ትምህርተ ሃይማኖት ዘተዋህዶ

ትምህርተ ሃይማኖት ዘተዋህዶ

Share

በዚህ ገፅ ኦርቶዶክሳዊ የዶግማና ቀኖና ትምህርቶች እንዲሁም ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ዘገባዎች ይቀርቡበታል !

04/06/2026

#ሞያተኛ ናችሁ ወይስ እረኛ? #

"እረኛ ያልሆነው፥ በጎቹም የሱ ያልሆኑት ሞያተኛ ግን ተኩላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኩላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።" (ዮሐንስ 10፥12)

ይህንን ጥያቄ ዛሬ በታላቅ ሃዘንና በቁጭት ሆነን በክብር ወንበር ላይ ለተቀመጣችሁት አባቶቻችን እንጠይቃለን። ዛሬ በጎቹ በየአቅጣጫው እየተበተኑ፣ ተኩላው መንጋውን እየበላው ነው። እናንተ ግን የት ናችሁ

እውነተኛ እረኛ፦ በጎቹን በስማቸው ያውቃቸዋል፤ ህመማቸው ያመዋል፣ ዕንባቸው ይገደዋል፤ ከፊት ቀድሞ እየመራ ከተኩላ ይጠብቃቸዋል። አደጋ ሲመጣ ራሱን ጋሻ አድርጎ "እኔን ግደሉኝ፣ በጎቼን ግን አትንኩ" ይላል።

ሞያተኛ ግን፦ በጎቹ የሱ ስላልሆኑ ጥቅሙን እንጂ ህይወታቸውን አይፈልግም። ደሞዝ እና ክብር እስካለ ድረስ ብቻ አብሮ ይቆማል። አደጋና መከራ ሲመጣ ግን ጥቅሙንና ህይወቱን ለማዳን በጎቹን ለተኩላ ጥሎ ይሸሻል።

ዛሬ ክርስቲያኖች ግፍ ሲፈጸምባቸው፣ እናቶች ሲያለቅሱ፣ ቤተክርስቲያን በእሳት ስትጋይ ዝምታን መምረጣችሁ... እረኛነታችሁን ትታችሁ "ሞያተኛ" (ቀጣሪ) መሆናችሁን በተግባር አሳይታችኋል።

ራስን መካድ የታለ?

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፦ "ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር፥ እራሱን ይክደው መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ" (ማቴ. 16፥24) ብሎ ነበር።

እናንተ ግን ራሳችሁን መካድ ቀርቶ፣ የያዛችሁትን ምድራዊ ክብር መተው አቃታችሁ።

ስለ አደራችሁ መታሰርን ፈራችሁ?

ለገነባችሁት ዘመናዊ ህንፃ፣ ለገዛችሁት የቅንጦት መኪና እና ላፈራችሁት ምድራዊ ንብረት ስትሉ ነው ዝምታን የመረጣችሁት?

ለስጋችሁ እና ለንብረታችሁ በመስጋት መንጋውን ለተኩላ አሳልፋችሁ ሰጣችሁ?

ከክርስቶስ መንበር በላይ የንብረታችሁ ፍቅርና የእስራት ፍርሃት ከበለጠባችሁ፣ እባካችሁን ያፈራችሁትን ንብረት፣ የገነባችሁትን ህንፃና የገዛችሁትን መኪና ሁሉ ይዛችሁ፣ ያንን ያልመጠነችሁትን ከባድ አባታዊ ስልጣን መልሱ!

የበጎቹ ዕንባና ደም ሳይጠይቃችሁ በፊት ወደ ፈለጋችሁበት ሂዱ። ቤተክርስቲያን ስለ በጎቹ ነፍሳቸውን አሳልፈው የሚሰጡ፣ እንደ አባቶቻችን እንደነ አቡነ ጴጥሮስ ያሉ የእውነት እረኞችን ትፈልጋለች እንጂ ለቪላና ለመኪና የሚሰሱ ሞያተኞችን አትሻም።

አባቶቻችን ሆይ!

"ሞያተኛ" መሆናችሁ ይብቃና እውነተኛ "እረኛ" መሆናችሁን በተግባር አሳዩን። ካልሆነ ግን መንገዱን ልቀቁ፤ እረኛ የሌለው በግ መሆን ሰለቸን!

