እስልምና vs ክርስትና

እስልምና vs ክርስትና

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from እስልምና vs ክርስትና, Education, Addis Ababa.

02/02/2023

#ይነበብ #ይነበብ
ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።
²² በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።
²³ የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።
²⁴ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል።
²⁵ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።
²⁶ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል።
²⁷ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ።
እስልምና vs ክርስትና

25/01/2023



መንፈስ "ፈጣሪ" ነውን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

40፥62 ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَأَنَّىٰ تُؤْفَكُونَ

በባይብል ሁሉንም ሰው የፈጠረ አንድ አምላክ አለ፥ ይህ አንድ አምላክ የሁሉ ነገር ፈጣሪ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን?
ኤርምያስ 51፥19 የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፥ እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነው፥ ስሙም የሠራዊት ጌታ "ያህዌህ" ነው።

ያህዌህ አምላክ ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፥ ይህ አንድ አምላክ ሰው ያበጀውም በእጆቹ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው።
መዝሙር 119፥73 እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም።

የያህዌህ እጆች ልክ እንደ ያህዌህ እራሳቸውን የቻሉ ማንነት ሳይሆኑ የምንነቱ መገለጫ ባሕርያት ናቸው፥ እነርሱ "ሠሩ" ስለተባሉ በስም መደብ "ሠሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ ያህዌህ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስ እፍ ስላለበት እና በአፉ እስትንፋስ ስለፈጠረ የአፉ እስትንፋስ "ፈጣሪ" አይደለችም፦
ዘፍጥረት 2፥7 በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት።
ኢዮብ 33፥4 የያህዌህ መንፈስ ፈጠረችኝ፥ የሁሉን ቻዩ እስትንፋስ ሕይወት ሰጠችኝ። רֽוּחַ־אֵ֥ל עָשָׂ֑תְנִי וְנִשְׁמַ֖ת שַׁדַּ֣י תְּחַיֵּֽנִי׃

በሴት አንቀጽ "ዓሳቴኒይ" עָשָׂתְנִי ተብሎ የተቀመጠው የግሥ መደብ "ፈጠረችኝ" ማለት ነው፥ "የያህዌህ መንፈስ" ማለት "የሁሉን ቻዩ እስትንፋስ" ማለት ነው፥ እስትንፋሱ "ፈጠረች" ስለተባለ "ፈጣሪ" ከተባለች እጆቹ "ሠሩ" ስለተባሉ በስም መደብ "ፈጣሪዎች" ይባሉ ነበር። ቅሉ ግን እስትንፋስ ሆነ እጆቹ መፍጠሪያ እንጂ ፈጣሪዎች አይደሉም። ሌላ ናሙና እንመልከት፦
መዝሙር 8፥3 የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ።
መዝሙር 102፥25 ሰማያትም የእጆችህ ሥራ ናቸው። וּֽמַעֲשֵׂ֖ה יָדֶ֣יךָ שָׁמָֽיִם׃

የያህዌህ ጣቶች እና እጆች ሰማያትን ስለሠሩ በስም መደብ "ፈጣሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ የያህዌህ መንፈስ ስለፈጠረች "ፈጣሪ" አትባልም። ተጨማሪ ናሙና እንመልከት፦
ኢሳይያስ 48:13 እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች።

የያህዌህ እጅ ምድርን ስለመሠረት እና ቀኙ ሰማያትን ስለዘረጋች በስም መደብ "መሥራቾች" "ዘርጊዎች" ወይም "ፈጣሪዎች" እንደማይባሉ ሁሉ በተመሳሳይ የያህዌህ መንፈስ ስለፈጠረች "ፈጣሪ" አትባልም።
እንግዲህ የያህዌህ መንፈስ ልክ እንደ ያህዌህ ማንነት ካለው የያህዌህ እጆች፣ ጣቶች፣ ቀኙ ብዙ ማንነቶች ሊሆኑ ነው፥ ያ ደግሞ ሥላሴን ከሦስት በላይ ሊያደርግ ነው። ነገር ግን በግሥ መደብ የሚመጣ ድርጊት ባለቤቱ ያህዌህ ስለሆነ "ሠሪ" "ፈጣሪ" "መሥራች" "ዘርጊ" እርሱ ብቻ ነው እንጂ የእርሱን ባሕርይን እየሸነሸንን ማንነት አበጅተን ፈጣሪ አናረጋቸው። ለምሳሌ፦
ኢሳይያስ 1፥20 እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የያህዌህ አፍ ይህን ተናግሮአልና።

24/01/2023

#ሼር

24/01/2023

የአምላክ ጥበብ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

43፥59 እርሱ በርሱ ላይ የለገስንለት ለእስራኤለም ልጆች ተአምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

ፈጣሪ በጥበብ ምድርን እንደ መሠረተ፣ በማስተዋልም ሰማያትን እንደ አጸና እና በእውቀቱ ቀላያት እንደ ተቀደዱ የምሳሌ ተናጋሪ ይናገራል፦
ምሳሌ 3፥19 ያህዌህ በጥበብ ምድርን መሠረተ፥ በማስተዋልም ሰማያትን አጸና። በእውቀቱ ቀላያት ተቀደዱ፥ ደመናትም ጠልን ያንጠባጥባሉ።

