Tewahido

Tewahido

Share

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች የ?

28/08/2022

ሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ
➱ "ወከዓዉ ደሞሙ///ደማቸውን አፈሰሱ"
✝️ደማቸውን አፈሰሱ የተባሉት እናማን ናቸው ? ለምን ይሆን ደማቸውን ያፈሰሱት?
✥" ለእናንተም ለወዳጆቼ እላችኋለሁ፥ ሥጋን የሚገድሉትን በኋላም አንድ ስንኳ የሚበልጥ ሊያደርጉ የማይችሉትን አትፍሩ። እኔ ግን የምትፈሩትን አሳያችኋለሁ፤ ከገደለ በኋላ ወደ ገሃነም ለመጣል ሥልጣን ያለውን ፍሩ። አዎን እላችኋለሁ፥ እርሱን ፍሩ።" ሉቃ ፲፪÷፬
ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ ዘሮንቶስ ይባላል። እናቱም ቴዎብስታ ትባላለች የዘር ሐረግዋም ከፍልስጥኤም ወገን ነው ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓም/// በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን ተወለደ የተወለደባትም በሀገረ ልዳ ቀጰዶቅያ በተባለ ስፍራ ነው።
➱የተወለደው ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓ.ም
➱የአባት ስም አንስታቴዎስ (ዘሮንጦስ)
➱የእናት ስም ቴዎብስታ
➱የትውልድ ሀገር ቀጰዶቂያ
➱በዓለ ንግሥ(ዕረፍቱ)- ሚያዚያ ፳፫ ቀን
✝️የቤይሩት (የሊባኖስ) ሰዎች ደራጎን የተባለ ዘንዶ እያመልኩ ሴት ልጃቸውን ይገብሩለት ነበር፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም ቤይሩታዊቷን ወጣት አዳናት ደራጎኑን በበትረ መስቀሉ ድል በማድረግ ገድሎታል፡፡በፋርስ (በኢራን) ዱድያኖስ የተባለ ንጉሥ ሰባ ነገሥታትን እየሰበሰበ ለሰባ ጣዖታት ሲሰግድና ሲያሰግድ ይኖር ነበር፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትም እንደ ኤልያስ ለእምነቱ ቀንቶ ንጉሡን መገሰጽ ጀመረ፡፡
ለሰባት ዓመታት ያህል ልዩ ልዩ መከራን እየተቀበለ በጽኑዕ ተጋድሎ ከኖረ በኋላ ሚያዝያ ፳፫ ቀን በ፳፯ ዓመቱ ሰማዕትነትን ተቀብሎ አርፏል፡፡
⛪️ቅዱስ ኤፍሬም በደረሰው በሐሙስ ውዳሴ ማርያም እንደተናገረው "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዛ ዓለም ወከዓዉ ደሞሙ በእንተ እግዚአብሔር ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግሥተ ሰማያት"/// “ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ፡፡

✝️"ሰዓል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሀረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብዓ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንስአ ሙታን አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ" #መሐረነ አብ

✝️" ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን?፤ ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።" ሮሜ ፰÷፴፭
✝️ ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንድ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ ፤ ከዚህም በኃላ እንደመጭመቂያ ሆኖ ከተሰራ የስቃይ መሳሪያ (መንኰራኩር/ወፍጮ) ላይ አወጡት ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት እንዲጨምቁት አዘዘ፤ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ እንዲሁ አደረጉበት ነፍሱ ከስጋው ተለየች የሰማእቱን ሰጋ አቃጠሉት ፈጩት አመድም ሆነ በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በነፋስ ዘሩት።

✝️ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ነው ወታደሮቹ የታዘዙትን ፈጽመው ተመለሱ። ያንጊዜም መብረቅ ነጎድጓድ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ ምድርም ከመሰረቷ እስክትናወጽ ድረስ ከሰማይ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ መላእክትን አስከትሎ በብሩ ደመና ወረደ በተራራውም ላይ ተቀመጠ አራቱን የምድር ነፋሳት የሰማእቱን ስጋ እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው ከሞትም አስነሳው ኃይሉን አሳደረበት ባርኮትም ወደ ሰማይ አረገ፤ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየሮጠ ወታደሮቹን ተከተላቸው ወንድሞቼ ቆዩኝ ከናንተ ጋር ልሂድ እያለ ተጣራ የነዚህ የወታደሮች ቁጥር አራት ነው ስማቸው ህልቶን፤አግሎሲስ፤ሶሪስና አስፎሪስ ነው፤ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፤ በኋላም በሰማእትነት ሞተዋል፤

➱ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ምዕራፍ ፮ ፤ ፲፭-፲፰

ከሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት ይክፈለን!!!

