Zena tube

Zena tube

Share

Jireenya Dhugaa Ortodoksumma Kootaa Baradha.

07/10/2025

① ባልሽን በቁልምጫ ጥሪው።

② በቤተሰቡ ውስጥ መሪ እንዲሆን ፍቀጂለት።

③ እሱ ከተበሳጨ ወይም ከተናደደ አትከራከሪ።

④ እሱ ሲቆጣ ዝም በይና በኋላ ይቅርታ ለመጠየቅ ተነጋገሪ።

⑤ አንቺ እሱን ካስከፋሽው ወዲያውኑ "ይቅር በለኝ ፍቅሬ" በይው፤ ይቅር ሲልሽ ደግሞ አመስግኚው።

⑥ በሌሎች ሰዎች ፊት ስለ እሱ ጥሩ ነገሮችን ተናገሪ።

⑦ እናቱን አክብሪ።

⑧ ለወላጆቹ ስጦታ እንዲገዛ አበረታቺው፤ ይህን ማድረጉ ላንቺም ተመሳሳይ ነገር እንዲያደርግ ያነሳሳዋል።

⑨ በተለይ ገንዘብ ሲያጥረው የሚወደውን ምግብ ሰርተሽ አስደንቂው/ሰርፕራይዝ አድርጊው።

⑩ አንቺ እቤት እያለሽ ለባልሽ ምግብ በሰራተኛ እንዳታቀርቢ፤ ራስሽ አቅርቢለት።

⑪ ከውጭ ሲመጣ በእቅፍ ተቀበዪው፤ ቦርሳዎቹንና ልብሶቹን እንዲያወልቅ እርጂው።

⑫ አብራችሁ ውጪ ስትሆኑ ፈገግ በይለትና ፍቅርን ስጪው።
⑬ በልጆቻችሁ ፊት አመስግኚው።

⑭ ሻወር ሲወስድ ጀርባውን እጠቢለት።

⑮ በምሳ ዕቃው ወይም በቦርሳው ውስጥ የፍቅር መልዕክት አስቀምጪለት።

⑩ እንደናፈቅሽው ለመንገር ብቻ ደውዪለት።

⑰ ስልክ ሲያነሳ "እወድሃለሁ" በይው።

⑱ ጠዋት ላይ ለአንድ አስፈላጊ ነገር ቀስ ብለሽ ቀስቅሺው፤ ፍቅር እንዲሰማው አድርጊ።

⑲ እሱን ባል በማድረግሽ እድለኛ እንደሆንሽ ንገሪው።

⑳ ያለምንም ምክንያት እቀፊው።

㉑ በሕይወትሽ እሱን ስለሰጠሽ ፈጣሪን አመስግኚ።

㉒ ሁልጊዜ ጸልይለት።

㉓ በተለይ ከመተኛታችሁ በፊት አብራችሁ ጸልዩ።

Telegram: Contact @Mindoforthodoxy

29/09/2025

ለዓመታት የሰራችበትን ገንዘብ ተከልክላና ታግታ የነበረችው ኢትዮጵያዊት ፍትህ አገኘች

ከ5 ዓመታት በላይ የሰራችበትን ደሞዝ ተከልክላ እና ታግታ የነበረች ኢትዮጵያዊት ቆንስላ ጽ/ቤቱ ባደረው ጥረት ከእገታ በማስለቀቅ ደሞዟ እንዲከፈላት መደረጉ በጅዳ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት አስታወቀ።

ወ/ሪት ራዲ ሁሴን ኢብራሂም የተባለች ኢትዮጵያዊት በህጋዊ መንገድ ለስራ ሳኡዲ አረቢያ ከመጣች በኋላ ላለፉት አስራ አራት (14) ዓመታት በጧኢፍ ከተማ በአሰሪዎቿ በመታገቷና የሰራችበትን ደመወዝ ተከልክላ ነበር።

የቆንስላ ጽ/ቤቱ መረጃ እንደደረስው ዲፕሎማቶችን ወደ ስፍራው በመላክ ከታገተችበት በማስለቀቅ የሰራችበትን የ5 ዓመት ቀሪ ደመወዝ ስልሳ ሺህ የሳኡዲ ሪያል እንዲከፈላት አድርጓል።

