Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ

Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ

Share

We provide you the latest and fundamental information about Ethiopian Banking Sector.
#Banking_Jobs

10/06/2026

የብሔራዊ ባንክ (NBE) የቅርብ ጊዜ የፎሬክስ ማሻሻያ ከዚህ ቀደም በቀጥታ በNBE ይከናወኑ የነበሩ አንዳንድ የውጭ ክፍያ ፈቃዶችና የሰነድ ማረጋገጫ ሂደቶችን ወደ ንግድ ባንኮች አስተላልፏል።

ይህ የውሳኔ ሂደትን ለማፋጠን፣ ቢሮክራሲን ለመቀነስ እና ለንግድ ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የታለመ ቢሆንም፣ ከአዲሱ ስልጣን ጋር ትልቅ ኃላፊነትና አደጋም መምጣቱ ትኩረት ስቧል።

ከካፒታል ጋዜጣ ጋር ቆይታ ያደረጉ ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ባንኮች የውጭ ንግድ ሰነዶችን በጥልቀት መመርመር፣ የማጭበርበር ሙከራዎችን መለየት እና ከውጭ አጋር ተቋማት ጋር የሚደረጉ ግብይቶችን በአግባቡ ማስተዳደር የሚያስችል በቂ አቅም እንዳላቸው ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።

ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች
• በውጭ ንግድና ፎሬክስ ዘርፍ የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረት
• የተጭበረበሩ ሰነዶችን ወይም ግብይቶችን የመለየት አቅም ውስንነት
• በባንኮች መካከል የአሰራር ልዩነት መኖር
• የቴክኖሎጂና የክትትል ስርዓቶች አለመጠናከር
• የፋይናንስ ኪሳራና የሕግ ተጠያቂነት መጨመር

ባለሙያዎች የሚመክሩት
• የባንክ ሰራተኞችን በፎሬክስና በውጭ ንግድ ጉዳዮች በስፋት ማሰልጠን
• የአደጋ አስተዳደር ስርዓቶችን ማጠናከር
• ዘመናዊ የዲጂታል ማረጋገጫና ክትትል ስርዓቶችን መጠቀም
• ብሔራዊ ባንክ በቅርብ ክትትልና ድጋፍ መቀጠል

አዲሱ ማሻሻያ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎቶችን ለማፋጠን ትልቅ ዕድል ቢፈጥርም፣ ስኬቱ በመጨረሻ ባንኮች አዲሱን ኃላፊነት ለመሸከም ያላቸው ዝግጁነት ላይ እንደሚመሰረት ባለሙያዎች ያስገነዝባሉ።

💬 እርስዎ ምን ይላሉ? የኢትዮጵያ ባንኮች ይህን አዲስ ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ናቸው? አስተያየትዎን ያጋሩ።

10/06/2026

በውስጥ የደረሠን መረጃ

10/06/2026

የደቡብ አፍሪካው ስታንቢክ ባንክ በኢትዮጵያ በራሱ ሙሉ ባለቤትነት አዲስ ባንክ በመመስረት ሥራ ለመጀመር እያጤነ መሆኑ ተገለጸ።

የደቡብ አፍሪካው ስታንቢክ ባንክ በኢትዮጵያ አዲስ ባንክ በመመስረት ሙሉ ባለቤትነት ያለው ሥራ ለመጀመር እያጤነ መሆኑ ተገለጸ።
ይህ ውሳኔ የውጭ ባለሀብቶች በአገር ውስጥ ባንኮች እስከ 49% ብቻ ድርሻ እንዲይዙ ከተፈቀደው ደንብ በኋላ የተወሰደ ነው። ይህም ብዙ የውጭ ባንኮችን ከነባር ባንኮች ድርሻ ከመግዛት ይልቅ አዲስ ባንክ እንዲመሰርቱ እየገፋፋ ነው።
የስታንዳርድ ባንክ ቡድን አባል የሆነው ስታንቢክ ከ2015 ጀምሮ በኢትዮጵያ የተወካይ ቢሮ ያለው ሲሆን፣ በመሠረተ ልማት፣ ኃይል፣ ግብርና፣ ቴሌኮም እና ዲጂታል አገልግሎቶች ዘርፎች ትልቅ ዕድል እንዳለ ያምናል።
የምስራቅ አፍሪካ ኃላፊ ጆሹዋ ኦይጋራ እንደገለጹት፣ ባንኩ የረጅም ጊዜ ዕቅድን በመከተል በኢትዮጵያ የእድገት እድሎችን እየገመገመ ነው።
ኬንያው KCB እና Equity እንዲሁም የናይጄሪያ Zenith Bank እና FirstBank ከዚህ ቀደም ወደ ኢትዮጵያ የመግባት ፍላጎታቸውን ገልጸው ነበር። ኦይጋራም የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ጥቅም ጥሩ ምሳሌ መሆኑን ጠቅሰዋል።