# #ቤተክርስቲያን #ፍትህ

04/06/2026

📌
ሞትን የናቁት የሰማዕታት ገድል፡ ከምድራዊ ስቃይ ወደ ሰማያዊ ክብር!

ለመሆኑ የጥንቶቹ ክርስቲያኖች ምን ዓይነት ልብ ነበራቸው?
በማያምኑና ጨካኞች በነበሩ ነገሥታት ዘመን ታላቅ ስደት ሲታወጅ፣ አማኞች በፍርሃት አልተሸሸጉም። እንዲያውም አንዱ ሌላውን እየጠራ "ለክርስቶስ የምንሞትበት ቀን ዛሬ ነው!" በማለት ለሰማዕትነት ይሽቀዳደሙ ነበር። ልክ ወደ ሰርግ ቤት እንደሚሄድ ሰው በደስታ ወደ አደባባይ ይወጡ ነበር። ይህንን ያደረጉት ግን ለምን ነበር? መልሱ አንድ ብቻ ነው—በሰማይ የሚጠብቃቸውን፣ መቼም የማይጠፋውን የክብር አክሊል ስላዩ ነው!

📖 መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

ይህ የሰማዕታት ወኔ መሠረቱ የጌታችን ሕያው ቃል ነበር፦

ጌታችን በፍርሃት ለተሸበበው ልባችን እንዲህ ይላል፡- "ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።" (ማቴ. 10፥28)

በሰው ፊት ስለመመስከርም ሲያስጠነቅቅ፡- "በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ፤ ... ከእኔ ይልቅ የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።" (ማቴ. 10፥33-37) ብሎናል።

"እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ" (ራእይ 2፥10) የሚለው ቃል የሰማዕታት የልብ ስንቃቸው ነበር።

📜 ከገድላትና ከቤተክርስቲያን ታሪክ

የቅዱሳን ገድላት እንደሚነግሩን፣ ክርስቲያኖች ለአንበሶች መኖ ለመሆን ወደ መድረክ ሲገቡ በደስታና በዝማሬ ነበር።

ቅዱስ አግናጥዮስ፦ ለአንበሶች ሊሰጥ ሲወሰድ፣ ምእመናን ሊያስጥሉት ቢሞክሩም እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፡- "የክርስቶስ ንጹሕ ስንዴ እንድሆን በአንበሶች ጥርስ ልፈጨው ይገባኛል። እባካችሁ አትከልክሉኝ፣ እኔ የሰማዩን ክብር ናፍቃለሁ" በማለት ለሞት ተሽቀዳደመ።

ቅዱስ ፖሊካርፐስ፦ "ክርስቶስን ካድና ከእሳት ትድናለህ" ሲሉት፡- "ለ86 ዓመታት አገልግለኝ አንዳች ክፉ አላደረገብኝም፤ ታዲያ እንዴት አድርጌ ያዳነኝን ንጉሤን እክዳለሁ?" ብሎ በደስታ ወደ እሳቱ ገባ።

በገድለ ሰማዕታት ላይ የምናነባቸው እነ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ቅዱስ ቂርቆስና እያሉጣ መከራው በበዛ ቁጥር "እኔም ክርስቲያን ነኝ!" እያሉ ራሳቸውን አሳልፈው ይሰጡ ነበር።

💡 የዛሬዎቹ ክርስቲያኖች ለምን እንዚ ደንታ ቢሶች ሆንን

የጥንቶቹ ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ሕይወታቸውን ሲሰጡ፣ እኛ የዛሬዎቹ ክርስቲያኖች ግን ስለ ሃይማኖታችን ለመመስከር፣ እውነትን ለመናገርና ጥፋትን ለመቃወም ለምን እንዲህ ፈሪዎች ሆንን?

ዛሬ በዓይናችን እያየን ክርስቲያኖች ሲገደሉ፣ አብያተክርስቲያናት በእሳት ሲቃጠሉና ሲፈራርሱ አንድ ቃል እንኳ የማንተነፍስ፣ በዝምታ የምንመለከት ስንት ክርስቲያኖች አለን! ለምን መሰላችሁ? ፈሪዎች ስለሆንን ነው! እውነተኛው እምነት በውስጣችን ስለጎደለ ነው!