በቀጣይም ፓስፖርቷ እንዲታደስ በማድረግ እንዲሁም ኢቃማዋን በማስተካከል ወደ ሀገሯ የምትመለስበትን ሁኔታ በማመቻቸት ላይ እንደሚገኝም ነው ጽ/ቤቱ ያስታወቀው።

ወ/ሪት ራዲ በቆንስላ ጽ/ቤቱ ላደረገላት ድጋፍ ምስጋና አቅርባለች።

ጽ/ቤቱ የዜጎችን መብት እና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚያከናውናቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል በማህበራዊ የትስስር ገፁ አስታውቋል።

‌‎

29/09/2025

ታዳጊዎች ለሴተኛ አዳሪነት መጋለጣቸውን
በአማራ ክልል ውጊያ ባለባቸው አካባቢዎች ታዳጊዎች ለሴተኛ አዳሪነት መጋለጣቸውን ጥናት አመላከተ

በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት ዓመታት ውጊያ ባለባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው፣ ዕድሜያቸው ለጋብቻ ያልደረሱ ታዳጊዎች ወደ አዲስ አበባና ወደ ሌሎች የክልል ከተሞች በመሄድ በሴተኛ አዳሪነት እንደሚሰማሩ፣ ጀንደር ኤንድ አዶለስንስ ግሎባል ኤቪደንስ (Gender and Adolescence Global Evidence) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የጥናት ቡድን አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ጥናት አማራ ክልልን ጨምሮ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በሶማሌና በአፋር ክልሎች ግጭትና ድርቅ ባሉባቸው አካባቢዎች በሚኖሩ 20 ሺሕ ሴቶች ላይ የተደረገ መሆኑንና የልጅነት ጋብቻን ጨምሮ ፆታዊ ጥቃት በከፍተኛ መጠን እንደጨመረ መረጋገጡ ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ የሴቶችን ማኅበራዊ ቅንጅት ‹‹ትመራለች›› በሚል መሪ ቃል ላለፉት አምስት ዓመታት በወጣት ሴቶች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ሲሠራ የነበረው ፕሮጀክት የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ ጥናቱን ያቀረቡት፣ የምርምር ተቋሙ የኢትዮጵያ ተወካይ ወርቅነህ አበበ (ዶ/ር) ናቸው፡፡

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን አምስት ወረዳዎች ውስጥ ካሉ 67 ቀበሌዎች ናሙና መወሰዱን የተናገሩት ወርቅነህ (ዶ/ር)፣ በቀበሌዎቹ ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተዘግተው መቆየታቸውንና ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ ለመሆን መገደዳቸውን ገልፀዋል።
via_reporter

29/09/2025

ሩስያ 100% ካንሰር የሚያድን ክትባት ይፋ አደረገች!!

ሩሲያ በመጀመሪያዎቹ ክሊኒካዊ ሙከራዎች 100% ስኬትን ባሳየው የኢንትሮሚክስ(Enteromix) ካንሰር ክትባት እጅግ አስደናቂ የሆነ የህክምና ስኬት አሳይታለች።

ይህ የሙከራ ክትባት በሽታ የመከላከል ስርዓትን የካንሰር ሴሎችን እንዲያውቅ እና እንዲያጠፋ ለማሰልጠን ያለመ ሲሆን ይህም የሰው ልጅ ገዳይ ከሆኑት በሽታዎች አንዱን ለመዋጋት አዲስ ተስፋ ይሰጣል ተብሎለታል።

ገና በመጀመርያ ደረጃዎች ላይ ውጤቶቹ በካንሰር ጥናት ውስጥ እንደ ታሪካዊ ተደርገው ይወሰዳሉ, ይህም ዓለም አቀፍ ትኩረትን እና ክርክርን አስነስቷል።

ተጨማሪ ሙከራዎች እነዚህን ግኝቶች ካረጋገጡ, ኢንተርሚክስ (Enteromix) የወደፊቱን የካንሰር ህክምናን በማስተካከል በዓለም ላይ የመጀመሪያው ውጤታማ የካንሰር ክትባት ሊሆን ይችላል ተብሏል።

ሩሲያ በባዮቴክኖሎጂ እና በሕክምና ፈጠራ ላይ ብዙ ኢንቨስት አድርጋለች ፣ ይህም እራሱን በሚቀጥለው ትውልድ የጤና አጠባበቅ መፍትሄዎች ውስጥ እንደ መሪ ለማስቀመጥ በማሰብ ነው።

