አሁናዊ መረጃ

አሁናዊ መረጃ

Share

ታማኝ፣ ትክክለኛና አዳዲስ ክስተትና መረጃዎች በሰዓታቸው።

A Region Under Redemption: The 2026 Somali Region Election | The Reporter Ethiopia 16/05/2026

“ሶማሊ ክልል በታሪኩ ምርጡን የሰላምና እድገት አመታት እያሳለፈ ነው..”

👉 ከኢትዮ ኦብሰርቨር የተገኘ

በሶማሊ ክልል በዴሞክራሲ ሰላምና መልካም አስተዳደር ላይ የሚሰራው የካራማራ ግሩፕ ተወካይ የሆኑት አሊ አብዲ “A Region under Redemption: The 2026 Somali Region Election” በሚል ርእስ ዛሬ ለህመት በበቃው ዘሪፖርተር ላይ ባጋሩት ፁሁፍ በአንድ ወቅት የድህነት እና ግጭት ምሳሌ የነበረው ሶማሊ ክልል በሚያስደንቅ ለውጥ ላይ ነው ፤ በኢትዮጵያም የሰላም፣ ልማት እና ብልፅግና ምልክት እየሆነ መጥቷል…” ሲሉ አትተዋል፡፡

አሊ በተለይም የአዲሱን ዘመን እድገት፣ አካታችነት እና ተቋማዊ ግንባታ ከተመለከትን ያለፉት ስምንት አመታት ሶማሊ ክልል በታሪኩ ሰላማዊ የተባለውን ጊዜ እያሳለፈ የሚገኝበት ነው ሲሉ ይገልፁታል፡፡

አስተማማኝ የልማት ፕሮጀክቶች፣ ዘላቂ መረጋጋት እና የፖለቲካ አካታችነትን በተግባር ያረጋገጠው የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ እና አመራሩ እነዚህ ማሳያዎች ለአዲስ የስልጣን ዘመን እንደገና ተመራጭ ለመሆን መሰረት ናቸው ብሎ ያምናል፡፡

በዚህ ክልል ተወልደው ላደጉ ሁሉ ያለፉት አስር አመታት ወሳኝ የታሪክ መታጠፊያ የሆነ ያክል ይሰማናል ያሉት ፀሀፊው - በአንድ ወቅት በግጭት እና ተገማች አለመሆን፣ ሲመሽ የሚዘጉ ከተሞችና ገበያዎች፣ ለጉዞ አደገኛ የሆኑ መንገዶች እና ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ቤተሰቦች ያመነቱ የነበሩበት ጊዜያት አሁን የሩቅ ትዝታ ይመስላሉ ሲሉም ነው ያስታወሱት።

ሆኖም ይላሉ ፀሀፊው ፣ ሆኖም ይህ ለውጥ በአንድ ጀምበር አልመጣም፡፡ ይህ ለውጥ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በመሩት እና የቀድሞውን ገዥ ፓርቲ ኢህአዴግ ከስልጣን መስወገድን የጠየቀ የፖለቲካ ለውጥም ጭምር የተመዘገበበት ያ ደግሞ በሶማሊ ክልል ለአዲስ የአመራር ሀይል በር የከፈተበት ነው ሲሉ አክለዋል፡፡

ያ የለውጥ ጅማሮ የቀድሞውን የክልሉ ፕሬዘዳንት አብዲ ሞሀመድ ኦማር (አብዲ ኢሌ) ከስልጣን ያስወገደ በምትኩም አቶ ሙስጠፋ መሀመድን ጊዜያዊ ፕሬዘዳንት በኋላም ፕሬዘዳንት እንደሆኑ መንገድ የጠረገ አጋጣሚ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱት👇🏽

A Region Under Redemption: The 2026 Somali Region Election | The Reporter Ethiopia A region once mired in prolonged conflict and underdevelopment has undergone significant transformation, emerging as a symbol of peace, development, and

10/05/2026

መልካም የእናቶች ቀን!