ልባችን ከሰማያዊው ክብር ይልቅ በምድራዊ ጥቅምና በጊዜያዊ ምቾት ተጠምዷል። ሰውን ከመውቀስ ይልቅ እግዚአብሔርን ማሳዘን ቀሎናል፤ ለሆዳችንና ለነጻነታችን ስንል እውነትን እየሸሸግን ነው። እነርሱ ሰማይን አይተው ምድርን ናቁ፤ እኛ ግን ምድርን አይተን ሰማይን ረሳን። ይህ ፍርሃታችንና ዝምታችን ከእውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ የሚጠበቅ አይደለም።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው፡-
"የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ሊገለጥ ካለው ከእኛ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢነጻጸር ምንም እንዳይደለ አስባለሁ።" (ሮሜ 8፥18)

የሰማዕታት እምነትና ያ የድፍረት መንፈስ ዛሬ ለእኛም ይስጠን

04/06/2026
03/06/2026

ማነው አዚም ያደረገባችሁ 🙄

03/06/2026

መፍትሔ አምጡ

ብዙ ሰው ወሬ ሲያመላልስ ነው የሚታየው እንዲህ ማድረግ አለብን ብሎ የመፍትሔ ሀሳብ ሲያመጣ አይታይም
በአስቸጋሪ እና ስጋት ባለባቸው ሁኔታዎች ውስጥ፣ ምዕመናን እና የሃይማኖት ተቋማት እራሳቸውን እና አካባቢያቸውን ለመጠበቅ እንዲሁም ሰላምን ለማስፈን ሊያደርጓቸው የሚችሏቸውን አንዳንድ ገንቢ እና ሰላማዊ መንገዶች ማሰብ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡

1. የውስጥ ትስስርን እና የንቃት ስርዓትን ማጠናከር

የመረጃ ልውውጥ መስመር መፍጠር፦ በየአካባቢው ባሉ አብያተ ክርስቲያናት እና ምዕመናን መካከል ፈጣን እና አስተማማኝ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት መዘርጋት። ስጋቶች ወይም ያልተለመዱ እንቅስቃሴዎች ሲታዩ ቀድሞ ለመደጋገፍና ጥንቃቄ ለማድረግ ይረዳል።

የሰላም ጥበቃ ኮሚቴዎች፦ በአጥቢያ ደረጃ ወጣቶችን እና የሀገር ሽማግሌዎችን ያቀፉ፣ አካባቢን በንቃት የሚከታተሉ ነገር ግን ከማንኛውም ሁከት የጸዱ የቅንጅት ቡድኖችን ማቋቋም።

2. ህጋዊ እና ሰላማዊ ተሟጋችነትን (Advocacy) መቀጠል

ማስረጃዎችን በስርዓት መዝግብ፦ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፣ የደረሱ ጉዳቶችን እና የደህንነት ስጋቶችን በግልጽ፣ በምስል፣ በቪዲዮ ወይም በጽሑፍ የተደገፈ መረጃ (Documentation) አደራጅቶ መያዝ። ይህም ለህጋዊ አካላትም ሆነ ለአለም አቀፍ ተቋማት አቤቱታ ለማቅረብ ጠቃሚ ነው።

የጋራ ድምጽ መሆን፦ ከተለያዩ የክርስቲያን እምነት ተቋማት (ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ ወንጌላውያን) የተውጣጡ መሪዎች በጋራ በመሆን ጠንካራ እና የተደራጀ ድምጽ ለመንግስት እና ለዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማቅረብ።

3. ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር ውይይት እና ትብብር መፍጠር

የአካባቢ ግንኙነትን ማጠናከር፦ ጥቃቶች የሚፈጸሙት በሁሉም የሌላ እምነት ተከታዮች ሳይሆን በጥቂት አክራሪ ወይም ጥቅመኛ አካላት ሊሆን ስለሚችል፣ በአካባቢው ካሉ የሌላ እምነት መሪዎችና ሰላም ወዳድ ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ የሰላም መድረኮችን መፍጠር።

የጋራ ደህንነት ምክር ቤት፦ በአካባቢ ደረጃ ያሉ የሃይማኖት መሪዎች በጋራ በመሆን የጥፋት ኃይሎችን በጋራ የሚያወግዙበትና አካባቢያቸውን በጋራ የሚጠብቁበትን መንገድ መፈለግ።