ይህ ክትባት ሳይንሳዊ ደረጃን ብቻ ሳይሆን በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ታካሚዎች ትልቅ ለውጥ ያመጣል።
ይህ የሰው ልጅ ሲጠብቀው ከነበረው ግኝቶች አንዱ ሊሆን ይችላል ተብሏል።

Photos from Zena tube's post 29/09/2025

የአውሮፓ ህብረት አመነ‼️

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የኮቪድ ክትባት ትክክለኛ የጤና ቁጥጥር ሂደቶችን ሳያሟላ መፅደቁንና መሰራጨቱን በይፋ አረጋግጧል።

የኮቪድ ክትባት በወሰዱ ሰዎች ላይ በተደረገ ጥናት የልብ፣ የአንጎል እና የደም መርጋትን አደጋ መጨመሩን በቅርብ ጊዜ የወጣ ጥናት አረጋግጧል።

ከስምንት ሀገራት የተውጣጡ ወደ 99 ሚሊዮን የሚጠጉ በተከተቡ ሰዎች ላይ በተደረገ አንድ ትልቅ አዲስ ጥናት Pfizer ወይም Moderna mRNA ክትባቶችን ወስደው አስትራ ዜኔካ ጃብን ከወሰዱ በኋላ የልብ ችግርን የመጨመር ግንኙነት እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል።

የመጀመሪያዎቹን ሁለት ክትባቶች በወሰደ ሰው ላይ የልብ ስጋት መጨመር በአንጻራዊ ሁኔታ ቀላል ቢሆንም፣ Astra Zeneca jab የተባለውን ክትባት ከወሰዱ በኋላ ግን በአማካይ በተፈጥሮ ከተከሰቱት የልብ ነርቭ በሽታዎች ቁጥር በሦስት እጥፍ እንደጨመረ ጥናቱ አረጋግጧል

Photos from Zena tube's post 11/10/2024

✔ ልጅ ወደ አባቱ ይሄዳል አባትም ወደልጁ ይሄዳል!!
✔ አባት ልጁን ይወልዳል ልጅም አባቱን ይወልዳል !!
✔ ልጅ ያለው አባት አለው አባት ያለውም ልጅ አለው !!
✔ ልጅ በአባቱ ይከብራል አባትም በልጁ ይከብራል !!
✔ አባት በልጁ ነጻ ይወጣል ልጅም በአባቱ ነጻ ይወጣል !!
✔ ልጅ በአባቱ ያጌጣል አባትም በልጁ ያጌጣል !!
✔ ልጅ የሌለው አባት አይባልም አባት የሌለውም
ልጅ አይባልም !!
✔ የአባት ዘሩ ልጅ ነው የልጅ ዘሩም አባት ነው !!
✔ አባት ለልጁ በረከት ነው ልጅም ለአባቱ በረከት
ነው !!
✔ አባት የልጁን ይወርሳል ልጅም የአባቱን ይወርሳል ።

በዚህ በችግር ወቅት አንዱም ወደ አንዱ በማይንቀሳቀስበት ወቅት
ሀገራችንም ሁለንተናዊ ችግር ውስጥ በገባችበት ዘመን የመጀመሪያ የሚጎዱ ጉባኤ ቤቶች ናቸው ።

እንደሚታወቀው ቤተክርሰቲያን የምትተነፍሰውና ሕያዊት ሆና የምትኖረው በጉባኤ ቤት ነው ።
ጉባኤ ቤት ከሌለ❖ ጵጵስናውም ❖ ምንኵስናውም ብሕትውናውም ❖ ምርጊትናውም ❖ ቅስናውም ሰባኪነቱም ❖ ዲቁናውም ❖ ክርስትናውም ❖ በጠቅላላው ምንም ነገር የሁሉም ነገር ምንጭ ቤተጉባኤ ናት ፨
ግን እንዳለመታደል ሆኖ ከላይኛው መዋቅር ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ጉባኤ ቤቶች ይኑሩ አይኑሩ የሚያውቃቸው የለም ።
በጀትም የለም ። ድጋፍም የለም ። መምሪያም የለውም ።

