የአንገር ጉትን ልዩ ዞን ጥያቄ / ANGER Gutin

የአንገር ጉትን ልዩ ዞን ጥያቄ / ANGER Gutin

Share

ለህዝባችን ብቸኛው የሰላም አማራጭ የሚሆነው ራስን በራስ የማተዳደር ህገ መንግስታዊ ጥያቄ ሲመለስ ብቻ ነው?! ወይስ?

25/05/2026

በአንዶዴ ድቾ በተፈጠረው ነገር አዝነናል። መንግስት ለሠላማዊ ንግግሮች ውይይት ለማድረግ መዘጋጀት አለበት።

ህዝቡ ተፈናቅሏል። ከቤት ንብረታቸው ወጥተዋል። ችግሩ ሰፊ ነው። ሁልጊዜ መገዳደል ትክክል አይደለም። ስለአካባቢው ያለውን ተጨባጭ እውነታ ደግሞ መቀበል አስፈላጊ ነው።

በቅርቡ እንኳን ከኦፈታ መ.&4 አሩሲ፣ ወጤ፣ መርካቶ፣ ገራዶና አንዶዴ ህያው ምስክሮች ናቸው። በብዙ ፈተና ውስጥ በመሆናችን ያለውን እውነታ እንኳን ለመመስከር አቅም አጥተናል።

ሆኖም ግን ችግሩ ለሌሎች ፖለቲካዊ ጉዳይ ሊያደርጉት ይችላሉ። እኛ ግን ታላላቅ ወታደራዊ ማዕረግ ያላቸውን ግለሰቦች ማጣት እንደሐገር ያሳዝነናል። በፍጹም መደገም እንደሌለበት እና በሠላማዊ ንግግር መጨረስ እንዳለበት እናምናለን።

ለሞቱት ነብሳቸውን በአፀደ ገነት እንድያሳርፍልን እየተመኘን፣ ለሌሎች ምህረትን እንመኛለን።

ነብስ ይማር😥😥😥

አጉልዞ ጥያቄ 24/05/2026

አስታውሱ፥ ተላላኪ አትሁን/ኑ።

እንዴት ሰው በራሱ ቤት፥ ሌላ የሚወስንለት ሰውን ያውም ተሽጦ፣ ባሪያ ሆኖ፥ ለሚስቱ ባል ይገዛል⁉🤔

ለዛ ነው፤ ሰዎች ለሆዳችሁ፣ ለከርሳች፣ ለጊዜያዊ ጥቅምና ዝና እራሳችሁን አትሽጡ። ህሊናችሁን በከርሳችሁ አትለውጡ/አትሸጡ የምንላችሁ። ነገ ደግሞ ሌላ ገበያ ላይ ገዢ ፍለጋ እንደምትንከራተት ያውቃሉ። ይንቁሐል። ያራክሱሐል።

አቶ ስብሐት ነጋ በአንድ ወቅት እንድህ ሲል ነበር በአንድ የያየሰው ሽመልስ ኢንተርቪው የተናገረው፦ "ላኪ ለጥቅሙ ነው። ተላላኪ ግን የራሱን ጥቅም ነው የሸጠው!" በማለት የተናገረው።

እናም እናንተ በሐገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ወገኖቻችን የወለጋ ተወላጆች፦
●ወገን መስለዋችሁ፣
●የተቀየማችሁትን ሰው የተበቀሉላችሁ መስሏችሁ፣
● መንግስትንም የሚገለብጥሏችሁ መስሏችሁ፣ የራሳችሁን ጥቅም ለሌሎች ሽጣችሁ፣
● በራሳችሁ ቤትና ንብረት ሌሎችን አዛዥ በማድረግ፣ የህዝባችንን ጥቅም ከመሸጥ አልፋችሁ፣
●አዋቂና ታዋቂ የሆንን መስሏችሁ፥
● የራሳችሁን ታጋዮች ስማቸውን እየጠራችሁ ስትሳደቡ፣ በሐሰት ስትከሱ ስትኮንኑ የነበራችሁት።

