Gulele branch educational training & quality & occ/competence assurance

Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance

Share

Gulele coc and eduactional quality

Telegram: Contact @AAEQOCAA 19/01/2024

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን, [18/01/2024 05:02]
[ Album ]
ብቁና ተወዳዳሪ ሙያተኛ እንዲኖር ለማድረግ የሙያ ብቃት ምዘና አይተኬ ሚና እንዳለዉ ተገለፀ፡፡
ጥር 9 ቀን 2016 ዓ.ም፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያዉን ግማሽ ዓመት የምዘና ዘርፍ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ ፡፡
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ፍቅሩ ገቢሳ ባስተላለፉት መልዕክትና የመድረኩን አላማ ሲገልጹ ጥራቱ የተጠበቀ የሙያ ብቃት ምዘና አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችለን ከቴ/ሙያ ተቋማት እና ከኢንዱስትሪ ተጠሪዎች ጋር በዘርፉ ያከናወናቸውን ስራዎችና ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በጋራ በመገምገም ጥንካሬዎቻችን እና ክፍተቶችን አንጥሮ በማዉጣት የተስተዋሉትን ክፍተቶች በቀጣይ ቀሪ 6ወራት የእቅድ አካል በማድረግ እና በመተግበር የተገልጋዮቻችንን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን, [18/01/2024 05:04]
አክለዉም በልምድ እና በተለያዩ ስልጠና የሚገኙ የተለያዩ የሙያዎችን ብቃት በምዘና ማረጋገጥ ሀገራችን በዝቅተኛና በመካከለኛ ደረጃ የምትፈልገውን የበቃ ሙያተኛ ለኢንዱስተሪው ለመመገብና ኢንዱስትሪው በእውቀት፣ በክህሎትና በአስተሳሰብ ብቁና ተወዳዳሪ ሙያተኛ እንዲኖረው ለማድረግ የሙያ ብቃት ሚና አይተኬ እንደሆነ ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ፍቅሩ ገቢሳ ገልፀዋል ፡፡
የ6 ወሩን የምዘና እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የቅ/ጽ/ቤቱ የቴ/ሙ/ብ/ም/አ/ዝ/አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጅላሎ አብደላ ሲሆኑ የቅ/ጽ/ቤቱ የ6ወሩ የምዘና እቅድ 7454 ስሆን ክንዉኑ 5449 ( 73 % ) መሆኑንና ከተመዘኑት ዉስጥ ብቁ የሆኑት 2642 ብቻ (48.4 % ) መሆኑን የገለፁ ሲሆን የምዘና ስራ የአፈፃፀም መመሪያን ለተሳታፊዎቹ ያቀረቡት የቴ/ሙያ ብቃት ምዘና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ነጋ ጉማታዉ ሲሆኑ በመመሪያ ዉስጥ የተካተቱትን ተግባራት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገቢዉ መንገድ በመፈፀም ኃላፊነቱን መወጣት እንደለበት አሳስበዋል፡፡ በመጨረሻም በቀረቡ ሰነዶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ለተነሱት ጥያዎች በቂ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠትና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ የእለቱ መድረክ ተቋጭቷል፡፡
ምንጭ፡- የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት

#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA

Telegram: Contact @AAEQOCAA

14/11/2023

30/2/2016
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ዙሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት ተደረገ፡፡
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና በቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ዙሪያ ከጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ የእቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ተወካይ የሆኑት አቶ አሸናፊ መለሰ የ2016 ዓ.ም 1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት ለ4,476 ተመዛኞች ብቃት በምዘና ማረጋገጥን እቅድ ተይዞ 3,231(72.2%) መመዘን ተችሏል፣ እንዲሁም በበጀት ዓመቱ የ5 የኢንዱስትሪ ማዕከላት የእድሳት ስራ መስራት እቅድ ተይዞ በሩቭ ዓመቱ 1(100%) መፈጸም መቻሉን የገለጹ ሲሆን በ4 ተቋማት የውጭ ኢንስፔክሽን መካሄዱን ተናግረዋል፡፡
በትምህርት ተቋማት ህገወጥ አካሄድን ለመቆጣጠር በ25 ተቋማት ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ለማድረግ እቅድ ተይዞ 100% መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ለ100% የትምህርትና ስልጠና ተቋማት አዲስ እዉቅና ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፤ በ40 ተቋማት የእውቅና ፍቃድ እድሳት ተካሂዶል፤ እንዲሁም በብልሹ አሰራር ረገድ 4 ግለሰቦች ላይ የማስተካከያ እርምጃ መወሰዱ በሰነዱ ላይ ተመላክቷል፡፡
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የ2016 በጀት አመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም በአብዛኞቹ ግቦችና ኢላማዎች የተገኘው ውጤት ከዕቅድ አንጻር ሲመዘን የተሳካ ሲሆን የታዩትን ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል በክፈተት የታዩ ተግባራትን መስተካከል እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሶ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