በዚህ ዘመን የደቀመዛሙርቱን አዕምሮውን የሚቀልቡት መምህራን ናቸው።
ሆዱንም የሚሞሉት ከበጎ አድራጊዎች ምዕመናን ጋራ በመናበብ መምህራን ናቸው ።

ከእነዚህም መምህራን አንዱ የኔታ ገብረ መድኅን ናቸው ።
አሁንም ከአለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ብዙ ነገሮች ምቹ አደሉምና በቅርብ ቀን ያሳተሙትን ከመዝ ነአምን የተሰኘ መጽሐፋቸውን ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት አሳትሞ እንዲጠቀመው አበርክተዋል ።
መጽሐፉም ወደማተሚያ ቤት ገብቶ ዛሬ ጥቅምት ሠላሳ ታትሞ ወጥቷል ከነገ ጀምሮ በጉባኤ ቤቱ አከፋፋይነት በሁሉም ከተማዎች ተደራሽ ይሆናል
ስለዚህም ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሁም ይህንን መጽሐፍ በመግዛት ጉባኤ ቤታችሁን አግዙ ።

ጉባኤ ቤትን መርዳት እራስን መርዳት ነውና
ጉባኤ ቤትን ማገዝ እራስን ማገዝ ነውና
ጉባኤ ቤትን መጠበቅ ሀገርን መጠበቅ ነውና
ጉባኤ ቤትን መደገፍ ወላጅ አባትን መደገፍ ነውና

ጉባኤ ቤት
ጤናማ ጳጳስን
ጤናማ መነኵሴን
ጤናማ ካህንን (የነፍስ አባት)
ጤናማ ዲያቆንን
ጤናማ ሰባኪን
ጤናማ አገልጋይን የምታመርት ሐዋርያዊት እርሻ ናት ።

31/08/2024

ሕሊና- ሕሊና መንፈሳዊ የሀሳብ ሚዛን ነው። ይህም አምላካችን እግዚአብሔር የሰው ልጅ ከሕጉ እና ከመንገዱ እንዳይርቅ የሚጠበቅበት ውሳጣዊ ዳኛ ነው። ልብ ያመላለሰውን ኩላሊት ያጤሰውን በእውነተኛ ሚዛን መዝኖ ክፉ ነው በጎ ነው የሚለውን ብያኔ ይሰጣል። አእምሮ ጠባያዊ የሚባለው ይህ ነው። ጥንቱን አዳም ሲፈጠር በሕሊና ሁሉ ነገር ተስሎለት ነው ልደተ ተፈጥሮን ያገኘው። በዚህ ሚዛናዊ ሕሊና አመዛዝኖ በሰራው ሥራ ወይ ይኮነናል ወይ ይጸድቃል። መክኒያቱም ሰው በተሰጠው ነጻነት በሕሊና አዋቂነት አውቆ ተረድቶ ሁሉን ሰለሚሰራ። ሀጥያት ቢሰራ እግዚአብሔር ሳይፈርድበት ሕሊናው ይፈርድበታል። በጎ ቢሰራ እግዚአብሔር ሳይፈርድለት እግዚአብሔራዊ ዳኛ ሕሊና ይፈርድለታል። ይህም የሰው ልጅ ክፉ በሰራ ቀን ሰላም ያጣል ልቡ ይታወካል አእምሮው ይጨነቃል ሰውነቱ ሁሉ ይቆጣል። በጎ ባደረገ ጊዜ ደግሞ ከፊቱ ገጽታ ጀምሮ እሰከ ልቡ ከልቡ እስከ አእምሮ ያለው ሰውነቱ ብሩ ገጽን የተሞላ ይሆናል። ሕሊና ያለ እረፍት ያመሰግነዋል። እንዲህ ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በጎ ጸሎት ጸልዮ የልቡን መሻት ያገኛል። ይቆየን
S.T 25/12/2016

Telegram: Contact @gedamate 20/08/2024

ልብ አእምሮ እና ሕሊና ቢስማሙ ሰው ሁሉ የተማላ ስብእና ባልቤት ይሆናል። እነዚህ ነገሮች ግን እርስ በርስ የሚጋጩ ከሆነ ከእራስ ሰላም ማጣት ጀምሮ እሰከ ቤተስብ ከዛም አልፎ ለሀገር የሚተርፍ ሁከትን ይፈጥራል። እነዚህ ነገሮች ደገም የሚገኙት ጸጥ ባለ ቦታ ከሁከት ርቆ ከእራስ ጋር በማውራት እና በመምከር ነው። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ በእግዚአብሔር ቃል እራስ መገንባት መስማት ብቻ ሳይሆን በማዳመጥ ይገኛል።...