10/06/2026

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ተቋም የሚሰጠውን የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ለናይጄሪያው የፋይናንስ ግዙፍ ተቋም ‘ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ’ መስጠቱን በይፋ አስታወቀ።

​ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰጠው ይህ ፈቃድ፤ ባለሥልጣኑ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ሌሎች የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለወራት ያደረጉትን ጥብቅ የሕግና የሰነድ ምርመራ ተከትሎ የተሰጠ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክር ሀና ተኸልኩ በተለይ ለካፒታል ጋዜጣ ተናግረዋል።

ዩናይትድ ካፒታል ‘ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር’ የተሰኘ ሙሉ በሙሉ የራሱ የሆነ የአካባቢው ቅርንጫፍ በመክፈት ከስድስት አስርት ዓመታት በላይ ያካበተውን የአፍሪካ አቀፍ ልምድ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል።

​ባለስልጣኑ እንደገለፀው ፤ ይህ ሙሉ በሙሉ በውጭ ተቋም ባለቤትነት የተያዘ ፈቃድ መሰጠቱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሊበራላይዜሽን ማሻሻያ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ማረጋገጫ ነው። ተቋሙ በሕግ ከተቀመጠው የ25 ሚሊዮን ብር አነስተኛ ካፒታል በላይ፣ ከ1.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ በቀጥታ ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቷል።

በኢያሱ ዘካሪያስ ከ Capital Ethiopia

10/06/2026

የምዕራባውያንን የፋይናንስ ሥርዓት (SWIFT) የበላይነት ለመስበር እና በውጭ የፖለቲካ ተጽዕኖዎች የሚመጣን የኢኮኖሚ ጫና ለመመከት፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚውል ዲጂታል የውጭ ምንዛሬ መላኪያ መረብ በይፋ ሥራ አስጀምራለች።

ከ35 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ኪሳራን ለማዳን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሀገር በቀሉ ኢግል ላዮን የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በመተባበር የተገነባው "CBE Connect Digital Wallet"፣ በየዓመቱ በጥቁር ገበያ (ሃዋላ) የሚባክነውን ከ35 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዲያስፖራ ገንዘብ ወደ ህጋዊ መስመር ለማስገባት ያለመ ነው። ዘ-ሐበሻ እጅ የሚገኙ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በአሁኑ ወቅት በህጋዊ መንገድ ወደ ሀገር እየገባ ያለው የውጭ ምንዛሬ 22 በመቶ (7.2 ቢሊዮን ዶላር) ብቻ ነው።

የኢግል ላዮን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ በሱፈቃድ ጌታቸው በምረቃው ላይ እንደገለጹት፣ "ይህ መተግበሪያ ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ የፋይናንስ መሰረተ-ልማት ነው፤ የውጭ ፖለቲካ ኃይሎች የገንዘብ ፍሰታችንን ሊዘጉብን የማይችሉበትን አቅም ፈጥረናል" ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ይህ ፕላትፎርም ግለሰቦች የውጭ ምንዛሬን (ዶላር/ዩሮ) በዲጂታል መንገድ እንዲይዙ (Dollar Wallet) ፈቅዷል፤ ይህም ከዚህ በፊት ለግለሰቦች የተከለከለ ነበር። ስርዓቱ ሳውዲ አረቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ዩኤሬ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በቀላሉ ገንዘብ ወደ ሀገር ቤት እንዲልኩ እና ለ70 ሚሊዮን የባንክ ሂሳቦች በቅጽበት ተደራሽ እንዲያደርጉ ያስችላል።

ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ በውጭ ምንዛሬ ግኝት ራሷን ለመቻል እና ከምዕራባውያን ጥገኝነት ለመላቀቅ የምታደርገው ትልቅ ስትራቴጂካዊ አካሄድ ተደርጎ ተወስዷል።
..
ምንጭ : @ዘ-ሀበሻ ዜና

06/06/2026

ደረጃ 16 ያለ የሲንቄ ባንክ ሠራተኛ የትራንስፖርት ብቻ 42,885.5 ብር በወር ያገኛል 😎😳

05/06/2026

አዲሱን የሲቢኢ አፕ ስልካችሁ ላይ ስትጭኑ ከታች በምስሉ የሚታየው መልኩ አልሰራ ካላችሁ በመጀመሪያ የስልካችሁ ስክሪን ዝግ ካልሆነ ፓተርን ወንም ፒን በመስጠት ስልካችሁ በፒን እንዲከፈት አድርጉ።አሁንም አልሰራ ካለ setting ውስጥ developer option off መሆኑን አረጋግጡ ስልካችሁ ላይ developer option ከሌለ setting ውስጥ build number ብላችሁ search አድርጉ ከዚያ ስምንት ጊዜ ተጫኑት፣build number የሚል ቁጥሮችን የያዘ ምርጫ ሲመጣላችሁ በተደጋጋሚ ተጫኑት ከዚያ developer option የሚል ምርጫ ይመጣል on ከነበረ off አድርጋችሁ ውጡ።ከዚያ ስልኩን Restart አድርጉ ይስተካከላል።
Via M***a

05/06/2026

ተሳተፉ

04/06/2026

ፀሀይ ባንክ በእያንዳንዱ ሰራተኛ 171,900 ብር እየከሰረ ነው ተባለ።
ባንኩ ይህን ኪሳራ እያስተናገደ ያለው ሌሎች ባንኮች በአማካይ በአንድ ሠራተኛ 310,655 ብር እያተረፉ ባለበት ነው። ባንኩ እንደገለፀው 1.03 ቢሊየን ብር ሲያስገባ 1.3 ቢሊየን ብር ደግሞ አውጥቷል። ይህም ኪሳራውን 271.4 ሚሊዮን ብር ያደርሰዋል። የባንኩ አመራር ወጪ ለመቀነስ የተለያዩ መንገዶችን እንደሚጠቀሙ የገለፁ ሲሆን የቅርንጫፎቻቸውን ስፋት እንደሚቀንሱም ተናግረዋል።

02/06/2026

በሰለም ስጠቀም የነበረውን አፕሊኬሽን ስራ አቁመው እያንከራተቱኝ ነው።

ሰሞኑን ንግድ ባንክ መመላለስ የስራ ቦታዬ ነው የሚመስለው፣ በዲጂታል ዘመን ንግድ ባንክ ምክንያቱ ምን እንደሆነ በማላውቀው ተደጋጋሚ እያመላለሰኝ ነው።

በኦላይን ያያዘኩትን ፋይዳ በድንገት አልተያያዘም ብሎ ረጅም ሰልፍ አሰልፎ ከፈተልኝ አሁን ደግሞ ቅዳሜ በድንገት አፕሊኬሽኑ ስራ አቁሞ ድጋሜ ወደ አሰልቺው ቅርጫፍ መስሪያ ቤት ብሄድም ገበያ መስሏል የህዝቡ ብዛት... ጉዳዬን አስረድቼ ለአይፎን ከሰዓት ና አሁን ሲስተም እየሰራ አይደለም ብለው ሸኙን።

እሁድ እና ሰኞን አሳልፌ ዛሬ ወደ ሌላኛው ቅርጫፍ ስሄድ እንደተለመደው በህዝብ ተጨናንቋል በዛ ላይ ሲስተም የለም OTP እያለከ አይደለም ብለው ሸኙን።

ባንኩ ለምንድነው በዚህ ዲጅታል ዘመን ህዝቡን በቅርጫፉ የሚያከማቸው፣ ለምንስ ነው የባንኩ አፕሊኬሽኖች ያለ ምክንያት ስራ የሚያቆሙት?

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Addis Ababa