Happy mother's day

አሁናዊ መረጃ
ቴሌግራም
https://t.me/AhunawiMereja
゚viralシfypシ゚viralシ

Photos from አሁናዊ መረጃ's post 30/04/2026

🚨 በልደት ክብረ በዓሉ ላይ ፊቴን ለምን ኬክ ቀባችሁኝ ያለው ባለልደት ጓደኞቹን ገደለ።

ጂቱ የተባለው የ33 አመት ህንዳዊ ከጓደኞቹ ጋር ልደቱን እያከበረ ነበር። ኬኩ በቀረበ ጊዜ አንዳንዶቹ ጓደኞቹ ለቀልድ ያህል ፊቱ ላይ ኬክ የቀቡት ቢሆንም፣ ድርጊቱ በልደቱ ባለቤት ዘንድ ያልተጠበቀ ቁጣን አስከትሏል።

በዚህ ሰበብ ከጓደኞቹ ጋር ከፍተኛ ጭቅጭቅ ውስጥ የገባው ወጣቱ ፕሮግራሙ ጥሎ በመሄድ፣ ሌሎች ሰዎችን ጨምሮ እና ፈቃድ ያለው ሽጉጥ ይዞ ተመልሶ በመምጣት ሶስቱንም ጓደኞቹን ተኩሶ እንደገደላቸው ኦዲቲ ሴንትራል ፅፏል።

የኩርጃ ናጋር ፖሊስ ጣቢያ ወጣቶቹ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም፣ እዚያ ሲደርሱ ህይወታቸው ማለፉ ተረጋግጧል ብሏል።

ለድርጊቱ እንደ ምክንያት የተጠቀሰው የአንዱ ተከሳሽ ልደት የነበረ ሲሆን፣ ሟቾቹ ፊቱ ላይ ኬክ በመቀባታቸው የተነሳ በተፈጠረ ጠብ ነው” ሲል አረጋግጧል።

ለጥያቄ እንዲረዱ ከ15 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ቢሆንም፣ ዋናው ተጠርጣሪ ጂቱ ሳይኒ ግን በፖሊስ አለመያዙን ዘገባው ጠቁሟል።

አሁናዊ መረጃ

ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ 👇

https://t.me/AhunawiMereja
゚viralシfypシ゚viralシ

24/04/2026

🎯 አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ በከፍተኛ ህመም ውስጥ ይገኛል ተባለ።

በህገ-ወጥ የፊንቴክ (Fintech) ኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ ከሚገኙት ታዋቂ አርቲስቶች መካከል፣ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ በከፍተኛ ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል እያደረገ መሆኑ ተሰማ። አርቲስቱ ቀደም ሲል በነበረበት የስኳር እና የደም ግፊት ህመም አሁን ላይ ጸንቶበት ለመቆጣጠር በመቸገሩ ምክንያት፣ አብዛኛውን የእስር ጊዜውን በፖሊስ ሆስፒታል ህክምናውን በመከታተል እያሳለፈ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

አሁናዊ መረጃ

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/AhunawiMereja

゚viralシfypシ゚viralシ

Photos from አሁናዊ መረጃ's post 18/04/2026

🎯 ለጉብኝት ወደ አዲስ አበባ የመጡ የሳውዲ አረቢያ ዜጎችን "ሿሿ" የሰራው የታክሲ ሹፌር በቁጥጥር ስር ዋለ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዳስታወቀው፤
ተጠርጣሪው ወንጀሉን የፈፀመው ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።

በዕለቱም፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ በመምሰል በተከራየው ተሽከርካሪ ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ወደ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሦስት በተለምዶ መስቀል ፍላዋር ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ለማድረስ ተስማምቶ በቦታው እንደደረሰ ቅድሚያ እናንተ ውረዱ ብሏቸው ልክ እንደወረዱ በፍጥነት ተሽከርካሪውን በማስነሳት ሻንጣዎቻቸውንና ሌሎች ቁሳቁሶቻቸውን ይዞ ማምለጡን ፖሊስ ገልጿል ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥርና አደጋ ምርመራ መምሪያ አመራር እና አባላት መረጃው እንደደረሳቸው ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ባደረጉት ጠንካራ ክትትል ዛሬ ሚያዚያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከቦሌ ድልድይ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ በሚያስገባው አደባባይ ከነተሽከርካሪው በቁጥጥር ሥር አውሎታል።

በዚህም የወንጀል ምርመራው እንዲጣራበት ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ላንቻ ፖሊስ ጣቢያ አስረክበዋል።

ፖሊስ በወቅቱ የተዘረፋ ሻንጣዎችና ሌሎች ቁሳቁሶችን ለተጎጂዎቹ ለማስመለስ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እያደረገ እንደሚገኝም ገልጿል።

© የፌዴራል ፖሊስ

አሁናዊ መረጃ
ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ👇
https://t.me/AhunawiMereja

゚viralシfypシ゚viralシ

18/04/2026

🎯 ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከአሜሪካ የተባረሩ 15 ደቡብ አሜሪካውያን ስደተኞችን ተቀበለች።