✥ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✥
ዲ/ን ሙሉቀን ግርማ
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
ለበለጠ መረጃ👉 "ዲያቆን ሙሉቀን ግርማ" ፔጁን ላይክ በማድረግ እለት እለት የቅዱሳኑን፣የጻድቃን፣የሰማዕታትን፣የነብያትን፣የሐዋርያትን ገድል ተአምራት ይከታተላሉ እንዲሁም ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ እንወያይ መልዕክት ይላኩ......ስለጎበኙን እግዚአብሔር አምላክ በረድኤት ይጎብኝልን፤ የእመቤታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት፤የጻድቃን የሰማዕታት ተራዳኝነት አይለየን አሜን።✟

29/06/2022

ማርያም

29/06/2022

እሷን እና ልጇን ከፊት ያስቀደመ ካሰበበት ይደርሳል
ለሁላችንም ድጋፏ አይለየን 🙏🙏

29/06/2022

መላኩ ዑራኤል

⛪️"ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ" ዕዝ ሱቱ ፪÷፩

✥ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቀ መላእክት አንዱ ነው። መላእክት በስማቸው ቅጥያ ኤል የሚል ቃል አለ ይኸውም እግዚአብሔር ማለት ነው። ዑራኤል ማለት የብርሀን ጌታ፣ የብርሀን አምላክ ማለት ሲሆን "ዑር" ማለት ብርሃን፤ "ኤል" ማለትም እግዚአብሔር ማለት ነው።

✔️ቅዱስ ዑራኤል በመባርቅትና በነጎድጓድ የተሾመ መልአክ ነው። መ.ሄኖክ ፮፥፪

✥ የሰማይን ሚስጥር ለሄኖክ እውቀትን የገለጸለት መልአክ ነው። የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መ.ሄኖክ 28፥13

✥ ቅዱስ ዑራኤል ልቡናን የሚያበራ እውቀትን የሚገልጽ ርሑሩህ መልአክ ነው። ቅዱስ ዑራኤል ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋአ ልቡናን አጠጥቶት ሰማያዊ ሚስጥራትን ገልፆለታል። ነብዩ እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸውን መጻሕፍት ደርሷል። በሰዓታቱም "ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ኤልያስ ወኤልሳዕ ነቢያተ እስራኤል ወምስለ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዓ ልቡና ዘአስተዮ ዑርኤል፡፡"/// "ነይ ወደ እኛ ድንግል ሆይ ከእስራኤል ነብያት ከኤልያስና ከኤልሳ እንዲሁም ዑራኤል ጽዋ ልቡናን ካጠጣው ከእዝራ ሱቱኤል ጋር።"

✥ ሌላኛው ቅዱስ ዑራኤል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእጸ መስቀል ላይ በቀራንዮ በአምስቱ ቅንዋት( ሳዶር፣አላዶር፣ዳናት፣አዴራ፣ሮዳስ) ተቸንክሮ ሳለ ይህ ብርሃናዊ መልአክ ነው ከጎኑ የክርስቶስን ደም በጽዋ ቀድቶ በዓለም ሁሉ ረጭቶታል።

✥" እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ። ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ፥ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው። እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ። ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ።" በዚህ የጭንቅ ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እየተራዳ መንገድን እየመራት በብርሃን ወደ ሀገረ ግብፅ ቀጥሎም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም አስራት ወደ ሆነቻት ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራት መጥቷል። ማቴ 2÷13-15

✥ " ሰላም ለአእጋሪከ ወለሰኰናከ እለ ሖራ። ፍና ተራድኦ ግሙራ። ዑራኤል ለድንግል ፍኖተ ምድረ ግብፅ አመራ። ሠለስተ ዓመተ በስደት እንዘ ታስቅቁ ነቢራ። ከመ በፍስሓ ትትመየጥ ለበዊእ ሀገራ።"///" ዑራኤል ሆይ ለእርዳታ ፈጽመው ለሚፈጥኑት እግሮችህና ሰኰናህ ሰላም እላለሁ። ዑራኤል ሆይ በስደት ወራት ለድንግል የምድረ ግብፅን መንገድ ያመለከትካት አንተ ነህ። ሦስት ዓመት እያለቀሰችና እያዘነች በስደት ከቆየች በኋላ ተመልሳ ወደ ሀገሯ እንድትገባ የደስታ የምስራች ያበሰርካት አንተ ነህና።" መልክአ ዑራኤል

✥ ሌላው የእውቀትን ብርሃን የገለጸላቸው የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ለሊቁ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው። እኚም አባታችን በመልአኩ ተራዳኢነት ብዙ ድርሰቶችን ደርሰዋል። እመቤታችንም በምልጃዋ ቅዱስ ዑራኤል የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ዘንድ አድርጋለች። አባ ጊዮርጊስ እመቤታችንን ይወዷት ስለነበረ አርጋኖን ሌሎችንም ደርሰዋል።

ዑራኤል ማለት የብርሃን ጌታ ማለት ነው

✔️ ቅዱስ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው። እርሱም መባርቅትን ለጥጋብና ለበረከት እንዲሁም ነጎድጓድን ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መ.ሄኖክ ፮፥፪

➕ ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል።

🙏🙏🙏
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ዑራኤል/2/
ሰዓል ወጸሊ በእንቲአ ነአዕርግ ፀሎተነ ቅደመ መንበሩ ለመድኃኒዓለም/2/
🙏🙏🙏

ቅዱስ ዑራኤል ሆይ እኛም ተቸግረናልና እንድትረዳን ወደ እኛ ና??? ለዕዝራ ያጠጣኸውን ጽዋ እንሻለን

✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
ለበለጠ መረጃ👉 "ዲያቆን ሙሉቀን ግርማ" ፔጁን ላይክ በማድረግ ዕለት ዕለት የቅዱሳኑን፣የጻድቃን፣የሰማዕታትን፣የነብያትን፣የሐዋርያትን ገድል ተአምራት ይከታተላሉ እንዲሁም ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ እንወያይ መልዕክት ይላኩ......ስለጎበኙን እግዚአብሔር አምላክ በረድኤት ይጎብኝልን፤ የእመቤታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት፤የጻድቃን የሰማዕታት ተራዳኝነት አይለየን አሜን።✟

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Address

Quara
Addis Ababa
0000