ኢትዮጵያዬ-My Ethiopia

ኢትዮጵያዬ-My Ethiopia

Share

Human right

26/09/2022
Photos from ኢትዮጵያዬ-My Ethiopia's post 26/07/2022

😢
አሁንም እዛው ነን
1ኛ
በተኩላ ልመና በእንቃቅላ ፀሎት
በአሳማ ምስክር በዝንጀሮ ችሎት
ፍትሕ አይገኝም ሰው እውነትን ቀብሮት
-

2ኛ
ግፉ ሲትረፈረፍ ሰው ፍትህ ሲርበው
እርካታ ተሰልቦ መከራው ሲቀርበው
ውሸት አቅም ሲያገኝ ሀቅ ሲመነምን
ጠብታ ይጠፋል ሰው ከጅብ ሲለምን
_

✍️ አብዱል ከሪም የእናቱ ልጅ
😓

የወሎ ድምፅ/Voice Of Wollo 17/07/2022

የወሎ ድምፅ/Voice Of Wollo በዚህ የቴሌግራም ቻናል ትክክለኛና ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ በወሎ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁነቶችንን እናቀርባለን። የቻናላችን አባል ይሁኑ

24/06/2022

ይህ ቁጭት ምን አርግዞ
ምን እንደሚወልድ
እናየዋለን

20/06/2022

መደበቂያ ያደረግነው መስጂዳችንን ነበር ግን እዛም ገብተው 46 ሰዎችን ገደሉብንየኔን ብቻ 12 ቤተሰቦች ገደሉብኝ አሁን እኔንም ቢገድሉኝ ኑሮ እያልኩ እየተጸጸትኩ ነው አላህ ለምን አተረፈኝ!? ከዚህ በኋላ ምን ቀረኝ?😭

#ወለጋ😥

19/06/2022

ንፁሀን ሰው መግደልን የሚፈቅድ ሀይማኖት
በንፁሀን ሞት ክብር ሞገስ ጀግንነት የሚጨምር ብሄር

በዳይ ከበደሉ ንፁህ ሆነ
ንፁህ ነብስን ገዳይ ፃድቃን ሆን
ወንጀለኛም አይጠየቅም ወንጀል መስራትም
መግደል መዝረፍ ማሰቃየት
የተከበረች የሰውን ነፍስ ማጥፋት ያውም ባሰቃቂ ሁኔታ
የጀግንነት የክብር መገለጫ ሆነ
ምክንያቱም የሆነ ብሄር የሆነ ሃይማኖት ግሩፕ አባል ነህ ምንም ወንጀል
ብሰራ በኩራት መኖር ትችላለህ።
ወለጋ???
ጎንደር???
ሞጣ???

Photos from ኢትዮጵያዬ-My Ethiopia's post 12/06/2022

ወንዶች 86%
ሴቶች 14%..... ሴቶች ምነው?????

በተረፈ አድስ አበቤዎች እናመሰግናለን።
ሌሎች ግን...

12/06/2022

በፕሮግራሙ ዙሪያ ጠቅለል ያሉ ነጥቦች‼
============================
(በተሰባሰበው ገንዘብ የኛው የሆነ ትልቅ ተቋምና አዳራሽ ብንገነባበትስ?)
||

✍ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይካሄዳል ተብሎ ታቅዶ የነበረው ዓለም አቀፍ የቁርኣን ውድድር ሳይካሄድ ቀርቷል። በዚህ ዙሪያ መነሳት ካለባቸው ነጥቦች መካከል ብዬ የማስባቸውን ላካፍላችሁ ወደድኩ።