አሁንስ ተጸጸታችሁ⁉ አረጋገጣችሁ⁉ ወደፊትስ ምን ለመስራት አሰባችሁ⁉

አሁንም በድጋሚ አስታውስ፥ በገዛ ቀዬህ፣ በራስህ ሞት፣ በራስህ ህዝብ ላይ ታምጽባቸው ዘንድ፣ ክህደት ትፈጽምባቸው ዘንድ የገዙህ ሰዎች፣ ነገ አንተን እንደሚበሉህ እንዳትዘነጋ።

በቅድሚያ አስታውስ!! በሬ የሚሸጠው ለሁለት አላማው ነው። አንደኛ በሙያው፤ ሁለተኛው ለስጋው ነው። ስለዚህ ሰንጋ መሆንህን ወይስ ባለሙያ መሆንህን አስታውስ። ሰዎች የገዙህ፣ የመረጡህ በዬትኛው አቋምህ ነው። ለስጋ የተገዛ ሰንጋ፣ ለሙያ አይታማም። መጀመሪያውኑ የተገዛው ለስጋው (ለጮማው) ነው።

የተሰጠህበትን (የተፈጠርክበትን) ተሰጥኦህን ለይ። እወቅ። ለዚህ ነው፤ ሰዎች ከመሬት ተነስተው የወደዱን፣ ያከበሩን ያገዘፉን የመሰሉ ሰዎችን በተመለከትክ ጊዜ፦ > በማለት በአባባላቸው የሚያስጠነቅቁን።

ስለዚህ ትናንት እነሱን አልገዛም፣ አልሸጥም፣ ህዝቤንም አልሸጥም ያላቸውን ሰው፣ በሐሳብም፣ በብዕርም፣ በሪዎትም ....... ወዘተ ማሸነፍ ሲያቅታቸው፤ አንተንና መሰሎችህን ገዝተው ሲያሰድቡህ፣ ሲያዘልፉህ፣ በሐሰት ሰውን ሲያስኮንኑህ የነበሩት።

እነዚያ ሰዎች በገዙበት ዋጋ ልክ እንኳን ዋጋ እንደሌለህና በገዙት ነገር በበቂ ሁኔታ ማትረፍ እንደማይችሉ ሲያውቁ፣ ዋጋህን ዳግም አራክሰው፣ አንዴ ከስረናልና ዳግም ዋጋ አልባ አድርገው የሚጥሉህ።

ትናንት አቅም ያለህ፣ እውቀት ያለህ፣ ብልህና አስተዋይ አድርገው ያዳነቁህ ሰዎች ለምክክር እንኳን ቦታ እንደማይሰጡህ አሁን ካወክ፣ ዳግም ላለመሳሳት እና ላለመላላክ ይቅርታ ለራስህና ለህዝቡ ቃል መስጠት ይጠበቅብሐል።

መልካም ሰንበት!!"
ሰኔ 16-2018ዓ.ም። ዕለተ-ሰንበት (እሁድ)
አጉልዞ_ጥያቄ ከአንገር_ጉትን_ወለጋ
አድስ አበባ ኢትዮጵያ
በቴሌግራም ቻናላችን ሊንክ👇👇👇
https://t.me/my_Angergutin_77

በዩቲዩብ ቻናላችን ሊንክ👇👇👇

https://www.youtube.com/

አጉልዞ ጥያቄ ይህ ቻናል በወለጋ አንገር ጉትንና በዙሪያው ለሚገኙ ህዝቦች የሚወያዩበት፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እንድሆን ታስቦ የተከፈተ ህዝባዊ ቻናል በመሆኑ በሓላፊነት ስሜን፣ በሰከነ መንገድ ለህ...