JELALU ABDELA, [14/11/2023 02:45]
[ Album ]

JELALU ABDELA, [14/11/2023 02:45]
[ Album ]

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 10/12/2021

በአ/አበባ ከ/አስተዳደር የትም/ት ስ/ጥ/ ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በስሩ ለሚገኙበ በመንግስትና መ/ባልሆኑ ትም/ት ተቋማት እየሰሩ ለሚገኙ እና በ2013 ዓ.ም የጽሁፍ ምዘና ወስደው ውጤታቸው 62.5%ና በላይ ያመጡ 132 መ/ራንና 1 ር/መምህር "የክንዋኔ ማህደረ-ተግባር (Port-Follow)" ተመዛኞች ለ2 ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና (Orientation) ተሰጠ::

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 24/09/2021

ቀን 14/01/14 ዓ.ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ግኝትን ለባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡
በት/ስ/ጥ/ሙ/ብ/ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ቡድን በ2013ዓ.ም በመደበኛ ኢንስፔክሽን የታዩ ተቋማት ውጤት ትንተና በቀን 14/01/2014 ዓ.ም በድልበር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ አድርጓል፡፡
በዕለቱ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮነን ታፈሰ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በዚህም መደበኛ ኢንስፔክሽን ማካሄድ ተቋማት የተሻለ ደረጃ ኖሯቸው የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ የሚያስችል በመሆኑ ይህ ይሳካ ዘንድ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ርብርብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
የመደበኛ ኢንስፔክሽን ውጤት ትንተናውን ያቀረቡት የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ኡርጂ ሙሉጌታ ሲሆኑ በ2013ዓ.ም በ50 መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ አጠቃላይ ትምህርት ተቋማት መደበኛ ኢንስፔክሽን ለማካሄድ ታቅዶ በ80 ተቋማት ላይ ማከናወን መቻሉንና ከነዚህም ውስጥ 44 መንግስታዊ ያልሆኑና 36 መንግስታዊ ተቋማት መሆናቸውን ተልጸዋል፡፡
ከታዩ ተቋማት መካከል 37 ቅ/መደበኛ፣20 የመጀመሪያ ደረጃ፣8 2ኛ ደረጃ ፣5 ኦ ክፍልና 10 አማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ተቋማት ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ ደረጃ 1 9(11.25%)፣ደረጃ 2 የሆኑ 67(83.75%)፣ደረጃ 3 የሆኑ 4(5%) ተቋማት ናቸው ፡፡እነዚህ ተቋማት በክፍል ደረጃ ሲታዩ ደረጃ 1 የሆኑ ኦ ክፍል 1፣ሁለተኛ ደረጃ 1 እና አማራጭ መሰረተ ትምህርት 7 ሲሆኑ ደረጃ 2 የሆኑ ኦ ክፍል 4፣ቅ/መደበኛ 37፣የመ/ደረጃ 17፣ሁለተኛ ደረጃ 6 እና አማራጭ መሰረታዊ ትምህርት 3 ተቋማት ፣ደረጃ 3 የገቡ ተቋማት የመጀ/ደረጃ 3 እና ሁለተኛ ደረጃ 1 መሆናቸው በውጤት ትንተናው ቀርቧል፡፡
አቶ ኡርጂ ውጤት ትንተናው ግብዓት ሂደትና ውጤትን መሰረት በማድረግ በቀጣይ በተለይ ደረጃ 1 እና ደረጃ 2 ያሉ ተቋማት ደረጃ ለማሻሻል የት/ቤት አመራሮች ፣ባለሙያዎች፣ሱፐርቫይዘሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
ከተሳታፊዎች በኩል የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን በሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በመጨረሻም በ2013 ዓ.ም ደረጃቸውን በማስጠበቅና በማሻሻል ደረጃ 3 ለሆኑ የትምህርት ተቋማት የእውቅናና ሰርተፍኬት አሰጣጥ ስነስርዓት ተከናውኗል፡፡

