Abextube

Abextube Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abextube, Tutor/Teacher, Addis Ababa.

ሰበር : - 27.1 ሚሊዮን እይታዎች በአንድ ቀን! ቴዲ አፍሮ በዓለም የምርጥ 20ዎች ዝርዝር ውስጥ ስሙን በወርቅ ቀለሙ ጻፈ:ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከ9 ዓመታት ቆይታ በኋላ...
17/04/2026

ሰበር : - 27.1 ሚሊዮን እይታዎች በአንድ ቀን!

ቴዲ አፍሮ በዓለም የምርጥ 20ዎች ዝርዝር ውስጥ ስሙን በወርቅ ቀለሙ ጻፈ:

ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከ9 ዓመታት ቆይታ በኋላ፣ 18 ሙዚቃዎችን ያካተተ “ኢትዮሪካ” የተሰኘ ስድስተኛ አልበሙን ትላንት በዚሁ ሰዓት በይፋ ለቋል።

አልበሙ ከተለቀቀበት ቅጽበት ጀምሮ ከፌስቡክ እስከ ቲክቶክ፣ ከዩቲዩብ እስከ X (ትዊተር) ዋነኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኗል።

በሀገራችን የኪነ-ጥበብ ስኬቶችን በዝርዝር መዝግቦ ይፋ የሚያደርግ ተቋም ባይኖርም፣ በግል ጥረት ጎግልን (Google) በመጠቀም በተደረገ ፍተሻ ቴዲ አፍሮ የሚከተሉትን ታሪካዊ ስኬቶች አስመዝግቧል፡

1. የአፍሪካ አዲስ ሪከርድ

ቴዲ አፍሮ በአንድ የአፍሪካዊ ድምፃዊ ታሪክ ውስጥ በ24 ሰዓታት ውስጥ ከፍተኛ ተመልካች በማግኘት ቀደም ሲል የነበረውን የ22 ሚሊዮን እይታ ሪከርድ በመስበር፣ በድምሩ 27.1 ሚሊዮን እይታዎችን በማግኘት የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሆኗል።

2. የሰብስክራይበር (Subscriber) እድገት

የድምፃዊው የዩቲዩብ ቻናል በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ አዳዲስ ተከታዮችን በማፍራት 1.84 ሚሊዮን ደርሷል። ይህ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመዘገበ ከፍተኛ እድገት በአፍሪካ ታይቶ የማይታወቅ ነው።

3. "ዳስ ጣል" እና ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ

በአልበሙ ውስጥ የሚገኘው "ዳስ ጣል" የተሰኘው ሙዚቃ ብቻውን ከ4 ሚሊዮን በላይ እይታዎችን በማግኘት፣ በዩቲዩብ ታሪክ በ24 ሰዓታት ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት ከሳቡ ጥቂት ቪዲዮዎች ተርታ ተሰልፏል።

4. ከምርጥ 20ዎቹ ተርታ

የዓለምን የ24 ሰዓት የሪከርድ ዝርዝር ስንመለከት (ለምሳሌ የቢቲኤስ "Butter" 113 ሚሊዮን)፣ ቴዲ አፍሮ በ27.1 ሚሊዮን እይታው በዓለም ደረጃ በ24 ሰዓታት ውስጥ ከፍተኛ እይታ ካገኙ ምርጥ 20 አርቲስቶች አንዱ ለመሆን በቅቷል።