24/05/2026

እንዴት ሰነበታችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያን በሙሉ፦
***********///************///************
በሰሞኑ ከነበረው የስራ ጫና አንፃር ላልተወሰነ ጊዜ ከሚድያው ራቅ በማለት ስራችንን ጨርሰን ተመልሰናል። ለዚህ ላበቃን ፈጣሪን እናመሰግናለን።

አጉልዞ ጥያቄ ለስምንት አመታት በተከታታይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል፣ የህዝቦችን ችግር፣ መከራ፣ ፍላጎት እና ጥያቄ እንድሁም አጠቃላይ ሁነቶችን ሲሰራ ቆይቷል።

አሁን ደግሞ በመላው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የነበረውን የተዛባ እይታ ወደአንድ መስመር አምጥቶ፣ በሐሳብ የበላይነት አሽናፊ እና ተሸናፊ ሳይኖር፣ ሁላችንንም አሸናፊ በሚያደርገን ህጋዊ ነገሮች ተግባራዊ ለማድረግ፣ ቀሪ የሚለቃቀሙ ስራዎችን በመስራት ውጤታማ ሆኗል።

ወቅቱ ሐገራችን ለ7ተኛ ጊዜ ምርጫ ለማድረግ የተወሰኑ ቀናቶች የቀሩበት ወቅት እንደመሆኑ መጠን፣ መንግስት እና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በወለጋ ህዝብ ጥያቄ ዙሪያ በቀዳሚነት ለመስራት የሚያስችላቸውን የተሟላ መረጃ በማዘጋጀት ለሁሉም አቅርቧል።

ለሁላቸውም ግልጽ ተደርጎ በመቅረቡ፣ መንግስት ለህዝቡ ጥያቄ አዋጭ የሚለውን ለማድረግ አመቺ ተደርጎለታል።

ሌሎችም ጥያቄያችን ፍትሐዊና ህገመንግስታዊ በመሆኑ በዬትኛውም መመዘኛ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆን እንዳለበት ከስምምነት ላይ ለመድረስ ተችሏል።

አጉልዞ ጥያቄ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እንጂ፣ የእርስት ጥያቄ የለውም። መንግስት የመሆንና መንግስትን በሐይል የመገልበጥ ፍላጎት የለውም።

እኛ ከውስጥም፣ ከውጭም ተጻራሪ ሐይሎች ጋር በጥቅም ተሳስሮ፣ ሐገርንና መንግስትን እንድሁም በህዝቦች ስቃይ ላይ ተንጠልጥሎ የመጉዳት አቅምም፣ ፍላጎትም፣ ምኞትም፣ ሐሳቡም የለውም።

የእኛ ጥያቄ ግልጽ ነው። እንደሐገር በህገመንግስቱ መሠረት ልክ እንደሌሎቹ ክልሎች እንደሚገኙት የብሔረሰብ ተወላጆች በማንነታችን፣ በቋንቋችን፣ ብሔረሰብ ማንነታችን፣ በባህላችን ...ራሳችንን በራሳችን እናስተዳድር የሚል ነው።

ይሄ ጥያቄ ደግሞ የሚፈታው በጠበንጃ ሳይሆን፣ በህግና በህገመንግስቱ መሠረት በመሆኑ፣ ቀላል ችግርን የማስወገጃ ዘዴ ብዕራችንን ብቻ በመጠቀም ነው።

ስለሆነም በወለጋ የተፈጠረውን የህዝብ ችግር እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ ሐይማኖታዊ እና ነገዳዊ የፖለቲካ አስተሳሰባቸውን ለማራመድ የሚፈልጉ ሐይሎች፥ የእኛን ምስጥራዊ ጥቅማችንን የምናስከብርበትን አካሔድ ለሌላ አላማ እንዳይጠቀሙበት በመስጋት፥ ስራዎቻችንን በሚስጥር ማስኬድን መርጠን፣ ዋና ዋና ነገሮችን ከዚህ ቀደም ጠቁመናል። ተናግረናል። ጽፈናል። ተንትነናል።