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 24/09/2021

ቀን 13/01/14 ዓ.ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የ2013 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅዱን ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ አደረገ፡፡
በት/ስ/ጥ/ሙ/ብ/ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የ2013 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅድ በቀን 13/01/14 ዓ.ም በድልበር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ አድርጓል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮነን ታፈሰ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ በ2013 ዓ.ም እንደ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና ጥራትና የሙያ ብቃትን በማረጋገጥ ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን በዚህም ውጤት እንደተገኘበት ገልጸው በ2014 ዓ.ም የተሻለ አፈጻጸም ለማምጣት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የ2013 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ያቀረቡት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ አለሙ የ2013ዓ.ም አፈጻጸም በሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ 15,420 ለመመዘን ታቅዶ 12,446(80.71%) መመዘን እንደተቻለና ከነዚህም ውስጥ 50.2% ማለትም 6372 ብቁ ሲሆኑ 5 አዳዲስ የምዘና ማዕከላት ለማፍራት ታቅዶ 7 ማፍራት እንደተቻለ 15 አዳዲስ መዛኞች ለማፍራት ታቅዶ 17 መዛኞችን ማፍራት የተቻለ ሲሆን በመምህራንና የት/ት አመራሮች ሙያ ብቃት ዘርፍ ለ394 የጽሁፍ ምዘና ለመስጠት ታስቦ 552 መስጠት መቻሉን ፣በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ለማየት ከታቀዱ 50 ተቋማት ውስጥ 80 ተቋማት ላይ ማከናወን መቻሉን ፣በትምህርትና ስልጠና ተቋማት እውቅና ፍቃድ እድሳት ዘርፍ ለ4 አዳዲስ ተቋማት እውቅና ፍቃድ ለመስጠት ታስቦ ለ7 ተቋማት መስጠት መቻሉን እንዲሁም ለ42 ተቋማት እድሳት ለማድረግ ታስቦ ለ42 ቱም መከናወኑና ድህረ እውቅና ለ46 ተቋማት ለመስጠት ታስቦ ለ46 ተቋማት ላይ የድህረ እውቅና ክትትልና ቁጥጥር መካሄዱ በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሙያ ብቃት ተመዝነው በቁ ለሆኑ ተመዛኞች 100% ቋሚና ጊዜያዊ ሰርተፍኬት መስጠት መቻሉ ተገልጽዋል፡፡
አቶ ክፍሌ የ2014 በጀት ዓመት እቅድ ሲያቀርቡ በሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ 14,935 ተመዛኖችን ብቃት ለማረጋገጥ መታቀዱና በመምህራንና ትምህርት አመራሮች ዘርፍ ለ384 የማህደረ ተግባርና የጽሁፍ ምዘና ለመስጠት መታቀዱን ፣በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ በ78 የትምህርትተቋማት ላይ መደበኛ ኢንስፔክሽን ፣60 ተቋማት ላይ ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ለማከናወን መታቀዱን ፣በእውቅና ፍቃድ ዘርፍ በ54 ተቋማት ላይ የእውቅና ፍቃድ እድሳት ለማከናወን መታቀዱን እንዲሁም በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሙያ ብቃት ተመዝነው በቁ ለሆኑ ተመዛኞች 100% ቋሚና ጊዜያዊ ሰርተፍኬት ለመስጠትና የመረጃ ፍሰቱን 95% ለማድረስ መታቀዱ ተገልጽዋል፡፡
በመድረኩ ተሳታፊዎች በኩል የተለያዩ ጥያቆዎችና አስተያየቶች ተነስተው በሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 06/09/2021

እንኳን ለ2014 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ
አዲሱ አመት የሰላም፤ የፍቅር፤ የብልፅግና ይሁንላችሁ
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 20/08/2021

ቀን 14/12/13 ዓ.ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅዱን ከሰራተኞች ጋር የጋራ አደረገ፡፡
በት/ስ/ጥ/ሙ/ብ/ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅዱን በቀን 14/12/13ዓ.ም በቅ/ጽ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
በዕለቱ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮነን ታፈሰ የ2013 በጀት ዓመት አፈጻጸም ከመጀመሪያው 6 ወር የ2ኛው 6 ወር የተሻለ አፈጻጸም ማሳየቱን ገልጸው በ2014 ዓ.ም የታዩ ክፍተቶችን በማስተካከልና የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ በመቀጠል የተሻለ አፈጻጸም ለማምጣት ሁሉም ባለድርሻ አካል በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱን የ2014 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ያቀረቡት የመምህራንና የት/ት አመራሮች ሙያ ብቃት ምዘና አሰጣጥ ቡድን መሪ አቶ መስፍን አበረ ሲገልጹ በበጀት አመቱ በትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማረጋገጥ ዘርፍ በ60 የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት ላይ የውጭ ኢንስፔክሽን ለማካሄድና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ለመስጠት መታቀዱን የገለጹ ሲሆን በት/ስ/ተ/እውቅና ፍቃድ እድሳት ዘርፍ ለ54 ተቋማት እውቅና ፍቃድ እድሳት ለመስጠትና የድህረ እውቅና ፍቃድ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ጥያቄ ለሚያቀርቡ ሰልጣኞች 100% ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል፡፡በሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ 18,612 የሙያ ብቃት ተመዛኞችን በምዘና ለማረጋገጥና አዳዲስ የምዘና ማዕከላትንና 10 አዳዲስ መዛኞችን ለማፍራት መታደቁን አቶ መስፍን አብራርተዋል፡፡በመምህራንና የት/ት አመራሮች የጽሁፍ ምዘና ዘርፍም ለ421 የጽሁፍ ምዘናና የማህደረ ተግባር ምዘና ለመስጠት መታቀዱን ተገልጽዋል፡፡በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ በምዘና ብቁ ለሆኑ ተመዛኞች 100% ቋሚና ጊዜያዊ ሰርተፍኬት ለመስጠትና በደረጃ ተመዝነው ብቁ ለሆኑ ተመዛኞች 100% በድረ ገጽ በቀጥታ ለማሰራጨት ታቅዷል፡፡
በእለቱ ከቀረበው መሪ እቅድ በመነሳት ከሰራተኞች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 19/06/2021
Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 19/06/2021

