05/03/2026
📢 ለዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የቀረበ ጥሪ! 📢
ጉዳዩ፡- ከጃቾ ከተማ እስከ ኦርጫ ቀበሌ (የምርምር ማዕከል) እየተገነባ ስላለው የ6 ኪሎ ሜትር መንገድ
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከምዕራብ ሶሮ ወረዳ ማዕከል ከሆነችው ጃቾ ከተማ እስከ ኦርጫ ቀበሌ የዩኒቨርሲቲው ምርምር ማዕከል ድረስ ያለውን የ6 ኪሎ ሜትር የጥርጊያና የጠጠር መንገድ ለመስራት ያሳየው ቁርጠኝነት የሚመሰገን ተግባር ነው! 🙏
ነገር ግን በአሁኑ ወቅት በመንገዱ ላይ የሚታዩ ችግሮች እጅግ አሳሳቢ ናቸው፡-
⚠️ የጥራት ጉድለት፦ እየተሰራ ያለው መንገድ ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ፣ ቀድሞ ከነበረው ይልቅ አሁን ለተሽከርካሪና ለእግረኛ አስቸጋሪ ሆኗል።
⚠️ እንቅስቃሴ መገደብ፦ መንገዱ በአግባቡ ባለመሰራቱና ባለመጠገኑ ምክንያት በአካባቢው ያለውን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አግዶ ይገኛል።
⚠️ የተቋሙ ስም፦ እንዲህ ያሉ ጥራት የጎደላቸው ስራዎች ትልቅ ዝና እና ገጽታ ያለውን የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲን ስም በህዝቡ ዘንድ እምነት እንዲያጣ ሊያደርጉት ይችላሉ።
ስለሆነም የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች እና የሚመለከተው የፕሮጀክት ክትትል ክፍል፦
የዚህን መንገድ የግንባታ ጥራት በአስቸኳይ እንዲፈትሹ፤
ለህዝቡ የገቡትን ቃል አክብረው መንገዱ ለትራፊክ ምቹ እንዲሆን እንዲያደርጉ፤
በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን ቅሬታ ሰምተው አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡ በአክብሮት እናሳስባለን።
የልማት ስራ ጥራት ሲኖረው ነው ለህዝብ የሚጠቅመው! 🇪🇹
10/02/2026
03/12/2025
02/05/2025