አሁን ጊዜው የወለጋን ህዝብ ልፋት፣ ምርቱን ከገለባው ለይተን፣ ምርቱን የምንሰበሰብበት ወቅት በመሆኑ፤ ማንኛውም የወለጋ ተወላጅ፥ ከሚያደናግሩ፣ ከሚያወዛግቡ፣ ከሚያጭበረብሩና የወለጋ ተወላጆች ሆነው፣ የህዝቡን ችግር በትናንሽ ጥቅማጥቅም ከሸጡትና እየሸጡ ካሉት ወገኖች ራሳቸውን በማራቅ ወደ መቅረብ የሚጠይቅበት ወቅት መሆኑን ልትዘነጉት የማይገባ ወሳኝ ወቅት ነው።

በመጨረሻም የወለጋን ህዝብ ችግር "በእንቅርት ላይ ጆሮ ገድፍ!" ካደረጉትና በሰሞኑ እርስበርሳቸው ይበላላሉ። ይጠፋፋሉ። እውነተኛ ሰዎች ይወጣሉ። ሐሰተኞች፣ አስመሳዮች እና ተላላኪዎች ይበጠራሉ። በሰሯቸው ግፎች ይጸጸታሉ።....... ወዘተ ባልነው መሠረት እነሆ፥ ዛሬ አንድ በአንድ የምንመለከተው ይሆናል።

መልካም ሰንበት!!"
ሰኔ 16-2018ዓ.ም። ዕለተ-ሰንበት (እሁድ)
አጉልዞ_ጥያቄ ከአንገር_ጉትን_ወለጋ
አድስ አበባ ኢትዮጵያ

17/05/2026

ከእኛ ጋ አትሳፈጥ ትበላለህ። የኔ ትውልድ ጭቆናን የሚሸከምበት ጫንቃ የለውም። ትናንት ዱርዩ፣ ወያላ... ወዘተ የምትለው ነው ዛሬ የአንተን ህይወት እየታደገ ያለው።

14 አይነት ግብር በማህተም አዘጋጅተህ፣ ህዝቤን የመኖር ተስፋቸው ተሟጦ አደጋ ላይ እየጣልክ ለምን ተነካሁ አትበል። ገና መሐል ከተማ ነኝ ብለህ የምትፎክር እና ስትፎክር የነበርከው የጊዜ ጉዳይ ነው። ትገረፋለህ ብቻ ሳይሆን፣ በደንብ ሒሳብ እናወራርዳለን።

የኔ ትውልድ የተፈጠረው ለነፃነት እንጂ፣ ለባርነት አይደለም። ጠብቀኝ ስልህ👊👊👊

17/05/2026

የሰው ልጅ ከብዙ ስጦታዎቹ ውስጥ ቢያንስ አንደኛውን ወይም ሁለተኛውን እንደየ መጠኑ ይሰጠዋል። እንዴት ይችን ልጅ ጥበብን ከውበት፣ ውበትን ከለዛ፣ አንደበትን ከአርበኝነት፣ ሐቀኝነትን ከነ ክብሩ ለሰው ልጅ በአንዴ ሊሰጠው ይችላል⁉

Yeju Genet (የጁ ገነት) በሚል የፌስቡክ ገጽ በቅርቡ ነው ማየት የቻልኩት። ድሮም የጁ እሳት ይዟል በእጁ ይባላል።

ይችን እህታችንን የምታውቋት ለአማራ ህዝብ እንደአንቺ አይነት ሐቀኛ፣ ጀግና፣ ባለመክሊት የታደለች ያለስስት አይነት ሰው እንጂ፣ ሌላ አይደለምና የተጎዱት የወለጋ ህዝቦች አድናቆታችን ከልብ መሆኑን አድርሱልን።

Yeju Genet ከልብ ከልብ ባለሽበት እናከብርሻለን። እንወድሻለን። ክበሪልን። አሁንም ወዳጅ የመሰሉ ሰዎች እንዳይጠልፉሽ ተጠንቀቂ።