4. የህግ እና የሰብዓዊ መብት ተቋማትን መጠቀም

ህጋዊ ክሶችን መመስረት፦ ምንም እንኳን የመንግስት ምላሽ አዝጋሚ ቢሆንም፣ በህግ አግባብ ጥፋተኞችን ተጠያቂ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አለማቋረጥ።

ለገለልተኛ ተቋማት ማመልከት፦ እንደ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና መሰል የሀገር ውስጥና የአለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሉትና ጫና እንዲፈጥሩ ሪፖርቶችን ማቅረብ።

02/06/2026

// ስልጣን ተሰጠኝ //

በማቴዎስ ወንጌል 28፥18 ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፦ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል” ሲል ምን ማለቱ ነው? ይህ ሥልጣንስ እንዴት ተሰጠው? ሰጪውስ ማን ነው?

ለእነዚህ ጥያቄዎች በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትና ምስጢረ ሥላሴ አስተምህሮ መሠረት ጥልቅ የሆነ ምላሽ አለን።

የሥላሴ ዘላለማዊ ምክርና ፈቃድ (መለኮታዊ አንድነት)

አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ በባሕርይ፣ በሥልጣን፣ በፈቃድና በመለኮት አንድ አምላክ ናቸው። የሰው ልጅ በበደለና ከገነት በወጣ ጊዜ፣ ሰውን ለማዳን በሥላሴ ዘንድ “መለኮታዊ ምክር” ተደረገ። በዚህም ምክር መሠረት፦
ወልድ በፈቃዱ (በአብና በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ) ሰው ለመሆን ወረደ፣
መንፈስ ቅዱስ ሥጋን ቀደሰ።

< እስመ በፈቃዱ ወበስምረተ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ መጽአ ወአድኃነነ> ይላል

ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ለብሶ ወደ ምድር የመጣው ከሥላሴ አሃዳዊ ሥልጣንና ምክር ተለይቶ ሳይሆን፣ የሥላሴን ፈቃድ ለመፈጸም ሥልጣን ተቀብሎና ተልኮ ነው።

“ሥልጣን ተሰጠኝ” ማለቱ ምን ማለት ነው?

ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹምም ሰው (በተዋሕዶ) ነው። ስለዚህ “ሥልጣን ተሰጠኝ” ማለቱ በሁለት መንገድ ይተረጎማል፦

በሰውነቱ (በትስብዕቱ)፦ ቀድሞ በሰውነቱ ሕማምን፣ ሞትንና ውርደትን የተቀበለው ክርስቶስ፣ አሁን በትንሣኤው ሞትን ድል አድርጎ በሰውነቱ የከበረውን የሰማይና የምድር ሥልጣን ገንዘብ ማድረጉን ለማሳየት ነው።

በመለኮቱ (በመለኮታዊ ተልዕኮው)፦ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባለው አንድነት፣ ዓለምን ለማዳን የተሰጠውን መለኮታዊ አደራና ሥልጣን በተግባር መግለጡን ያሳያል።

📖 የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነት (ከኦርቶዶክሳውያን መጻሕፍት)

ይህ የሥልጣን መቀበል እና የሥላሴ ምክር በብሉይም በሐዲስም መጻሕፍት ላይ በግልጽ ተጽፏል፦

“መንግሥትና ክብር ሥልጣንም ተሰጠው፥ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ፤ ሥልጣኑ አያልፍም፥ መንግሥቱም አይጠፋም።”

— (ትንቢተ ዳንኤል 7፥14)

(ይህ ነቢዩ ዳንኤል ክርስቶስ ሥልጣንን ተቀብሎ ሰማይና ምድርን እንደሚገዛ አስቀድሞ ያየው ድንቅ ትንቢት ነው።)

“እግዚአብሔር ቀባኝ... ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ ልኮኛል።”

— (ትንቢተ ኢሳይያስ 61፥1)

(ቅቡዕ መሆኑና መላኩ ከሥላሴ የተሰጠውን ሥልጣን ያሳያል።)

“እኔ ከራሴ አልመጣሁም ነገር ግን እርሱ ላከኝ።”

— (የዮሐንስ ወንጌል 7፥29)

“አብ ወልድን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።”

