አድስ ተዋህዶ መዝሙርና ለሎች ነገሮችን ጭምር

አድስ ተዋህዶ መዝሙርና ለሎች ነገሮችን ጭምር

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አድስ ተዋህዶ መዝሙርና ለሎች ነገሮችን ጭምር, Addis Ababa.

28/10/2021
22/10/2021

ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙትን የጾም ዓይነቶች እንዲሁም መቼ እና ለምን እንደሚጾሙ
ከመጥቀሳችን በፊት ጾም ማለት ምን ማለት እንደሆነና መቼ እንደተጀመረ ማወቅ አስፈላጊ ስለሚሆን ከዚህ በታች መጠነኛ
የሆነ ማብራሪያ እንሰጥበታለን፡­
ጾም መቼ ተጀመረ፤ የማንስ ትእዛዝ ነው?
ጾም ማለት በምግብ እጦት መሰቃየት ወይም የሚበሉት ነገር አጥቶ መቅበዝበዝና መባከን ላለመሆኑ የአዳምና የሔዋን ኑሮ
ቋሚ ምስክር ነው። ምክንያቱም በተድላ እና በፍሥሐ በመኖር ምድር ፍሬዋን ሳትከለክላቸው የሚበላው እና የሚጠጣው
ነገር ሁሉ ከፊታቸው ነበራቸውና። ለአዳምና ለሔዋን ልዑል እግዚአብሔር የሚበሉትን ነገር ሳይከለክላቸው ከተወሰነ
ምግብ ግን እንዳይበሉ አዝዞአቸዋል። እንግዲህ ጾም ማለት የሥጋ ፍላጎትን መግታት ማለት እንጂ ምግብ ማጣት አይደለም።
ከጾም መታዘዝን፣ ራስ መግዛትን፣ የሥጋን ፍላጎት መቆጣጠርን፣ እግዚአብሔርን ማወቅን፣ ታማኝነትን እና በተስፋ
መጠበቅን እንማራለን። ስለዚህም ጾም የተጀመረው በመጀመርያው የሰው ልጆች ፍጥረት በሆኑት በአዳምና በሔዋን ሲሆን
ይኽንንም መልእክት ያስተላለፈው እግዚአብሔር ነው። አምላክ መሆንን ይሻ የነበረው የቀደመው እባብ ምኞቱና ሐሳቡ
መክኖ ስለቀረበት ወደ አዳምና ሔዋን በመሔድ ያልተፈቀደላቸውን ነገር አይተው እንዲጓጉ ሁኔታዎችን አመቻቸላቸው።
ከተከለከለው በመብላታቸው መታዘዝን ዘነጉ፣ ራስ መግዛትን ተዉ፣ የሥጋን ምኞት መቆጣጠርን ቸል አሉ፣ እግዚአብሔርን
ማወቅን ሰነፉ፣ ታማኝነትን እና በተስፋ መጠበቅን ረሱ። እንግዲህ አለመታዘዛቸው ምን እንዳስከተለባቸው ለሁላችን
ትምህርት ሆኖን እኛም በምንጾምበት ጊዜ ፈቃደ እግዚአብሔርን የምንፈጽም መሆን ይገባናል። ምንጊዜም ቢሆን ሥጋችንን
ሊያስደስት እና እኛን ሊያሳስተን የሚመጣ ነገር መኖሩን መርሣት የለብንም። ትናንት አዳምና ሔዋንን ከእግዚአብሔር የለያየ
እና ከመልካም ስፍራ እንዲወቱ ያደረገ ከሳሽ ዲያብሎስ ዛሬ በእኛ እቅፍ የለም ለማለት አይቻልም። ዕለቱን ባያስፈርድብን
በመጨረሻው ዘመን ደጃፍ ያዘጋብናልና በምንጾምበት ጊዜ ራስን በመግዛት በፈሪሃ እግዚአብሔር መሆን ይጠበቅብናል።
የጾም አስፈላጊነት፡­
ለሰው የሚያስፈልገውን ሁሉ ያዘጋጀ አምላክ ዘወትር መብላትና መጠጣት ብቻ ሰውን ስለማያንጸው
የጾምን አስፈላጊነት ጠቅሶለታል። ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ጾም ባስተማረበት አንቀጹ
እንዲህ በማለት ያስተምረናል፡­
 ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት
እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ
ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።
ማቴ.፮፡­ �
ሰው ደስተኛ ሆኖ እንዲኖር የሚያስፈልገው ገንዘብ ብቻ አይደለም። ሀብት እያላቸው የማይደሰቱ፣ ልጆች እያላቸው ባዶነት
የሚሰማቸው፣ በመልካም ኑሮ እየኖሩ የጎደለባቸው፣ ተምረው እርካታ የሌላቸው ብዙዎች ናቸው። ከዚህ ቃል የምንረዳው
ሰው ለፍጹም ደስታው የእግዚአብሔር እጅ እንጂ ምግብና መጠጥ ብቻ እንደማያስፈልገው ነው። ጌታችን በገዳመ ቆሮንቶስ
በፈታኝ ዲያብሎስ ለቀረበለት ጥያቄ ከመጽሐፍ በመግለጽ ምላሽን እንደሰጠው ልብ ልንል ያስፈልጋል። እግዚአብሔር
ለሕዝበ እስራኤል የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስፈልጋቸው ሲነግራቸው እንዲህ ይለናል፡­
 በሕይወት እንድትኖሩ፥ እንድትበዙም፥ እግዚአብሔርም

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Addis Ababa