Telegram: Contact @gedamate

02/08/2024

የኔታ መዝገበቃል
ህጻናት ላይ የምትሰራ ሃገር ራሷን ትገነባለች ህጻናት ላይ የማትሰራ ሃገር ራሷን ታፈርሳለች" መምህር መዝገበ ቃል /የወለህ ነቅዓ ሒወት የአራቱ ጉባኤ ቤት መምህር

ሰቆጣ፣ ሐምሌ 23/2016 ዓ.ም (sekota ketema communication) በዋግ ኽምራ ሃገረ ስብከት የወለህ ነቅዓ ሒወት የአራቱ ጉባኤ ቤት ከሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በዋግ ስዩም አድማሱ ወሰን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ።

የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ሲወስዱ ተገኝተን ካነጋገርናቸው ተማሪዎች መካካል የ8ኛ ክፍል ተማሪ ታምር ግርማ የወለህ ነቅዓ ሒወት ጉባኤ ቤት በሂሳብና በእንግዘኛ የትምህርት አይነቶች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱ ጊዜየን በአልባሌ ቦታ እንዳላሳልፍ ከማድረግ ባለፈ ቀጣይ ዓመት በክልል ደረጃ ለሚሰጠው የሚኒስትሪ ፈተና እንድንዘጋጅ ያግዘናል ብላለች፡፡

ሌላው የአምስተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ተማሪ ተዋሕዶ ሃይማኖት ከአለማዊ ትምህርት ጎን ለጎን መንፈሳዊ ትምህርቶችን እንድንማር ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ የቤተ-ክርስቲያኗን እውቀት እንድንቀስምና በሥነ-ምግባር ታንፀን ከአሰብነው አላማ እንድንደርስ ይረዳናል ብሏል፡፡

በተለይም ክርስቲያናዊ ስነ ምግባር መማራችን መልካም ያልሆኑ ስነ ምግባሮችን አስወግደን መልካም ስነ ምግባር እንድንላበስና በአለማዊ ትምህርታችንም ጠንክር እንድንማር አግዞናል ሲሉ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የሚወስዱ ተማሪዎች ተናግረዋል፡፡

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠ የሚገኘው የ4ኛ አመት የዩኒቨርስቲ ተማሪ የሆነው መምህር ያሬድ ጣምተው ህፃናት ነገን አውቀው ዛሬ ላይ በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠሁ ነው በማለት ገልጿል፡፡

‹‹በጎነት ለራሱ ነው› ያለው መምህር ያሬድ የማጠናከሪያ ትምህርት ከመስጠት ባሻገር 6ኛና ለ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና የሚያዘጋጁ ጥያቄዎችንም በመሥራት የበኩሌን አሻራ እያሳረፍ ነው ብሏል፡፡

በዋግ ኽምራ ሃገረ ስብከት የወለህ ነቅዓ ሒወት የአራቱ ጉባኤ ቤት መምህር የሆኑት መምህር መዝገበቃል ገ/ሕይዎት ጉባኤ ቤቱ የቤተ-ክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የሚያስጠብቁ ደቀ መዛሙርትን ከማፍራት ባሻገር ከሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የክፍል ደረጃቸው ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ለሆኑ ተማሪዎች የክረምት የማጠናከሪያ እየሰጠን ሲሆን አላማውም የነገ ሃገር ተረካቢ የሆኑ ህጻናት አልባሌ ቦታ እንዳይውሉና የክረምት ጊዜያቸውን በትምህርት እንዲያሳልፉ ለማድረግ ነው ብለዋል።