ይህም አልበሙን ከእንግሊዝኛ ቋንቋ ውጭ ተሰርተው እንዲህ ያለ ከፍተኛ እይታ ካገኙ ጥቂት የሙዚቃ ስራዎች ቀዳሚ ያደርገዋል።

* ዳስ ጣል፦ 4.2 ሚሊዮን በላይ
• ጀምበር፦ 2.8 ሚሊዮን በላይ
• መሬማ፦ 2 ሚሊዮን በላይ
• ጽዮን ሙሽራዬ፦ 1.8 ሚሊዮን በላይ
• ስምምነን፦ 1.6 ሚሊዮን በላይ
• ኢትዮሪካ፦ 1.4 ሚሊዮን
• መርከብ፦ 1.4 ሚሊዮን በላይ
• ስማ ራሴ፦ 1.4 ሚሊዮን በላይ
• ሺ ቢባል፦ 1.3 ሚሊዮን በላይ
• ብልጭታ፦ 1.3 ሚሊዮን በላይ
• የአዞ ዕንባ፦ 1.3 ሚሊዮን በላይ
• ዝ ፀዳል፦ 1.3 ሚሊዮን በላይ
• ሳምነው፦ 1.2 ሚሊዮን በላይ
• ታንታጎ፦ 1.1 ሚሊዮን በላይ
• በመስኮቱ፦ 1.1 ሚሊዮን በላይ
• ታየኝ፦ 1 ሚሊዮን በላይ
• ተወዳጅ፦ 932 ሺህ በላይ
• የማዕረግ ጥግ፦ 861 ሺህ በላይ

ማጠቃለያ

ማህበራዊ ሚዲያ መጠቀም ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲህ በአንድ ድምፅና በአድናቆት የቆሙበት አጋጣሚ አይቼ አላውቅም። የፌስቡክ ግድግዳዎች በሙሉ በኢትዮጵያዊነት ፍቅርና በቴዲ አድናቆት ተሞልተዋል።

ማሳሰቢያ፦ ይህ መረጃ ጎግልን እና የዩቲዩብ መረጃዎችን በመጠቀም በግል ጥረት የተዘጋጀ ነው።

Via ታዴ የማመይ ልጅ

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

በሚዛን ተፈሪ ከተማ የአቡነ ተ/ሀይማኖት አካዳሚ መስራችና አስተዳዳሪ እማሆይ ፅጌ ማርያም ዛሬ ከሰይፉ ጋር ባደረጉት ቆይታ ከተናገሩት በከፊል የተወሰደ👇👇👇-"በምንኩስና መከራ ሲያጋጥም ደስታ...
02/03/2026

በሚዛን ተፈሪ ከተማ የአቡነ ተ/ሀይማኖት አካዳሚ መስራችና አስተዳዳሪ እማሆይ ፅጌ ማርያም ዛሬ ከሰይፉ ጋር ባደረጉት ቆይታ ከተናገሩት በከፊል የተወሰደ

👇👇👇

-"በምንኩስና መከራ ሲያጋጥም ደስታ ነዉ።"

- "በአካዳሚዉ ከ2012 ዓ.ም ወዲህ ከ600 በላይ ተማሪዎች በነጻ ተምረዋል"

-"ከኦርቶዶክሳዊያን በተጨማሪ የእስልምና እና ፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ተማሪዎች በነጻ ጭምር ይማራሉ"

-"ማንም ሰዉ በጎ ነገር ማድረግ ግዴታዉ ነዉ"

-"በት/ቤቱ ለ146 ሰራተኞች የስራ እድል ተፈጥሯል"

-"የእዉነት ነዋሪዎች ከሆንን ክርስቶስን ነዉ የምንመስለዉ"

-"በአሁኑ ሰአት 2262 ተማሪዎች በአካዳሚዉ ይማራሉ"

-"60 መነኮሳት በቦታዉ ይገኛሉ"

-"ረዳት ያጡ ልጆችን እናግዛለን"

-"የምንሰራዉ ስራ ለትርፍ ስላልሆነ ለእለት የምንበላዉ ምግብ እስከ መቸገር የምንደርስባቸዉ ጊዜያት አሉ።"

-"26.6 ሚሊዮን ብር እዳ አለብን"

እማሆይ ፅጌ ማርያም የሚሰሩትን በጎ ስራ ለማገዝ

ንግድ ባንክ- 1000184770338

አዋሽ ባንክ- 013200109509100

ደብረ በረከት አቡነ ተ/ሀይማኖትና ቅ/ኡራኤል የእናቶች አንድነት ገዳም።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abextube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category