— (የዮሐንስ ወንጌል 3፥35)

🕊️ ከቅዳሴና ከሃይማኖተ አበው ምስክርነት

በቅዱስ ያሬድ ዜማዎችና በቅዳሴያችን ላይ እንደሚነገረው፣ ወልድ ሥጋ ለብሶ የመጣው በሥላሴ አንድነትና ፈቃድ ነው።

“አብ ፈቀደ ወልድ ወረደ መንፈስ ቅዱስ ቀደሰ” (አብ ፈቀደ፣ ወልድ ወረደ፣ መንፈስ ቅዱስም ሥጋን ቀደሰ)።

ስለዚህ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣው በራሱ ፈቃድ ብቻ ሳይሆን፣ በአንድነቱና በሥልጣኑ አንድ በሆነው በእግዚአብሔር (በሥላሴ) ዘላለማዊ ምክር፣ ሙሉ ሥልጣንን ተቀብሎና ተልኮ ነው።

💡 ለማጠቃለል...

ማቴዎስ 28፥18 ላይ የተጠቀሰው ሥልጣን የክርስቶስን ፍጹም አምላክነትና እርሱ የሥላሴ ፈቃድ ፈጻሚ መሆኑን የሚያረጋግጥ

Photos from ትምህርተ ሃይማኖት ዘተዋህዶ's post 28/05/2026

!

“ታሪክን ለትውልድ የማሻገር ተራው የእኔ ነው” በሚል መርህ እየታደሰ ለሚገኘው የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቂያ ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩ ጥሪ ቀረበ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ግንቦት ፲፬/፳፻፲፰ ዓ/ም

በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት የሚገኘው ታሪካዊው የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከተቆረቆረ 130 ዓመታትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ልዩ እና በሥነ ሕንጻ ቅርጹ በልዩ ሁኔታ የተገነባ ድንቅ የሆነ ታሪካዊ ቅርስ ነው።

ግንቦት ፲፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ክብሩ ገብረ ጻድቅ እንደገለጹት ቤተክርስቲያኑ ዕድሳት ሥራ እየተከናወነ ቢገኝም ሥራው ከሚፈልገው ከፍተኛ ገንዘብ አንጻር በቂ የገንዘብ አቅም በማስፈለጉ ከግንቦት ፳፰-፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የበይነ መረብ (የኦንላይን) የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር መታቀዱን ገልጸዋል።

ይህ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በተጓዘባቸው ዓመታት በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ያልተቋረጠ መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ የቆየ ሲሆን በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሠራሽ ምክንያት አደጋ እየተጋረጠበት በቀደሙ አባቶቻችን ጥገና እና እድሳት እየተደረገለት በትውልድ ቅብብሎሽ ዛሬ ላይ ቢደርስም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን፣ በውስጣዊ ግንባታው ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የተከሰተ የውሃ ሥርገት፣ በውጫዊው ገጽታው ላይ የመወየብ እና የመሰንጠቅ አደጋ ያለምንም ብረት እና ተጨማሪ ድጋፍ በተሠራው ልዩ “የእሳተ ከላ” (የቀይ ሸክላ ኮርኒስ) ግንባታው የመሰንጠቅና የመሸሽ ሁኔታ መፈጠሩ፣ ከላይ ከጉልላቱ ጀምሮ ዝናብ በማስገባትና የውስጥ ግድግዳዎቹም በመሰነጣጠቃቸው ምክንያት ዕድሳቱ መደረጉን ገልጸዋል።

በመልአከ ገነት እንዳብራሩት የበይነ መረብ (ኦንላይን) መርሐ ግብር ከ250-300 ሚሊየን ብር ገቢ ለማሰባሰብ የታሰበ ሲሆን በዚህ መርሐ ግብር ላይ መላው ሕዝበ ክርስቲያን ቅዱስ ጊዮርጊስ ውለታ በማሰብ እና በስፋት በመሳተፍ በገንዘብ፣ በጉልበትና በአቅርቦት ክርስቲያናዊና ሀገራዊ ኃላፊነቱ እንዲወጣ አሳስበው በሁሉም ባንኮች “1423” አጭር የሒሳብ ቁጥር በመጠቀም ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የመስቀል መልሶ ማስቀመጥ መርሐ ግብርን በተመለከተ የጉልላት ሥራ በመጠናቀቁ እሑድ ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓም ከቅዳሴ ውጭ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት በሚከናወነው ታላቅ የመልሶ ማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን በአካል ተገኝቶ የመስቀል መልሶ ማስቀመጥ ሂደት እንዲሳተፉና ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ዘገባው የኢኦተቤ ቴቪ ነው።