በቁርኣን ውስጥ አሏህ አፍ እንዳለው ያልተገለጸ ሲሆን በባይብል ውስጥ ግን አምላክ አፍ ኖሮት ከአፉ ጥበብ፣ ማስተዋል፣ ዕውቀት እንደወጡ ይናገራል፦
ሲራክ 24፥3 እኔ(ጥበብ) ከልዑል "አፍ ወጣሁ" ምድርንም እንደ ጉም ሽፈንኋት።
ምሳሌ 2፥6 "ከ-"አፉም" እውቀት እና ማስተዋል "ይወጣሉ"።

ፈጣሪ እና ጥበቡ ሁለት የተለያዩ ማንነት ሳይሆኑ ጥበብ የራሱ ባሕርይ ሲሆን ፈጣሪ የራሱ ማንነት ያለው ምንነት ነው፦
ኢሳይያስ 44፥24 ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ "ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?
ምሳሌ 8፥27 ሰማዮችን በዘረጋ ጊዜ አብሬ ነበርሁ፥ በቀላያት ፊት ክበብን በደነገገ ጊዜ፥

ፈጣሪ ሰማያትን ሲዘረጋ እና ምድርን ሲያጸና ከእርሱ ጋር ማንም የለም፥ ጥበብ ግን ማንነት ሳትሆን የራሱ ባሕርይ ስለሆነች በምሳሌአዊ ንግግር "ሰማዮችን በዘረጋ ጊዜ አብሬ ነበርሁ" አለች። ይህ የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌ ነው፦
ምሳሌ 1፥1 የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች።
ምሳሌ 8፥1 በውኑ ጥበብ አትጮኽምን?
ማስተዋልስ ድምፅዋን አትሰጥምን?

ጥበብ እና ማስተዋል ከአምላክ አፍ የሚወጡ ባሕርያት ሆነው ሳለ ጥበብ አትጮኽምን? ማስተዋልስ ድምፅዋን አትሰጥምን? መባሉ “ፈሊጣዊ አገላለጽ”idiomatic expression” ነው፥ ለምሳሌ፦ እራሳቸውን የቻሉ ማንነት ሳይኖራቸው የተናገሩ ቀላይ እና ባሕር ተጠቃሽ ናቸው፦
ኢዮብ 28፥14 “ቀላይ፦ “በእኔ ውስጥ የለችም” ይላል፤ ባሕርም፦ “በእኔ ዘንድ የለችም” ይላል”። תְּהֹ֣ום אָ֭מַר לֹ֣א בִי־הִ֑יא וְיָ֥ם אָ֝מַ֗ר אֵ֣ין עִמָּדִֽי׃

ቀላይ እና ባሕር እራሳቸው የቻሉ ቅዋሜ-ማንነት ወይም እኔነት ሳይኖራቸው መናገራቸው ከተገለጸ እንግዲያውስ ጥበብ መጮኽዋ እና ማስተዋል ድምፅ መስጠቷ አያስደንቅም። በምሳሌ ስምንት ውስጥ ያለውን ምሳሌ ብቻ ሳይሆን ትርጓሜም ነው፦
ምሳሌ 1፥6 ምሳሌን እና ትርጓሜን የጠቢባንና ቃልና የተሸሸገውን ነገር ለማስተዋል።

"ትርጓሜ" የተባለው በውስጠ ታዋቂነት ኢየሱስ ጥበብ ተብሏል፥ እራሱም በሦስተኛም መደብ ስለራሱ፦ "ጥበብ በሥራዋ ጸደቀች" ብሏል፦
ማቴዎስ 11፥19 የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ፥ እነርሱም፦ እነሆ፥ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ ይሉታል። "ጥበብም በልጆችዋ ጸደቀች"።

ለኢየሱስ በላተኛ፣ የወይን ጠጅ ጠጭ፣ ቀራጮች፣ ኃጢአተኞች ወደ እርሱ በመምጣት ወዳጆች ሲሆኑ "ጥበብ በሥራዋ ጸደቀች" ተባለ፥ ኮዴክስ ኤፍሬማይ "በልጆችዋ" τεκνων αυτης ሲል ኮዴክስ ሲናቲከስ ደግሞ "በሥራዋ" εργων αυτης ይላል። ኢየሱስ የአምላክ ጥበብ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት በክርስቶስ ርስትን ለመቀበል ስለፈጠረው ነው፦
1 ቆሮንቶስ 2፥7 ነገር ግን እ

23/01/2023


“ደግሞም መጽሐፉን ማንበብን ለማያውቅ፦ ይህን አንብብ ብለው በሰጡት ጊዜ እርሱ፦ ማንበብ አላውቅም ይላቸዋል።”
— ኢሳይያስ 29፥12
#በቁረዓን

اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Addis Ababa