"ህጻናት ላይ የምትሰራ ሃገር ራሷን እየገነባች ነው ህጻናት ላይ የማትሰራ ሃገር ራሷን እያፈረሰች ነው" ያሉት መምህር መዝገበ ቃል ነገ ራሱን፣ ቤተሰቡን፣ ማህበረሰቡን ብሎም ሃገሩን የሚጠቅም ትውልድ ለመገንባት ህጻናትን በእውቀትና በስነ-ምግባር ኮትኩቶ ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ ህጻናት ላይ ሥራ እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የግብረ ገብነት ትምህርት መማር ቤተሰብንና ጎረቤትን ከማክበር ይጀምራል ያሉት መምህር መዝገበቃል ከኢትዮጵያ አልፎ ለዓለም የሚተርፍ ትውልድ ትውልድ ለማፍራት ህፃናትን በስነ-ምግባር አንፆና ገንብቶ ማሳደግ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በስነ-ምግባር የተባላሸ ትውልድ ቤተሰቡንም ሆነ ሃገሩን የወላድ መካን ያደረገ በመሆኑ ከትውልዱ ያጣነውን መልካም ሥራ ለመመለስ የግብረ ገብ ትምህርት ለመስጠት ተገደናል ብለዋል፡፡

በሒሳብ ፈጠራ ችሎታው የተራቀቀና ሃገር በቀል የሆነው የግዕዝ ቋንቋ ያወቀና በሁሉም የትምህርት አይነት ውጤታማ የሆነ ትውልድ መገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ትውልድ የመገንባቱ ሂደቱ ዛሬ ተጀምሮ ነገ የሚቆም ሳይሆን የዘወትር ተግባር ሆኖ የሚቀጥል በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል በማለት የአራቱ ጉባኤ መምህር የሆኑት መምህር መዝገበቃል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ካሳሁን በከተማ አስተዳደሩ ባሉ ትምህርት ቤቶች በልዩ ሁኔታ 6ኛ፣ 8ኛና 12ኛ ክፍል ክልላዊና አገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎችና በ2016 የትምህርት ዘመን ክፍተት ያለባቸውን ተማሪዎች በመለየት በ2017 የተሻለ የትምህርት ዝግጅት እንዲኖራቸው ከ8 መቶ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል።

የማጠናከሪያ ትምህርቱ አላማ ተማሪዎች
ቀጣይ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ታሳቢ ያደረገ ነው ሲሉ አቶ ታምሩ ገልጸዋል።

ትምህርት ተቋሙ የማጠናከሪያ ትምህርት የሚሰጥ የሰው ሃይል በማስተባበርና የተለያዩ ግብአቶችን በማሟላት የመማር ማስተማር ሥራውን ያስጀመሩ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው የዚህ እድል ተጠቃሚ ያልሆነ ተማሪዎች ከዚህ ሰዓት ጀምሮ የማጠናከሪያ ትምህርቱን መውሰድ ይኖርበታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#በጌትነት አጉማስ

01/08/2024

መዓዛ ወንጌልን በሕይወት መግለጥ
ርቱዓዊ ሰው ሁል ጊዜም ከዋናው ምንጩ ከእግዚአብሔር ማዕከልነት በመገለጫዎቹ ብርሃንነት እየተመራ ዓይነ ሥጋውን ጨለም ዓይነ ነፍሱን ገለጥ አድርጎ፣ እንደ ሥዕል ንድፍ ተሥሎ፣ አተኩሮ ማሰብ፣ ማየት፣ መሥራት፣ ሱታፌ ማድረግ አለበት። እግዚአብሐርን እና የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ በተቀደሰ ኅሊና በተዘክሮ ማመላለስ ይገባዋል። ይህ የጸጋ አምላካዊ የሱታፌ ሕይወት አበው ቅዱሳን የተጓዙበት የሕይወት ጎዳና ነውና። "ነኪራነ ረስዩ ርእሰክሙ እምኩሉ ግብራት ኃላፍያት አጽምሙ እለ ይትረዓያ አዑሩ አዕይንቲክሙ እለ በገሐድ ከመ ታእምሩ ፈቃዶ ለኢየሱስ ክርስቶስ ወትለብው ምሥጢረ መድኃኒትክሙ- ሰውነታችሁን ከኃላፊው ግብር ለዩ፤ አፍአዊ ጆሯችሁን ከመስማት አፍአዊ ዓይናችሁን ከማየት ከልክሉ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደውን ታውቁ ዘንድ የድኅነታችሁንም ምሥጢር ታስተውሉ ዘንድ" ሃይ.አበ. ፬፥፭ ብሎ አምላካችን ክርስቶስ በአፍአዊ ሕዋስ ላይ ሠልጥነን በውስጣዊ ኃይላችን እንመለከት ዘንድ እንደነገረን።

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Finot
Addis Ababa
1000