ቀን 11/10/2013ዓ/ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የልምድ ልውውጥ አካሄደ፡፡
በአ/አበባ ከተማ አስተዳደር በትምህርትና ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅርንጫፍ የት/ስ/ተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ዳይሬክቶሬት በ 11/10/2013ዓም /የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ባለቤቶችና ርዕሰ መምህራን ፣ከክፍለ ከተማና ከወረዳ የተውጣጡ የትምህርት ባለሙያዎች በተገኙበት በቀኝ አዝማች አንዳርጌ መታሰቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የልምድ ልውውጥ ተካሂዷል፡፡
በቅ/ጽ/ቤቱ የት/ስ/ተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ስርጉት ሺመልስ የልምድ ልውውጡ ዓላማ በግብዓትና በአደረጃጀት እንዲሁም በአሰራር ቤንችማርክ የሆኑ ተቋማትን መፍጠር ነው ብለዋል፡፡አክለውም ስለተቋሙ አመራረጥ ሲገልጹ በ ዓ.ም እውቅና ፍቃድና እድሳት ካከናወኑ ተቋማት መካከል የተሻለ ውጤት ያመጣ ተቋም በመሆኑ ለሌሎች ልምድ እንዲያካፍል በማሰብ ነው ብለዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮነን ታፈሰ በበኩላቸው ልምድ ልውውጡ በግብዓትና በአደረጃጀት የተሻለውን ተቋም በመምረጥ እያንዳንዱ ተቋም ለራሱ የሚጠቅመውን ወይም የተሻለውን አሰራር ወደራሱ ተቋም ወስዶ እንዲለውጥ ለማስቻልና ወደ ተቀራረበ ስታንዳርድ እንዲመጡ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል፡፡
የቀኝ አዝማች አንዳርጌ መታሰቢያ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ልዑል ሰገድ ዘካሪያስ ት/ቤታቸው ለቤንችማርክነት በመመረጡ መደሰታቸውን ገልጸው ት/ቤቱ በወጣትነት እድሜ ላይ ያለና ከትንሽ ደረጃ ተነስቶ በርካታ ውስብስብ ችግሮችን አልፎ ለስኬት የበቃ ተቋም ነው ብለዋል፡፡ስራዎችን በተቀናጀና በተናበበ ሁኔታ መስራታችን ተቋማችን አሁን ላለበት ደረጃ አብቅቶታልም ብለዋል፡፡
በዕለቱ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች ያላቸው የአደረጃጀት፣የግብዓትና የአሰራር ሁኔታ ተጎብኝቷል፡፡
በልምድ ልውውጡ የተካፈሉ እንግዶች የቀኝ አዝማች አንዳርጌ መታሰቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ብዙ ልምድ እንዳገኙና በቀጣይ ወደራሳቸው ተቋም በመውሰድ ለመስራት መነሳሳታቸውን ተናግረዋል፡፡