17/05/2026

ከነቀምት ወደ አአ መዉጫ አዲያ ድልድይ የሚባል ቦታ ላይ የደረሰ አደጋ ነው በእርጋታ እናሽከርክር።

16/05/2026

አቶ ጅብሪል እባቡ በሰሞኑ በገጠመው ድንገተኛ እክል ምክንያት፣ ስልኩ የማይሰራ ሆኖ፣ በኪረሙ ወረዳ ቤቱን፣ መጋዘኑንና የባህርዛፍ መሬቱን በሐሰተኛ ከሳሽና ምስክር እስከዞን ድረስ ወስደው የነበሩት ግለሰቦች እና ቡድኖች የእሱን ድንገተኛ ችግር በመጠቀም እንደሐሰተኛና ውሸት ቢቆጥሩም፣ ዛሬ ከዚያ ውስብስብ ችግር ተላቆ በመውጣቱ አግኝተነዋል።

ስለሆነም የአቶ ጅብሪል የመጋዘን ሁኔታ ወረዳው ሁለት ግዜ ጫረታ በማውጣት መሸጡንና የግለሰብ ተጠያቂነት እንዳይኖር በማህበር ማዘዋወራቸውን ለማወቅ ችለናል።

ይሁን እንጂ መንግስት የአቶ ጅብሪል ህጋዊ ቤት በግለሰብም ይሁን በማህበር በሐሰት ለተወሰነው ውሳኔ፣ አሁንም በተጨማሪ ሌላ ወንጀል እንዳይሰራበት በባንክ አስይዘው ብድር እንዳይወስዱበት እገዳ ተደርጎበታል።

በመጨረሻም በኪረሙ፣ በአሙሩ፣ በጉትን፣ በቱሉጋና፣ በሻምቦ፣ በጃርቴ ጃርዴጋ፣ በሐሮአድሳለም፣ በሉጎ፣ በኡኬ፣ በመ.10; በነቀምቴ፣ በአኖ፣ በሲቡስሬ፣ በባኮትቤ፣ በአርጆ፣ በቶሌ፣ በጊምቢ፣ በነጆ፣ በጊዳአያና፣ በደንቢዶሎና ... ወዘተ አከባቢዎች ንብረቶቻቸው በግፍ የተነጠቁ አካላት ለጊዜው በፍርድ ቤት ወረዳ ባቋቋማቸው ግለሰቦች እና በሐሰተኛ ምስክሮች የተወሰደ ቢመስልም፣ አጉልዞ ጥያቄ ባዘጋጀው የሰነድ መላኪያ በመግባት በባንክ ንብረቶቻቸውን እንዳይበደሩበት ማድረግ ተችሏል።

በዚህ ረገድ መንግስት ባደረገው እርምጃ እያመሰገንን፣ አሰራሩን በአጉልዞ በውስጥ መስመር ማወቅ የሚችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

አቶ ጅብሪል እባቡ ህጋዊ ንብረቱን የያዛችሁ የማህበር አባላትም ይሁን ግለሰብ፣ በቅርቡ ገቢ የምትደረጉ ይሆናል። ሌሎችም በሌሎች አከባቢ የምትገኙ፣ በተመሳሳይ ወንጀል የምትገኙ የሚገጥማችሁ እድል ተመሳሳይ መሆኑን እወቁ።

https://t.me/my_Angergutin_77

14/05/2026

አቶ ሐቢቡ ንጉሴ የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን የአቤደንጎሮ ወረዳ የመ.25 (ለጋሐዊ) ቀበሌ ኗሪ ነው። በአከባቢው መልካም ስራዎችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሰዎችን በቀናነት የሚያግዝ በጎ ሰው ነው።

በወለጋ ውስጥ ከተፈጠረው ጋንግስተሮች መካከል የሰውን ልጅ ስም ለጥፎ ማሰርና ማሳደድ የተለመደ የመጣ ከሆነ ሰነባብቷል።

ታድያ ወጣቱ ሐቢቡ ንጉሴን በባለፈው ጊዜ የሚኒሻ አባሉን ሞባይል መቀማታቸውን ለመከላከያ ሠራዊት በመደወል ያስያዝከው አንተ ነህ በማለት እና መረጃውን ለሚድያ የሰጠኸው አንተ ነህ በሚል አስረውታል።

