በትምህርት ቤት እና በጉድኝት ደረጃ ለመምህራን በይፋ ያደርሳሉ።
🔹 እስከ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም፦ ዝውውር ለተፈቀደላቸው መምህራን የክሊራንስ እና የመሸኛ ሥራዎች ይከናወናሉ።
💡 ማወቅ ያለብዎት ዋና ዋና ነጥቦች፦
1. ዘንድሮ ዝውውሩ የተሠራው ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ በወጣው አዲሱ መመሪያ ቁጥር 19/2018 መሠረት ነው።
2. አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት (Curriculum) ያስከተለውን የትምህርት ዓይነቶች መታጠፍ ያገናዘበ አሠራር ተዘርግቷል።
3. መምህራን ከግንቦት ማብቂያ ጀምሮ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ ከየወረዳችሁ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ወይም ከትምህርት ቤታችሁ መረጃውን መከታተል ትችላላችሁ።
------------------------------
📌 ይህንን ፔጅና ቻናል ይቀላቀሉ 👇
05/05/2026
15/12/2025
14/12/2025