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 14/06/2021

ቀን 07/10/2013ዓ.ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የልምድ ልውውጥ አካሄደ፡፡
በአ/አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች በቀን 05/10/2013 ዓ.ም በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ በመገኘት የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል፡፡
በእለቱ የተቋሙ ቴክኒካል ባለሙያዎች ስለተቋሙ አሰራርና ስላለበት ሁኔታ ገለጻና የማስጎብኘት ስራ ተሰርቷል፡፡በጉብኝቱም የታንክና ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች መገጣጠሚያና እድሳት ስራ እንዲሁም ልዩ ልዩ ከባድና ቀላል ተሸከርካሪዎች ከመገጣጠም ጀማሮ ለአገልግሎት ዝግጁ እስከሚሆኑ ድረስ የሚያልፉበትን ሂደት ተጎብኝቷል፡፡ተቋሙ በቂና የሰለጠነ የሰው ሃይል ያለው እንዲሁም የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር የተደረገ በመሆኑ ወደፊት አቅም እየጎለበተ ሲሄድ ማሽነሪዎችን (ሞልዶችን ) በራስ አቅም ለመስራት የሚቻልበት ሁኔታ መኖሩንና ይህም ለሀገር እድገት ጠቃሚ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮነን ታፈሰ በበኩላቸው ተቋሙ ከነበረበት ውስብስብ ችግር ተላቆ ወደስራ መግባቱ የሚደነቅና ትምህርት የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ከልምድ ልዉዉጡ ትምህርት ማግኘታቸውን እንዲሁም በፊት ከነበረበት ተለውጦና ተሻሽሎ ማየታቸውንና የማያውቋቸውን ነገሮች እንዲያዉቁ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡

Photos from Gulele branch educational training  &  quality & occ/competence assurance's post 26/03/2021

ቀን 17/07/2013ዓ.ም
ቅ/ጽ/ቤቱ የ2013ዓ.ም የ2ኛ ግማሽ ዓመት የተከለሰ እቅድ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት፣ ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን ጉለሌ ቅርንጫፍ የ2013ዓ.ም የ2ኛ ግማሽ ዓመት የተከለሰ እቅድ በቀን 17/07/2013ዓ.ም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
በዕለቱ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ታፈሰ የ2ኛ ግማሽ ዓመት እቅድ መከለሱ ከሰራተኛው ጋር የጋራ ማድረግ ከመጀመሪያው ግማሽ ዓመት አፈጻጸም የነበረውን ጥንካሬና ድክመት በመገምገምና አፈጻጸሙን መሰረት በማድረግ እቅዱ መከለሱን ገልጸው በቀጣይ የቀሩትን ስራዎች አጠናክሮ በመቀጠል የተሻለ አፈጻጸም ለማምጣት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክቶር አቶ ክፍሌ አለሙ የ2ኛ ግማሽ ዓመት የተከለሰ እቅድ ሲያቀርቡ በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ የቅድመ መደበኛ፣ የኦ ክፍሎች፣ የአማራጭ መሰረታዊ የትምህርት ጣቢያዎች፣ የመጀመሪያ ደረጃ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ተቋማት ላይ የውጭ ኢንስፔክሽን በማካሄድ 100% የደረጃ ምደባ በማካሄድና ግብረ መልስ መስጠት፣ድንገተኛ ኢንስፔክሽን ማካሄድ፣በእውቅና ፍቃድ ዘርፍ የድህረ እውቅና ክትትልና ቁጥጥር ማድረግና መስፈርቱን ላሟሉ ተቋማት የእውቅና ፍቃድና እድሳት አገልግሎት መስጠት ፣በሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ 15 አዳዲስ ብቁ መዛኞችና ማፍራት፣ለ5 አዳዲስ የምዘና ማዕከላት እውቅና መስጠትና ለ30 ነባር የምዘና ማዕከላት እድሳት ማድረግ ለ15,420 ተመዛኞችን ብቃት በምዘና በማረጋገጥ እንዲሁም የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና አመራሮች በመንግስት፣ በግልና በመያድ በጠቅላላው 394 የጽሑፍ ምዘና፣ 100% የማህደረ ተግባር ምዘና እንዲሁም 100%እውቅና ፍቃድ የምስክር ወረቀት በመስጠት የሙያ ብቃታቸውን ማረጋገጥ ፣የድረ-ገጽ ግንባታና ማሻሻያ፣የኔትዎርክ መሰረተ-ልማት ዝርጋታ፣የአንድ ቋት የመረጃ ፍሰቱን ቀጣይነት በማረጋገጥ የመረጃ ሽፋን፣ ጥራትና ተደራሽነት 100% ማድረስ በቀሪ 6 ወራት ውስጥ የሚከናወኑ ተግባራት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ከሰራተኞች በኩል የ2ኛ ግማሽ ዓመት እቅድ የተከለሰ እቅድ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በመጨረሻም በ6 ወራት ውስጥ የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው ሰራተኞችና ዳይሬክተሮች የእውቅናና ሰርተፍኬሽን አሰጣጥ ስነስርዓት ተከናውኗል፡፡

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Address

Addis Abeba Samen Hotel
Addis Ababa