መንግስት በየቀበሌው በየወረዳው የሚገኘውን ካቢኔ የፈጠራቸው ሚኒሻዎች በሚሰሯቸው ግፎች አማካኝነት በተደጋጋሚ ለመንግሥት ጉዳዩን ከመካከለኛው ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅርን እንድፈትሽ እየተጠየቀ እያደመጥን ነው።

አቶ ሐቢቡ ንጉሴ በአንገር ጉትን መግቢያ ላይ ሚኒሻዎች ፈጸሙት ተብሎ የመከላከያ ሠራዊት ከቱሉጋና ከተማ ተነስቶ፣ ለተበዳይ እጅ ከፈንጂ ይዞ ንብረቱን ማስመለሱና በህግ እንድጠየቅ ማድረጉ ምናልባትም እውነት ከሆነ ያሸልማል እንጂ፣ ለእስራትና ለእንግልት የሚዳርግ አይደለም።

ነገሩ ግን ምክንያት ለማድረግ ሞከሩ እንጂ፣ ለጉትን ሚኒሻ የቱሉጋና ሚኒሻ ምንም አይመለከተውም ነበር። ምክንያቱም በዞንም፣ በወረዳም አይገናኙም። ቢሆንም ግን በቱሉጋና ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ውስጥ ያለምንም ክስ፣ ወደፍርድ ቤት ሳይሔዱ የታሠሩት ግለሰቦች መረጃዎችን በአጉልዞ ጥያቄ በመውጣቱ ተጠያቂ ላለመሆን ምክንያት እየደረደሩ፣ አሁንም የመከላከያ ሠራዊት በቦታው እያየ ዝምታን መርጧል።

መንግስትም የመረጃ እጥረት ሳይሆን፣ የወለጋን ህዝብ ከነችግሮቻችን ትቶን፣ አጀንዳው ቀይ ባህር በሚል ተጠምዷል።

ስለሆነም አቶ ሐቢቡ ንጉሴ የተባለውን ግለሰብ እና በቱሉጋና ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ታስረው የሚገኙትን በሙሉ ተፈተው እንድለቀቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።

በሰብዓዊ መብቶች ላይ በኦሮሚያ ክልል የኢሰመኮ ተወካይ ጉዳዩን አሳውቀን፣ በነቀምቴ ለሚገኘው የኢሰመኮ ተወካይ ሐላፊ ጉዳዩ እየተከታተሉት ነው።

ጉዳዩ ተመርምሮ እልባት እንድያገኝ እንጠይቃለን። እኛ አግባብነት የሌለው እስራት፣ ዝርፊያ እና ግድያን በጽኑ የምንቃወመውን ያህል፣ ወንጀለኛ ካለ ግን በህግ አግባብ አይጠየቁ አንልም። ነገር ግን የግፍ እስራትን እንቃወማለን። መፍትሄም እንጠይቃለን።

ምስል ከፋይል

13/05/2026

ይድረስ በቱሉጋና፣ በዳልቾ፣ በወባንጭ፣ በመ.24&25 እንድሁም በመላው በአንገር ጉትንና በዙሪያው ለምትገኙት በሙሉ፦

በጠየቃችሁት መሠረት የነጋዴው ጉዳይ አስመልክቶ፣ በቀደመው መልዕክታችን በመቶ ሚሊዮን በሚገመት ገንዘብ ከህዝቡ የእህል ገንዘብ ይዞ መሰወሩን አስመልክቶ እንዳግዘውና ለስራ ምክንያት የወጣ እንጂ፣ ጠፍቶ አይደለም በሚል ለህዝቡ የተሳሳተ መረጃ የሠጡት ሶስት ሰዎች ዝርዝር አስቀምጥላችኋለሁ።