①) ለፕሮግራሙ አለመሳካት ሰበቦቹ ራሳቸው የፕሮግራሙ አዘጋጆች መሆናቸው ታውቋል። የተሳሳቱት ጥቃቅን የሚባል ስህተት ሳይሆን ቀድሞ ማጠናቀቅ የነበረባቸውን መሠረታዊ ነገር ነው። የሚያሳዝነው ደግሞ አለመሳካቱን ቢያንስ ትናንት እንኳ ማሳወቅ አለመቻላቸው ነው። ቀድመው ቢያሳውቁ ኖሮ በአንፃሩ ብዙዎችን ከልፋት መታደግ ይቻል ነበር። እነርሱ ተሳስተው ታላላቆችንም አሳስተዋል። መሠረታዊ ሂደቶችን ያጠናቀቁ መስለው፤ ሌሎችም by default «ይሄንማ ሳያሟሉ አይቀርም!» በሚል እምነት መድረክ ላይና ሚዲያ ላይ ፕሮግራሙን አስተዋውቀዋል፤ አስተዋውቀናል። ትልቅ ፕሮግራም ብቻ ማለም በቂ አይደለም፤ ትልቅ ዝግጅትም እንደሚጠይቅ ማወቅ ያስፈልጋል። ካላወቁ የሚያውቅን መጠየቅና አጋር መፈለግ ይቻላል።
°
②) እንኳን እንደዚህ ትልቅ ፕሮግራም ማዘጋጀት ትንሽ ፕሮግራም ማዘጋጀት ምን ያክል ትልቅ ትግል እንደሚያስፈልግ አዘጋጆቹ ሰዎችና አላህ ብቻ ያውቁታል። እኛ ካምፓስ ስንማር ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች «የእንኳን ደህና መጣችሁ!» ፕሮግራም ለማዘጋጀትና ከተመራቂዎች ደግም የሽኝት ፕሮግራም ለማዘጋጀት ስንት ፍዳ እንደምንበላ በተጨባጭ አውቃለሁ። ቦታ ማመቻቸት፣ ኡስታዞችንና ተጋባዥ እንግዶችን ማመቻቸት፣ ለምሳና ለሻይ ቡና ወጪ ገቢ ማሰባሰብ፣ ተሸላሚዎች ካሉ ለነርሱ ማፈላለግ፣ ጥሪውን ለተማሪዎች ማድረስ… ብቻ እንቅልፍ እንደት እንደሚነሳ አውቃለሁ። ከአላህ እገዛ ቀጥሎ በዙሪያችን የሚያግዙን ልምዱ ያላቸው ሰዎች ባይኖሩ ኖሮ እንደማናሳካው የታዘብኩባቸው ብዙ አጋጣሚዎች ነበሩ። ጭራሽ ሃገር አቀፍ ፕሮግራም ሲሆን ደግሞ አስቡት! ቢሆንም ግን መሠረታዊ ነገርን ሳያሟሉ ለጥሪ መቸኮል አያስፈልግም። ምነው ትኬት እንደት እንደሚቆረጥ ያመቻቹበትን ዘዴና ልፋት ለቦታው ተጠቅመውት በነበር!
°
③) ዙሮ ዙሮ ጥፋት ተከስቷል። እነዚህን ሰዎች አሁን ላይ ብንቀጣቸው፣ ብንገርፋቸው… ያጠፉትን ጥፋት ማካካስ አንችልም። ከክፍለ ሃገር ድረስ የለፉትንና ልባቸው የተሰበሩትን ሁሉ መጠገን አንችልም። የሆነው ሆኗልና አሁን መሄድ ያለብን ወደ መፍትሄው ነው። ዳሜጁ ተከስቷል፤ መሥራት ያለብን damage control ላይ ነው። መወቃቀሱ መፍትሄ የለውምና!

°
④) እኛ የሻነው ሳይሆን አላህ የሻው ሆኗል።
እንዲህ ብሎን የለ፦
(وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ ۚ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا حَكِيمًا)

«አላህም ካልሻ በስተቀር አትሹም፡፡ አላህ ዐዋቂ ጥበበኛ ነውና፡፡»

[አል-ኢንሳን: 30]

(وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ)

«የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡»

[አ-ት'ተክዊር: 29]

√ ደግሞ ይህ የሆነው እኛ ለማናውቀው አላህ ግን ለሚያውቀው የተሻለ ኸይር ነገር ሊሆን ይችላል።
ስቴዲዬም ቢካሄድ ደግሞ እንደባለፈው አንዱ ባርቆብኝ ነው ብሎ ችግር ቢፈጠርና የሰው ህይዎት ቢጠፋስ? በቃ! ለበጎ ነው!

(وَعَسَىٰ أَن تَكْرَهُوا شَيْئًا وَهُوَ خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰ أَن تُحِبُّوا شَيْئًا وَهُوَ شَرٌّ لَّكُمْ

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Address

Addis Ababa