📷ዲ/ን ቅዱስ ጥበቡ

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሠሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍስሓ ወሰላም

🔵@የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን

20/05/2026

ተራዳኢው መልአክ እስራኤልን በምድረበዳ የመራው ጨለማውን እየገፈፈ ሀሩሩን እየጋረደ የመራቸው በሰማይ ሰልፍ ሆኖ ዘንዶውን ድል የነሳው መልአክ ተራዳኢነቱ አይለየን !

07/05/2026

ጠርሴስ / Tarsus

የኪልቅያ ዋና ከተማ የሆነችው ጠርሴስ በሮማ ዘመነ መንግሥት ከፍተኛ የንግድ መዳረሻ የነበረች ከሜዲትራንያን ባሕር በጥቂት ርቀት የምትገኝ ከተማ ናት።

የቤተ ክርስቲያን ምርጥ ዕቃ የተወደደው መምህር ቅዱስ ጳውሎስ የተወለደባት ቦታ ናት።

ለጨለማው ዓለም የክርስቶስን ብርሃን ያበራው ታላቁ ሐዋርያ የተወለደው፣ ያደገው በዚህች ምድር ነው።

የኪልቅያ ጠርሴስ በዚያ ዘመን በ ኢየሩሳሌም የተከሠተውን ክፉ ቀን ለማሳለፍ በየሀገሩ የተበተኑ ብዙ አይሁድ ይኖሩባት ነበር።

ምንም እንኳን በስደት የመጡ ቢሆኑም በጠርሴስ የሚኖሩ አይሁድ ሮማዊ ዜግነት ያገኛሉ። ሮማዊ ዜግነት ቢያገኙም ይሁዲነታቸውን አይለቁምና ለልጆቻቸው በሚኖሩበት አገር ያለውን ጥበብ ከማስተማር በተጨማሪ ይሁዲነታቸውን ጠብቀው የአብርሃም ዘር መሆናቸውን አውቀው እንዲያድጉ ያደርጋሉ።

በዚህ መሠረት የቅዱስ ጳውሎስ ቤተሰቦች የጠርሴስን ጥበብ ድንኳን መስፋትን እና የቤተ አይሁድና ሃይማኖታዊ ትምህርቶች እየተማረ እንዲያድግ አድርገውታል።

ቅዱስ ጳውሎስ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠርሴስን ለቆ የሄደው ወደ ኢየሩሳሌም ሲሆን የብሉይ ኪዳን ትርጓሜ ለማጥናት ወደ ገማልያል ጉባኤ ነው።

በዚያ ሂዶ ከ15 ዓመታት በላይ ብሉይ ኪዳንን በማጥናት ከታወቁ ፈሪሳውያን አንዱ ለመሆን በቅቷል። እጅግ ለሃይማኖቱ ቀናተኛ ያደረገውም ምሁረ ኦሪትነቱና ፈሪሳዊነቱ ነው።

እስጢፋኖስ ሲገደል ተስማምቷል፤ የእስጢፋኖስን ሞት ተከትሎ በየሀገሩ የተበተኑ ምእመናንን ለማሳደድ ነበረ ወደ ደማስቆ እየገባ የነበረው።

በደማስቆ ጎዳናዎች ላይ ተፈልጎ የተገኘው የጠፋው የእግዚአብሔር በግ ቅዱስ ጳውሎስ የተወለደባትን ያደገባትን ምድር በመርገጤ ደስታዬን በልቤ የያዝሁትን ያክል ለእናንተ መግለጥ እንዳልችል ቃላት ሁሉ ዐቅም ስለሚያጡብኝ ነው።

በጨርቁ ድውይ የፈወሰው፣ ያለ እረፍት ወንጌልን የሰበከው፣ አስጨናቂ የሚባሉ መንገዶችን ሁሉ ስለ ክርስቶስ የተመላለሰው ያ ቅዱስ ሰው በዚህች ምድር ተወለደ።