በወቅቱ ህዝባችን ከነጠፋበት ገንዘብ በተጨማሪ ነብስ ከማጥፋት እንድቆጠብ ብለን ለማረጋጋት ባደረግነው ነገር በፍጹም አንጸጸትም። ገንዘብ ነገ ይገኛል። የሰው ነብስ ግን አይገኝም። ነብስ ማጥፋት ደግሞ ወንጀልም ነው። ህዝባችን ሁሉንም ከሚያጣ ብለን ለማረጋጋት ባደረግነው ነገር የማይንቆጭ ቢሆንም፣ እውነታውን ግን እስከዛሬ ባለማሳወቃችን ይቅርታን እንጠይቃለን።

ኡመር ወጤ የተባለውን ግለሰብ የሚድያ ትብብር እንድናደርግለትና በወቅቱ ኡመርንም ከተደበቀበት በስልክ እንድናገኘው ያገናኙንና በሚያምንበት በቁርዓን የማለው የስልክ ቅጅ እንድሁም በቤተሰብ ትስስር የነበሩት ሰዎችን ለማሳወቅ እንገደዳለን።

በመጨረሻም ኡመር ወጤ የተባለው ግለሰብ መውጣቱና ቃሉን ማጠፉ ሳያንስ፣ የበርካታ ህዝቦችን ገንዘብ ይዞ የሌሎችን ቤት አፍርሶ፣ በድጋሚ በሊቢያ እንደታገተ ተደርጎ የሚናፈሰውና ህዝቡ ገንዘብ እንድያዋጣ የተደረገበት ምክንያት፣ ሆን ተብሎ ሌሎች ገንዘባቸውን የተነጠቁ ሰዎች በቤተሰቦቹ ላይ ሌላ እሳቤ እንዳይኖራቸው እንጂ፣ እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ በራሳችሁ ገንዘብ እየተዝናና መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነወ።

ይህንን ማጭበርበር ለመስራት የተጠቀመባቸው የባለቤቱ ቤተሰቦችና በንግድ ስራ የነበሩ ጓደኞቹ እና ቤተሰቦቹ ሲሆኑ፣ የሁላቸውንም የስልክ ልውውጥና እውነታውን ከተወሰነ የውይይት ጊዜ ቡኋላ፣ ለህዝቡ ያለበትን በአንደበታቸው ተናግረው የማያሳውቁ ከሆነ፣ በገፃችን ኡመር ወጤን በመቶ ሚሊዮን ገንዘብ ይዞ እንድወጣ የተባበሩትን የምናጋልጥ ይሆናል።

ከእውነት ጎን እንጂ፣ ለሐሰተኞች ቦታ የለንም!!

13/05/2026

የመ.21 ህዝብ ተጨፈጨፉ ብሎ ነበር አንበሳው አርበኛ ፋኖ ጌጤ ግርማ፣ የሶስት ሬጅመት ሰራዊትን ለመግጠም 20 የማይሞሉ ሰራዊቱን ይዞ ገብቶ መስዕዋትነትን የከፈለው።

የኛ ሰው ጀግኖችን እያስበላ በዘፈንና በቀረርቶ ሌላውን ለሆድ አደር ተላላኪዎች ቦታውን፣ ጀግንነቱንና አርበኝነቱን አሳልፎ የሰጠው።

ዛሬ ህዝባችን እያለቀሰ፣ ጸጉሩን ላጎፈረ ቦታ የለኝም።

ጓድ አርበኛ ፋኖ #ጌጤ ግርማና ጓድ አርበኛ ፋኖ #አለልኝ ነብሳችሁን በአጸደ ገነት ያኑርልን!! የታገላችሁለትን አላማ ለማስቀጠል፣ በሚያስችል ጀግንነት ላይ አይደለንምና የጀግንነት መንፈሳችሁ አይለየን🙏🙏🙏🙏

ነብሳችሁን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን😥😥😥

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Address

Addis Ababa