በዋሺንግተን ዲሲ እና በኪንሻሳ መካከል በተደረሰው ስደተኞችን የመቀበል ስምምነት መሰረት የመጀመሪያዎቹ 15 ተመላሾች ኪንሻሳ ደርሰዋል።

በዚህ በመጀመሪያው ቡድን ውስጥ 7 ሴቶች የሚገኙ ሲሆን የፔሩ እና የኢኳዶር ዜጎች መሆናቸውን አናዱሉ ዘግቧል።

አሜሪካ የሚያስፈልጉትን ወጪዎች በሙሉ የምትሸፍን ሲሆን በኪንሻሳ አቅራቢያ ማቆያ ቦታዎችም እንደተዘጋጀላቸው ተገልጿል።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከ30 በላይ ተመላሾች በዚህ ሳምንት ወደ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ይደርሳሉ።

አሁናዊ መረጃ

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇
https://t.me/AhunawiMereja

゚viralシfypシ゚viralシ

18/04/2026

🎯 ኢራን ሆርሙዝን ከፈትኩ ባለች በሰዓታት ውስጥ ዳግም ዘጋችው።

ኢራን በከፈተችበት ቅፅበት የተወሰኑ የጭነት መርከቦች ሰርጡን አቋርጠው አልፈው የነበር ቢሆንም ወዲያውን ግን ዳግም ተዘግቷል።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ በሰጠው መረጃ አሁን ላይ ሆርሙዝ በቀደመ መዘጋቱ ላይ እንዲሆን ተደርጓል።

አሁናዊ መረጃ

ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ 👇
https://t.me/AhunawiMereja

16/04/2026

👉 የአልበሙ መታሰቢያነት

ቴዲ አፍሮ ዛሬ የለቀቀውን "ኢቶሪካ" አልበም መታሰቢያ ይሁንልኝ ያለውን ይፋ አድርጓል።

ድምፃዊው ይህንን አዲስ ስራውን በሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት በማንነታቸው ምክንያት ጥቃት ለደረሰባቸው እና ለተፈናቀሉ ንጹሀን ኢትዮጵያውያን መታሰቢያ እንዲሆን ማበርከቱን አስታውቋል።

ቴዲ አፍሮ ከአዲሱ አልበሙ ሽፋን ጋር ባጋራው ይፋዊ መልዕክት ላይ እንዳሰፈረው፤ "ይህ ሙዚቃ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በማንነታቸው ብቻ ተለይተው በግፍ ለተገደሉ ንፁሀን ወገኖቻችን እና እንዲሁም ከቀያቸው ለተፈናቀሉ የአካል እና የስነ-ልቦና ጉዳት ለደረሰባቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በሙሉ መታሰቢያ ይሁንልኝ" በማለት አጋርነቱን ገልጿል።

አሁናዊ መረጃ

ቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇

https://t.me/AhunawiMereja

゚viralシfypシ゚viralシ

15/04/2026

🎯 ኢትዮጵያ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ በቅርቡ ታስመርቃለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከEBC ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገራችን እስካሁን ጥሬ ወርቅን ወደ ውጭ በመላክ ላይ ብቻ ተወስና መቆየቷን በማስታወስ፣ አሁን እየተገነባ ያለው ፋብሪካ በዘርፉ ያለውን የእሴት መጨመር ችግር እንደሚቀርፈው አብራርተዋል።

ግንባታው እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ተጠናቆ ለምረቃ እንደሚበቃ ይጠበቃል።

ይህ ፋብሪካ፣ በሀገር ውስጥ እና በአካባቢው የሚመረተውን ወርቅ እሴት ታክሎበት በተሻለ ዋጋ ለገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

አሁናዊ መረጃ

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
https://t.me/AhunawiMereja

゚viralシfypシ゚viralシ

12/04/2026

🎙 ተወዳጁ ቴጂ አፍሮ ምን አለ?

"የአክብሮት ሰላምታዬን በማስቀደም ቀጣዩ ‘ኢቶሪካ’ የተሰኘው አዲስ አልበም የፊታችን ሐሙስ ሚያዝያ 8/2018 በTeddy Afro Official Youtube ድህረገፅ (www.youtube.com/TeddyAfroOfficial) ከቀኑ በ8 ሰዓት ወደ እናንተ እንደሚደርስ በአክብሮት እገልጻለሁ"።

ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
አሁናዊ መረጃ
የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇

https://t.me/AhunawiMereja

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Addis Ababa