Skillmart International College

Skillmart International College

Share

Skillmart International College is fully Accredited higher education institution located in Ethiopia

06/07/2025

የስኪልማርት አካዳሚ የ2017 ዓም የኬጂ-3 ተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት

05/06/2025

እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉን የሠላም፣ የፍቅርና የደስታ ያድርግልን።
ኢድ ሙባረክ!

ስኪልማርት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ

18/01/2025

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!

Photos from Skillmart International College's post 06/01/2025

መልካም የገና በዓል!
Merry Christmas!

Photos from Skillmart International College's post 22/12/2024

ስኪልማርት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ባህርዳር ካምፓስ ተማሪዎቹን አስመረቀ!
ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓ.ም || 21st December 2024
***

ስኪልማርት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በባህርዳር ካምፓሱ በድህረ-ምረቃ (ማስተርስ) መርሐግብር በፕሮጀክት ማኔጅመንት፣ አናላይሲስና ኢቫልዌሽን (Project Management, Analysis and Evaluation_ PMAE) እንዲሁም በቢዝነስ አስተዳደር (MBA) የትምህርት መስኮች ሲያስተምራቸው የቆያቸውን ከ250 በላይ ተማሪዎቹን ኮሌጁ ከተመሠረተ ጊዜ አንስቶ ለ4ኛ ጊዜ እንዲሁም በካምፓሱ ታሪክ ለ2ኛ ጊዜ በባህር ዳር ከተማ፣ በአማራ ክልል ምክር ቤት አዳራሽ ቅዳሜ ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓም አስመርቋል።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የስኪልማርት ትምህርት ልማት አክስዮን ማህበር የቦርድ አመራር፣ የኮሌጁ መምህራንና ሰራተኞች፣ የተመራቂ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በመርሐ-ግብሩ ላይ በኮሌጁ የካምፓሱ ዲን የሆኑት አቶ ምኒልክ ግዛቸው፣ የአክስዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ በቀለ ምንዳ እና የማህበሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ከማል ስዒድ ለተመራቂዎች እና ለተመራቂ ቤተሰቦች ባስተላለፉት መልዕክት የዕለቱ ፕሮግራም በይፋ ተጀምሮ በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

የፕሮግራሙ የክብር እንግዶች እና የተቋሙ አመራሮች በዕለቱ የምረቃ ስነስርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ምሩቃኑ በየዘርፋቸው ያለውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ክፍተት ከማጥበብ ባሻገር ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ እና በእውቀት በመምራት ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ አደራቸውን ገልጸዋል።




Telegram: https://t.me/skillmartInternationalcollege
https://t.me/skillmartbahirdar
Facebook: https://www.facebook.com/

24/11/2024

Class of 2024

Photos from Skillmart International College's post 18/11/2024



ስኪልማርት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በአዲስአበባ መገናኛ አደባባይ ካምፓሱ በድህረ-ምረቃ (ማስተርስ) መርሐግብር በፕሮጀክት ማኔጅመንት፣ አናላይሲስና ኢቫልዌሽን (Project Management, Analysis and Evaluation_ PMAE) እንዲሁም በአካውንቲንግና ፋይናንስ (Accounting and Finance) የትምህርት መስኮች ሲያስተምራቸው የቆያቸውን ተማሪዎቹን ቦሌ አትላስ አካባቢ በሚገኘው ማግኖሊያ ሆቴል አዳራሽ ቅዳሜ ህዳር 7 ቀን 2017 ዓም አስመርቋል።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የስኪልማርት ትምህርት ልማት አክስዮን ማህበር የቦርድ አመራሮችና አባላት፣ የኮሌጁ መምህራንና ሰራተኞች፣ የተመራቂ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን፣ የአክስዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚና የኮሌጁ ዲን የሆኑት አቶ በቀለ ምንዳ እና የእለቱ የክብር እንግዳ አቶ ተሰማ ገዳ ለተመራቂዎች እና ለተመራቂ ቤተሰቦች ባስተላለፉት መልዕክት የዕለቱ ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።

በፕሮጀክት አመራርና በተለያየ ደረጃ በባለሙያነት የበርካታ ዓመታት ልምድ ያካበቱት እና በአሁን ሰዓትም የፒ ኤም አይ ኢትዮጵያ ቻፕተር (PMI Ethiopia Chapter) ፕሬዘዳንት እንዲሁም በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ፋውንዴሽን ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የሆኑት የዕለቱ የምረቃ የክብር እንግዳ አቶ ተሰማ ባስተላለፉት መልእክት ምሩቃኑ በሰለጠኑበት ዘርፍ ያለውን የሰው ሀይል ክፍተት ከማጥበብ ባሻገር ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ እና በመምራት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት የሚችሉ እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።




Magnolia https://www.facebook.com/magaddis?mibextid=ZbWKwL

Telegram: https://t.me/skillmartInternationalcollege
Facebook: https://www.facebook.com/

24/09/2024

Bahir Dar Campus

14/09/2024

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ የስኪልማርት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ቤተሰቦች፤

እንኳን ለ1499ኛው የታላቁ ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በዓሉን የአንድነት፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ያድርግልን።


Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Address

(1) Gurdshola, Figa Mazorya (2) Kotebe 1 Fermata
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 12:00