በእውነት ጠርሴስ ከቱርክ ተራሮች ሥር ያለች አንዲት መንደር ብቻ ሳትሆን የቤተ ክርስቲያን ብርሃን የተገለጠባት ታናሽ ሰማይ ናት።

ስለ እስራኤል ተስፋ ሰንሰለት የለበሰው፣ በማልታ (መላጥያ) ደሴት በ እባብ የተነደፈ፣ የ እባቡን መርዝ በሃይማኖቱ ያጠፋ፣ ዓለም በክርስቶስ አምኖ እንዲድን በፍጹም ትጋት የሰበከ ወንጌላዊ ፍጹም የክርስቶስ አገልጋይ እነሆ በዚህች ምድር ተወለደ።

እስከዛሬ ድረስ በዓለም ሁሉ መምህር ነው። የማይሞተው መምህር፤ ሳያቋርጥ የሚሰብከው ትጉህ አገልጋይ ከዚህች ትንሽ መንደር ተገኝቶ ለመላው ዓለም መምህር ሆኖ ተሾመ።

ዛሬ ከተወለደባት መንደር ጥቂት ፈቀቅ ብላ ከምትገኝ መንደር አድረን ወደ ቀጰዶቅያ ጉዞ ጀምረናል።

መኪና ውስጥ እያለን በጉዟችን ላይ በቊስጥንጥንያ ስለተደረጉ ጉባኤያት እና በአንጾኪያ መንበር ስለተሾሙ ቅዱሳን አበው ከወንድሞቻችን (ዲያቆን ያረጋልና ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ) ሰፊ የታሪክ ማስረጃዎች የተካተቱበት ትምህርት ተሰጥቶናል።

ከሊቃውንቱ ጋር ወደ ሊቃውንቱ ምድር ወደ ቀጰዶቅያ ለመድረስ 15 ደቂቃ ብቻ ቀርቶናል።

እነ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ ጎርጎርዮስ ዘ እንዚናዙ ደሞ በዚህ ተሰይመው ይጠብቁናል።

እነዚያ ከዋክብት ደምቀው በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ላይ ያበሩባት የተጋድሎ ምድር እንደምናት?

ደርሰናል!

ስምዓኮነ መልአከ / Simakone Melak

07/05/2026

ሲኖዶሱ እረኝነቱን ማርጋግጥ የሚችለው በጎሣ ሲመት፣ በሕንጻ ግንባታ፣ በቦታ ቅያሪና በበጀት ውይይት ሰለማይሆን የሚከተሉትን 5 +1 አንገብጋቢ ጉዳይ ያንሳ የሚል መልእክት አለኝ፦

(1) መንግሥታዊ እና ሥርዓታዊ የክርስቲያን እልቂት፣ መፈናቅል፣ ፍትሕ መነፈግ፣ በእቅድ መደኸየት እና በአጠቃላይ የኦርቶዶካስውያን ዘር ማጥፋት ለማስቆም ምን ማድረግ አለብን?

(2) በየጎሣው ፖለቲካው የሚፈጥራቸው አባቶች፣ ሲኖዶሶች፣ ቤተ ክህነቶች፣ ቅባት፣ የመናፍቃን ጥቃትን ለመከላከል ምን ማድረግ አለብን?

(3) ባንኮችን ያጨናነቀው የቤተ ክርስቲያን ገንዘብ እንዴት ለገጠር፣ ለገዳማት፣ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ይዋል?

(4) በዘመድ አዝማድ፣ በፖለቲካ ሥራትኝነት፣ በሙስና የተደራጀው ከአገር ውስጥ እስከ ውጭ የተንሰራፋዊ ኢክርስቲያናዊ የአስተዳድር ብልሽት እንዴት ይስተካከል?

(5) ትብብርን የሚቃረን የብልጽግና መንግሥት ሁለገብ ጣልቃ ገብነት እንዴት የቁም?

6) በተጨማሪም ሀብት ያላቸው ጳጳሳት ሀብታቸውን አሳውቀው ባስቸኳይ እንዲያስረክቡ ! ከተቻለ ከየት እንዳመጡ እንዲናገሩ ! (ደመቀ መኮንን እንደጨመረው)
Fantahun Wakie

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Addis Ababa